የኢሳት የውይይት መድረክ ከየት ወዴት!!?
እዬገደለ የመጣ ቅጥረኛና ፋሽስት ኃይል የሚኖረውም እየገደለ ነው። (እምብኝ በል-ጎፍንን )
እምብኝ በል-ጎፍንን
እዬገደለ የመጣ ቅጥረኛና ፋሽስት ኃይል የሚኖረውም እየገደለ ነው።
የሰው ልጅ ህይወት እጅግ በጣም ውድ ነው በድሮው ጊዜ የሰው ልጅ ሕይወት ይቅርና ሰው የሚመገባቸው እንሥሣትም ሊታረዱ አንዳንድ ቅድመ ዝግጅቶች ሲደረጉ ቡናው ሲፈላ እጣኑ ሲጨስ ጮፌው ሲነሰነስና ሊታረዱ ሲቀርቡ አራጁ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን በአዕምሮው ላይ ሥነ-ልቦናዊ መረበሽ እንደሚፈጥርበት ይታመናል። የለየለት ደም አፍሳሽ ከሆነ ግን ይህ ላይከሰት ይችላል። ታራጆቹ እንሥሣትም በአራጃቸው ወይም በገዳያቸው እጅ ሲገቡና ሲታሰሩ ጭንቀትና መረበሽ ሊኖር እንደሚችል እገመታለሁ። ሕይወት አንዴ ካለፈች አትመለስምና ከባድ ጫና ያሳድራል ነገሮች ሁሉ ይጨልማሉ ይህ ግን የሚሆነው ፈሪሃ እግዚአብሔር በልቡ ላደረበትና አርቆ ለሚያስብ ብቻ ነው። ለአረመኔዎቹና አምባ-ገነኖች ይህ በፍጹም አይገባቸውም።
በሰው ልጅ ላይ የሚፈፀሙ የግድያ ሁኔታዎችን ስንመለከት ዘርፈ ብዙ ሆነው እናገኛቸዋለን።-በሕግ ዓምላክ በሚባልበትና የሕግ የበላይነት ባለበት አገር በሰው ልጅ ላይ ሞት የሚፈረደው ተከሳሹ ወንጀል መፈጸሙ ታምኖበት በፖሊስ ተይዞ በአቃቢ ሕግ ክስ ተመስርቶበት ፍርድ ቤት ቀርቦ የፈጸመው ወንጀል በማስረጃ ከተረጋገጠ በኋላ የፍርድ ውሳኔዎች ይተላለፋሉ ወንጀሉ በሞት የሚያስቀጣ ከሆነ ዳኛው ወይም ዳኞች የሞት ፍርድ እንዲበየንበት ያደረገውን የወንጀል አፈጻጸም ድርጊትና ምክንያት በዝርዝር ከሕጉ ጋር እያገናዘቡ ካስረዱና ብዙ ተመልካችን እንዳያስደነገጥ ጥንቃቄ በማድረግ ወይም ዝግ በሆነ ችሎት በወንጀለኛው ላይ የሞት ፍርድ ይፈጸምበታል። ይህ እርምጃ የሚወሰደው የአካባቢውን ሕዝብ ደህንነት ለመጠበቅ ፤ሰላም እንዲሰፍንና የተረጋጋ ለማድረግ ዳግም የዚያ አይነት ወንጀል እንዳይፈጸምና ሕብረተሰቡ በሥነ-ምግባር የታነጸና በሕግ የሚገዛ እንዲሆን ለማድረግ ፤ የወንጀል መፈጸም ተግባርን እንዳይስፋፋ ጤናማ ሕብረተሰብ ለመገንባት የሚወሰድ የመንግሥት እርምጃ ነው። የፖሊስ ፤ አቃቢ-ሕግና የዳኛ ተግባሮች በፍጹም የማይለያዩ ተያያዥነት ያላቸው ሲሆን የአንድን ማሕበረሰብ ደህንነት ፤ ሰላምና ፀጥታ እንዲሰፍን ለማድረግ ደረጃ በደረጃ በየተቋማቸው ማድረግ የሚገባቸውን ፈጽመው መገኘትና አንዱ ሌላውን እያገዘ በጋራ የሚሰሩት የተቀናጀ የሥራ ውጤት ግቡን ይመታል።
ግለሰቦች ከሕግ በላይ በሆኑበትና በሕግ ዓምላክ በማይባልባቸው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሚኖረው ግድያን ወስደን ስንመለከት ደግሞ ሁኔታዎች ቦታቸውን ለቀው በግልባጩ እናገኛቸዋለን። ከዚህ በታች ስማቸውን የጠቀስኳቸው አገር መሪዎች በዓለም ላይ እንዲታወቁ ያደረጋቸው ተግባር ምን እንደሆነ አንባቢዎቼ በግልጽ የሚረዱት እንደሚሆን አምናለሁ። «ዘለው ኦፍ ጃንግል» (the law of jangle )«የጫካ ሕግ» በሚል የተፃፈች ትንሽ መጽሐፍ አንድ ወቅት ላይ አንብቤ ነበር። ያች ትንሽ መጽሐፍ ያዘለችው መልዕክት ሕግ ለምን እንደሚወጣና ጠቀሜታው ምን ያህል እንደሆነ ያሳደረብኝ ግንዛቤ እስከ መቼውም አይረሳኝም።መጽሐፏ በጫካ ስለሚኖሩ የዱር አራዊት(እንሥሣት) ህግ አለመኖርና ጉልበታሙ ወይም ጉልበታሞች ተባብረው ጉልበት የሌለውን አስገድደው ገድለው ተመግበው እንደሚያድሩና እንደሚውሉ እንደሚኖሩ ግልጽ አድርጋ ታሳያለች። በሩዋንዳ ፤ካሞቦዲያ እንዲሁም እስከ አሁን ድረስ ትኩሳቱ ባልበረደው ሶሪያ የምንሰማውና የምንመለከተው በዘረዘርኳቸው አገሮች የተካሄደውና እየተከሂያደ ያለውን ስንመረምር በምን አይነት መርህ እየተጓዙ እንደሆነና ጨካኞችና አምባገነኖች የሚፈጽሙትና የፈጸሙት ተግባር ከጫካው ሕግ ያልተለየና አረመኔያዊ ተግባር መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል።
አገርንና ዳር ድንበርን ለማስከበር ይሞታል፤ በሀሰት በፍርደ ገምድል ዳኛ ተፈርዶም ይሞታል፤ ሲሰርቁና ሰው ሊገድሉ ሲሞከርም ይሞታል ፤ በትንታም ይሞታል ፤ሌባ በረት ሲከፍት ፤ ከባለትዳር ሴት ሲልከሰከሱም ይሞታል፤ የሰው ቤት ሲበረብሩም ይሞታል፤ በሕመምና እድሜ ሲደርስም ይሞታል የሰው ልጅ ሕይወት ማለፊያዋ መንገድ ብዙ ነው። የእኔ መነሻ ግን ይህ አይደለም ሥልጣን ለመያዝና ከያዙ በኋላም ጨካኝና ነብሰ ገዳይ ሆነው ለመቀጠል የሚያስቡ አርመኔዎችን አስመልክቶ ትንሽ ለመግለጽ ያህል ነው። በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የዘውዳዊ አገዛዝ ዘመን የ1966ቱ የየካቲት የሕዝብ አልገዛም ባይነት ለማንበርከክ የተወሰዱትን እርማጃዎች ፤ቀደም ሲል በአርሲ ፤በጎጃምና በትግራይ የአርሶ አደሮችን ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ለማፈን የተደረግውን እርማጃ ፤በደርግ የወታደራዊ አገዛዝ ዘመን ለመገንጠል በተነሱ ጎጠኞች(ጠባብ ብሔረተኞች) የተወሰደው ፤አዲስ ሥር ዓት እንገነባለን ብለው በሕብረ- ብሔር ድርጅት ተቃውሞ ያነሱትን ትግል ለመበተን የተደረገውን ጥቃት ፤ህወሃት ከኤርትራ ጋር በጫረው ጦርነት የያለቁት የሁለት ወገን ትውልዶችና፤ «ራስ ሳይጠና ጉተና እንዲሉ» ወደ ሶማሊያ ሄደው ያለቁት ኢትዮጵያውያን ፤ ወደ ሩዋንዳ ፤ኮንጎ፤ ኮርያ የሄዱት ኢትዮጵያውያን ፤ ህወሃት ከበርሃ ጀምሮ በስውር የፈጀው ታጋይ የትግራይ ወጣት ፤ በቀን በአደባባይ መሠረት በሌለው ቂመኝነት የተገድሉት ኢትዮጵያውያን አሁንም በሰበብ አስባቡ እተጨፈጨፉ የሚገኙት ዜጎቻችን ሕይወት ቀጠሮ ተይዞለት በአዲስ ዓመት ይመለሳል የሚባል እንዳልሆነ ሁላችንም እናውቃለን ። በደርግ ጊዜ ደርግ ሕዝቡን ፈጀው እያሉ ነፍጥ አንስተው የተንቀሳቀሱት የዛሬዎቹ ገዥዎቻችን ለምን ሕዝባችን ይጨፈጭፋሉ?ወይስ ከጌታ ትእዛዝ ወርዶ ተፈቅዶላቸው ነው?ደርግ በሕዝብና በቀድሞ የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ባለሥልጣናት ላይ ኢ-ፍትሃዊ እርማጃ ወሰደ ያ አስፈሪ ሞት በራሱ ላይ መጣ። ህወሃት ከዚያ አስፈሪ ሞት የሚያመልጥበት ምን ብልሃት አገኘና ነው እንዲህ በእብሪት ተወጥሮ ሕዝብን በጅምላ የመጨፍጨፍ ተግባሩን እንደ ሰደድ እሳት እያቀጣጠለ ያለው? ግራኝ መሐመድ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ነበር በውጭ ድጋፍና እርዳታ በክርስቲያን ሕዝባችን ላይ ጨካኝ ጭፍጭፋ እንዳደረገ ታሪክ ዘግቦት አልፏል ። ቶርኮች ፤ ግብጾች እንዲሁም በዓረቦች ድጋፍ በሱዳን መሐዲስቶች(ድርቡሽ) እየተባለ የሚታወቀው በተመሳሳይና በተደጋጋሚ በክርስትና እምነት(በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሀዶ ሃይማኖት) ላይ ዘምተው አልተሳካላቸውም።ኢትዮጵያዊ የእስልምና እምነት ተከታዮችን እስላማዊ መንግሥት ሊያመጡብህ ነው ብሎ ሕዝብን ማስፈራራትና የማከፋፈል ዘመቻ ማካሄድ የት ሊያደርስ ነው? ለመሆኑ ህወሃት ምንስ እምነት ኖረውና ነው እስላማዊ መንግሥት ክርስቲያናዊ መንግሥት እያለ ሊሰብከን የከጀለው ? ይህ ከንቱ ውዳሴ ነው። ስለዚህ ሕዝቡ ጀሮውን ሊሰጥ አይገባውም ባይ ነኝ። መጀመሪያ የዜጎችን መብት ማክበር ይቅደም።የቻይና ባለሀብቶች ኢትዮጵያዊ ዜጎችን ተወልደው በአደጉበት እትብታቸው በተቀበረበት በአጥቢያቸው በአገራቸው ምን እየሆኑ እንደሆነ የሚያውቀው ህወሃት ዜጎቼ ተደፈሩ ብሎ ለምንስ እርምጃ አልወሰደም ? ከዚህ በላይ መርከስና መውረድ የበለጠ ምን ሊመጣ ይችላል? አቶ በረከት እናቱ ሲቀበሩ መድፍ እንዲተኮስላቸው አስደርጓል እናቱ ቢሞቱ እህት እንኳ የለውም የሚያዝን ልብ? እግዚአብሔር ያሳያችሁ!! እውን እኒህ ጠይም ደማማ እናት እንዲህ ተፈንክተው ደማቸውን እያዘሩ እንዲሄዱ ማድረግ ይገባል ? ምን አይነት ሥልጣኔስ ሊባል ነው? አሁን እኒህ እናት ጠቅላይ ሚንስቴር ለመሆን መንግሥትን ለመፈንቀል እያሸበሩ ነው? እንዲህ የተቀጠቀጡት? ኢትዮጵያ አገራቸው አይደለችም ? ወይስ ኢትዮጵያዊ መሆን የግድ ካልተቀጠቀጡና ደማቸውን እያዘሩ ካላሳዩ (ካልታዩ) ኢትዮጵያዊ ዜግነት አይገባቸውም ?ኢትዮጵያ እኮ የሁላችን አገር ናት። እንዴት ኢትዮጵያዊ ሆኖ ኢትዮጵያዊ እናቱን ደም እያዘሩ እንዲሄዱ ያደረጋል? ምን አይነት ሰው በላ ሥርዓት ነው የተፈጠረብን? ለመሆኑ ይህ በህወሃት ዘመን ተወልዶ በህወሃት የታጠቀ የአጋዚ ነብሰ በላ ጠመንጃ አንጋች ኃይል እናት እህት ሚስት ይኖረው ይሆን ? ሴቶችን እንደ ፊውዳሉ ሥርዓት ማናናቄ አይደለም እኒህ እናታችን ሴትና በእድሜ ጠና ያሉ ናቸው በምን ሂሳብ ነው የተደበደቡት በምን ምክንያት ነው ደማቸው እንዲፈስ የተፈረደባቸው? ይህ የህወሃት አጋዚ ሠራዊት አደብ የሚገዛውና ለሕግ የሚገዛው መቼ ነው ?እኛ ኢትዮጵያውያንስ መቼ ነው እንደበግ እየተጎተትን ከመታረድ የምንድነው? ድምፃችን ይሰማ በማለት ሁለት ዓመት አንዲት ጠጠር ሳይወረውሩ፤አንዲት ቅጠል ሳይበጥሱ የእምነት ነፃነታችን ይከበር ብለው ጥያቄ ስለአቀረቡ ችግሩ ምኑ ላይ ነው? መልሱን መስጠት ወይስ እያፈሱ ማጎርና መደብደብ በጥይት መቁላት? ኧረ እናስተውል ጎበዝ እስከ መቼ ነው ቀን እንዲህ ሊገፋ የሚችለው ?አሸባሪውስ ማን ሆነና ነው? አሸባሪ የሚሉት ለእምነታቸው ነፃነት የሚታገሉትን ነው ወይስ ከነዚህ ለእምነት ነጻነት ከሚታገሉት ኢትዮጵያዊ እስላሞች ውስጥ ሰርጎ የገባ አለ በሚል ነው ? ሰርጎ የገባ ካለ ለይቶ ማውጣትና በሕግ እንዲቀጣ ማድረግ የማን ተግባር እንደሆነ ከጠፋቸው እውነትም ጠፍተዋል ማለት ነው ቢጠፉም ይሻላቸዋል።
እየገደለ የመጣ ፋሽስታዊ ኃይል የሚኖረውም እየገደለ ነው። ያልኩበት አብይ ምክንያት ህወሃት በወርሃ የካቲት 1967 ዓመተምህረት እንደ ድርጅት ከመቆሙ በፊት የተለያዩ መጠሪያዎችን ይዞ ይንቀሳቀስ የነበረ ሲሆን በመጨረሻ ህወሃት በሚለው ስም ጸንቶ ሲቀጥል ከቀን አንድ ቀን ጀምሮ በሰው ግድያ የተጀመረ የራሱን አባላት ሳይቀር እየበላ ያደገ ድርጅት ሲሆን 17 ዓመት ደርግ ሥልጣን ላይ በነበረበት ወቅት 22ዓመት መላ አገሪቱን ከወረረ በኋላ ጊዜውን ያሳለፈው ሰው በመግደል ነው። ሰው መግደልና በደም መጠማት ደግሞ በሕክምና ሊድን የማይችል በሽታ መድኃኒቱ በመሰል እርምጃ(አክሽን )ሊወገድ የሚችል ከቫይረስ የከፋ በሽታ ነው። ህወሃቶች የፈለገው ብዛት ያለው ሰው ይሙት አንድ ሰው ይሙት ቅንጣት ታህል አይሰማቸውም የሚሰማቸው የሰው በላው ሥርዓት አስከባሪ ወይም እንደ አበደ ውሻ የሚክለፈለፈው አንጋች ሲሞት ብቻ ነው። ሰው የገደለ እኮ አዩኝ አላዩኝ ብሎ ራሱን ለመሸሸግ መታገል አለበት።እንዴት ሰው ገድሎ ታማኝነቱን ማስመስከር እንደ ዝና ተቆጥሮ ይሳለቁብናል? ቤተመንግሥታችንስ እንዴት የነብሰ ገዳዮች መናኻሪያ ይሆናል?እየገደሉን መጥተው እንዴት እየገደሉን እንዲኖሩ እድሉን እንሰጣቸዋለን? ስማቸው ተቆጥሮ የማያልቅ ወንዝ የማያሻግሩ የተቃዋሚ ድርጅቶች ወይም ከአውሮፓና አሜሪካ ሄዶ ኢትዮጵያውያንን ከህወሃት የአፓርታይድ አገዛዝ ነፃ ሊያወጣ የሚችል እንደሌለ እንቅጩን እንነጋገር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በወጣት ኢትዮጵያውያን የሚመራው ሰማያዊ ፓርቲና አሁን ከእንቅልፉ የባነነው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን እንደ አንድ ግኝት እንደ አንድ ርምጃ እንውሰድና ትግሉን አጋግሎ መቀጠል ያለበት ሲሆን ከዚያ ባሻገር ያለው ግን መድሕሃኒቱ ያለው ከየሁላችን እጅ ነው ። እምብኝ አልገዛም ማለት ፤ ፍርሃትን ማስወገድ ፤ ራስን ነፃ ለማውጣት መታገል ፤መደራጀት ፤ አንድነት መፍጠር የህወሃትን ሰርጎ ገቦችና ሰላዮችን ማዋከብና ማጋለጥ ፤የሚሠሩት ጸረ-ሕዝብ ተግባር ህወሃት በአማራ እናትና እህቶቻችን ላይ የሚያመክንና የአማራውን ሕዝብ ቁጥር ዝቅ እያደረጉ ከሁሉም አካባቢ እያፈናቀሉ እየገደሉ ዘሩን ለማጥፋት የሚያደርጉትን ድርጊት በቀጣይነት ማጋለጥ በርን ከፍቶ አለማስገባት…ወዘተ እንጅ እንደ ብሉይ ኪዳን ቀኙን ሲመታህ ግራውንም ስጠው ወይም በየተራ እንደ ዓመት በዓል በግ እየተጎተቱ መታረድና በየከርሸሌው እየገቡ በፈላና በቀዝቃዛ ውሃ መቀቀል በሌባ ጎማ ተዘቅዝቆ መገረፍ፤ በኤሌክትሪክ ሽቦ መጠበስ ፤በሴትና በወንድ ብልት ወስጥ አሰቃቂ ተግባር በመፈጸም የገደሉትን ሰው ዘቅዝቆ ማንጠልጠልን በመኪና መጎተት በደርግ ጊዜ ከነበረው በሚበልጥ ሁኔታ መዋረድ እንዴት እንዲቀጥል እድሉን እንሰጣቸዋለን? እኛም ቤት እሳት አለ መባል አለበት። ነፍጥ ወይም ጠመንጃ አንግቶ የሚንቀሳቀስ ኃይል ካለም የህወሃትን የመከላከያ ሠራዊት በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ማዋከብና ቢያንስ ወደ ሕዝብ ያዞረውን መሣሪያ እንዲያነሳ ማድረግ፤ በህወሃት ፖሊስ ፤ ደህንነትና የመከላከያ ሠራዊት፤በካድሬው ላይ የመበተን ወይም በውስጡ ያለው ቅራኔ እንዲባባስ የፕሮፓጋንዳ ሥራ አዘውትሮ መሰራት አለበት ወደዚህ ለመግባት የሚያስችሉ ብዙ ክፍተቶች አሉ በፖሊስና በመከላከያ በደህንነት ውስጥ ከላይ እስከ ታች ያለው መዋቅር የተያዘው ከአንድ ጎሳ በመጡ ስለሆነ ሌላውን ለማነሳሳት ለም ሆኖ ያለ ነጥብ ነው። በግንባሩ በውስጡ የተፈጠረውን የእኔ እቀደም እኔ ሽኩቻም እንዲባባስ መገፋፋት ይገባል በተጨባጭ ያየነው የግንባሩ አባላት ባኮረፉ ቁጥር እንዳያፈነግጡ ተሰርቶ የማያውቅና ራሱ ባወጣው ሕግ ላይ እንኳን ያልሰፈረ 3 ጠቅላይ ሚንስቴር ወዘተ…የፖለቲካ ሥልጣን ከችሎታና ከአቅም ብቃት የተመዘነ ሳይሆን ላለመቀያየም የሚደረገው ጥረት ውስጡ ምን ያህል የነኮረና የበሰበሰ እንደሆነ ስለሚያሳይ ይህን መጠቀም ያሻል። በግብር የሚሰበሰበው ገንዘብ ገቢ እንዳይሆን ማድረግ ፤ ከውጭ የሚገኘውን እርዳታ እንዳይሰጥ ማድረግ በማንኛውም አይነት መንገድ የሚገኘው ገቢ ለአገር እድገትና ልማት ሳይሆን የሚውለው የህዳጣኖችን ከርስ መሙያና ፍላጎት ማስተናገጃ እንጅ ለሕዝብ ብሶትና ችግር ስለማይውል ይህን በጡንቻው የሚያምን ኃይል ለማሽመድመድ ኢኮኖሚያዊ አቅሙን እንዲወርድ ማድረግ ማዳከም ገበሬው ፤ነጋዴው ፤ ሌላው ግብር ከፋይ አልከፍልም እንዲል ማድረግ ያስፈልጋል። ተተኪ ትውልድ እንዳይኖር የተስማሙ ጭፍኖችን በማሳከም በሕብረት ለአንዲት ኢትዮጵያና ለአንድ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሁሉም አይነት ዘርፎች መስዕዋትነት መክፈል ይገባናል። ኢትዮጵያ ተተኪ ትውልድ እንዳይኖራት የማድረጉ ዓላማ የማን እንደሆነ አስፈፃሚው ማን እንደሆነ እንተዋወቃለን። ዛሬ ኢትዮጵያዊ መሆንን የጠሉና ኢትዮጵያ የገጠማትን ችግር ላለመጋፈጥ ታሪክን ሸምጥጠው የካዱ ሁሉ ፈጥነው ችግራቸውን ቢያስተካክሉ ይበጃቸዋል። አዎ ኢትዮጵያ አሁን ከራስዋ በበቀሉ የአገር ውስጥ ጣሊያኖችና ከውጭ እንግሊዝና ጣሊያን አጥልተውብን በሄዱት የመከፋፈልና የእርስ በርስ አለመተማመን ምክንያት ችግር ገጥሟታል ።ነገር ግን በቅርቡ ኢትዮጵያ የኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያ ትሆናለች። ያኔ ታዲያ እነዚህ የእናት ጡት ነካሾችና የበሉበትን መሶብ የደፉ የአገር ውስጥ ጣሊያኖች ጀንበር ትጠልቅባቸዋለች፤አንገታቸውን እንዲደፉ የግድ ይሆንባቸዋል።ለሆዱ ያደረው የሚበዛ ቢሆንም እውነቱ የት ላይ እንዳለ መርምረው ያወቁ ወይም የሚያውቁ በዚህ ሥርዓት ውስጥ ስለሚገኙ ምርቱን ከገለባው የመለየት እንቅስቃሴም ሊሰራ ይገባል።የራስን ደጋፊ ኃይል በየተቋሙ መፍጠር ካልተቻለ መሣሪያ አምላኪ የሆነው ቡድን የውስጡን ቅራኔ ጋብ በማድረግ ነገሮችን በመለጠጥ የተለከፈበትን ወረርሽኝ ወደ ሌላው እያላከከ እድሜ ለመግዛት ስለሚችል የዚህ ዓይነቱን እድል አለመስጠትና በሩን መዝጋት አስፈላጊ ነው ብቻ ሳይሆን በጣም ጠቃሚ ነው። ሥርዓቱ መበስበሱን ለማየት ሩቅ መሄድ አያስፈልግም የአማራው ነገደ ብሔር ዘሩ እንዳይራባና ቁጥሩ እንዲቀንስ የተደረገው ፀረ-ሕዝብ ተግባር ቀላል አይደለም ነገር ግን ምሥጢሩን ደብቆ ለመያዝ አለመቻል ዋና ምልክት ነው። አሁንም ይህን ትኩረት ሰጥቶ ቢቀሰቀስበትና ለዓለም ሕብረተሰብ እንዲደርስ ቢደረግ አንዳንድ ጤናማ የሆኑ አገሮች ድጋፋቸውንና ግንኙነታቸውን ስለሚያቋርጡ ሥርዓቱ ብጥስጥሱ የሚወጣበት ጊዜ እየፈጠነ እንዲሄድ ያደርጋል። የታሰሩ ጋዜጠኞች የፖለቲካ ድርጅት አባላት እነአንዱ ዓለም አራጌ (የሕሊና እስረኞች) የታሰሩበትን መርምሮና ግልጽ አድርጎ ማቅረብ አንዱ የማጋለጥ ሥራ ተሰራ ማለት ነው። ክቡር አምባሳደር እምሩ ዘለቀ እንደጻፉት ሳይቦዝኑና ሳይሰላቹ በተቻለው መንገድ ሁሉ ሥርዓቱን ማዋከብ ያስፈልጋል።
(Adolf Hitler German-Rodolfo Graziani Italy– Joseph Stalin Soviet Union -Omar Hassan al-basher Sudan–Mengistu Haile Mariam- and Meles Zenawi in Ethiopia)
ራዶልፍ ሂትለር በጀርመን አገር የሚኖሩ ይሁዳዎችን ጨረሰ ፤ አዶልፎ ግራዚያኒ አውሮፓን አቋርጦ ባሕር ተሻግሮ በአፍሪካ ምድር የቅኝ ተገዥ አገሮችን ለማስፋፋትና ሀብታቸውን ለመዝረፍ ወደ ኢትዮጵያ አቅንቶ ሕዝባችን ጨረሰ ፤ጆሴፍ ስታሊን የብላድ ሚር ኢሊችን ሥልጣን ከተረከበ በኋላ እንደ ሬድ ተረርና የስታሊን ዱላ በሚል የራሱን ሕዝብ ጨፈጨፈ ፤ የሱዳኑ ኦማር ሀሰን አልበሽር ከዐረብ ጋር ያልተዳቀሉትን የደቡብ ሱዳንን ሕዝብ ፈጀ ፤ ዝሃና ግራውን መለየት የተሳነው መንግሥቱ ኃይለማሪያም በቀይ ሽብር ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር እያለ ተኪ የማይገኝለትን ወጣት ምሁር ሠራተኛ ፤ አርሶ አደር ፤ የከተማ ነዋሪ ፤ ነጋዴ አዛውንት ጨረሰ የኤርትራን ተቃዋሚዎች በኃይል ለማንበርከክ ሞክሮ የመገንጠል እድል እንዲታደሉ አደረገ ። ሌላው የአገር ጉድና አረም የምዕራባውያንና የዐረቦች አሽከር አያት ቅድመ አያቶቹ የጣሊያን አባሽ አጎንባሽ ሹምባሽና ለባሽ የነበሩት ልጅ በነ-ስብሃት ነጋና አባይ ፀሐየ አጆሃ! እየተባለ የሻእቢያን የመገንጠል ዓላማ ነዳጅ ሆኖ አገለገለ ኢትዮጵያን ወደብ የሌላት አገር አደረገ ፤ አብዛኛውን ከውጭ አገር የሚያዋስነውን የአገሪቱን ለም መሬት ለባዕዳን በረከት ሰጠ ፤ ሊበርድ የማይችል የጎሳና የሃይማኖት ግጭትና ጦስ አቀጣጥሎ በአበበ ገላው (አንድ ጋዜጠኛ ወቀሳ) ምክንያት በ30 ሰከንድ ውስጥ በድንጋጤ ርዶ ያለቀኑ የተቆረጠ ቅጠል መስሎ እኛን ረመጥ ውስጥ ከቶ ከማይጠየቅበት ዓለም ተጓዘ ያ ሚፈራውን ሞት ሞተ። መለስ ዜናዊና ድርጅቱ ህወሃት ነፍጥ ያነሱት የትግራይ ሕዝብ በሁሉም አይነት መንገድ ተበደለ ብለው እንደሆነ አድርገን የምንረዳ ልንኖር እንችላለን። የዛሬውን አላውቅም እንጅ ህወሃት የትግራይ ወላጆችን ጨርሷል።የተረፉትን ጧሪ አልባ አስቀርቷል፤ተኪ የማይገኝለት ወጣት ትውልድ በልቶ ያደገ ድርጅት ነው።በርግጥ በሥርዓቱ ዙሪያ ያሉት ሚሊየነር ሆነዋልከሚገባው ብላይ ከበርዋል ። የትግራይ ሕዝብ ግን በሳውዝ አፍሪካ እንግሊዞች ካራመዱት የአፓርታይድ አገዛዝ ሊመሳሰል የሚችል ሲኦል ውስጥ ገብቶ ነው የሚገኘው።በቅርቡ አንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ የሚሊዮኖችን ድምጽ ለማሰባሰብ በጀመረው ዘመቻ መቀሌ ላይ በክልሉ ገዥዎች የተደረገውን ሰምተናል።ትግራይ ውስጥ ወይን ከሚለው የህወሃት ጋዜጣና ከህወሃት ራዲዮ አልፎ ዜና ማድመጥና ማንበብ ወይም በሌላ አነጋገር ሌሎችን ጋዜጦችና መጽሔቶች አይገቡም የመገናኛ ብዙሃንን መስማት የሚያስቀጣ እንደሆነ ይታወቃል።የትግራይ ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን ይህን እሥራት ሰብሮ መውጣትና መብቱን ማስከበር ይገባዋል።
በመጨረሻም በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነው በኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን አገልግሎት አስተዳደር ክፍል አዘጋጅነት በ18/08/2013 ዋሽንግተን አርሊንግተን የሚካሄደው የታዋቂ ግለሰቦች ፤ የፖለቲካ አክቲቪስቶች ፤ የሃይማኖት መሪዎችና የተቃዋሚ ድርጅቶች ፤ የስቪክ ማህበራትና ሌላውንም ያካተተው ስብሰባ ለኢትዮጵያ ህዝብ ትልቅ የምሥራች ይዞ ብቅ እንደሚል ተስፋ አደርጋለሁ። ለሁሉም ግን የማሳስበው ቢኖር ሰጥቶ መቀበል ፤ መናበብ ፤ መደማመጥ ፤ መከባበርና ፍቅርን መተሳሰብን የሚያጎናጽፍ እንዲሆን መልካም አርአያ ሆናችሁ እንድትገኙ ነው።
ኢትዮጵያ በክብር ለዘልዓለም ትኑር!!!
ዋስትናችን እርቅ ብቻ ነው!
“እኛ የእሳት አደጋ ብርጌድ የለንምና ዋ!!” ኦባንግ
በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
እሳት ሲነሳ የመጀመሪያው ተግባር እሳቱን በፍጥነት ማጥፋት ለሚችለው የእሳት አደጋ ብርጌድ መደወል ሲሆን፣ ቀጣዩ ተግባር እሳቱ በተነሳበት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎች ነፍስ አትርፈው እሳቱን በተገኘው መንገድ ለማጥፋት መረባረብ ነው። ይህ የተለመደው ተግባር ዛሬ በኢትዮጵያ ስለመስራቱ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ /አኢጋን/ ዋና ዳይሬክትር ስጋት አላቸው። እናም “እኛ የእሳት አደጋ ብርጌድ የለንምና ዋ!!” የሚል ማስጠንቀቂያ አዘል ጥሪ ያሰማሉ።
“አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ እሳቱ ፊትና መልክ ይዞ ሲቀጣጠል አላነውም እንጂ በርካታ የማቀጣጠያ ቅመሞች ተዘጋጅተውለት ለመንደድ በዝግጅት ላይ ነው። መንደዱ የማይቀረው ይህ እሳት ቢነሳ የሚያጠፋው የለም” የሚሉት አቶ ኦባንግ ሜቶ፣ ጥላቻው በሰፈር ደረጃ ከርሯል ይላሉ። በየመንደሩ ህዝብ እንዲቧደን ተደርጓል። ሚና ለይቷል። አገር የሚመራው መንግሥትም ችግሩን ከመፍታትና አገሪቱን ከስጋት ከማላቀቅ “ጥሪ አይቀበልም” በሚል የሃይል ርምጃ መምረጡ ነገሮችን ይበልጥ እንዳወሳሰበ ይናገራሉ።
በየአቅጣጫው ያሉ ወገኖች ቆም ብለው ሊደበቁት ከማይችሉት ከህሊናቸው ጋር ሊነጋገሩ እንደሚገባ ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “ግብጾች ግብጾችን ገደሉ፣ ገና ቀውሱ ይቀጥላል። ይህ እጅግ ዘግናኝ የሆነው ቀውስ እኛ ዘንድ ሳይደርስ ወደ እርቅ እናምራ። ለእውነተኛ እርቅ ጊዜው አሁን ነው” በማለት አንገብጋቢ ያሉትን ጥሪ ያስተላልፋሉ።
“ላለፉት 22 ዓመታት ኢትዮጵያ ላይ ከየአቅጣጫው የተረጨው መርዛማ ፖለቲካና፣ ሰብአዊነት የጎደለው አስተዳደራዊ መዋቅር የፈጠረው ውጥረት ወደ መፈረካከስ እየነዳን ነው” በማለት የስጋቱን መጠን የሚጠቁሙት አቶ ኦባንግ ፣ በግብጽ የተፈጠረው ቀውስ በሃይል ሊቆም የማይችልበት ደረጃ ሲደርስ ምዕራባዊያንም ሆኑ አሜሪካ የሃዘን መግለጫ ከማውጣት የዘለለ ስራ አለመስራታቸው ለኢትዮጵያዊያን ታላቅ ትምህርት ሊሆን እንደሚገባ ያሰምሩበታል።
በሩዋንዳ ለቁጥር የሚያዳግቱ ሰዎች አልቀዋል። በኮሶቮ ህዝብ ተጨፍጭፏል። ዳርፉር ንጹሃን የጥይት ራት ሆነዋል። ይህ ሁሉ ከመሆኑ በፊት ሃያላን መንግስታትና “ድርጅቶቻቸው” በእነዚህ አገራት ውስጥ ነበሩ። እያወቁት ነው የሆነው። ግን ጉዳዩ የጥቅም ችግር ስለማይፈጥርባቸው አገራቱ በደም ጎርፍ ሲታጠቡ በዝምታ ተመልክተው እንደነበር ያስታወሱት አቶ ኦባንግ፣ “ሶሪያ ስትፈርስ፣ ከ100 ሺህ ሰው በላይ ሲያልቅና አሁንም እያለቀ ባለበት ሁኔታ እልቂቱን ማስቆም እየቻሉ ዝምታን መርጠዋል” በማለት አቶ ኦባንግ ከነዚህ አገሮች፣ በተለይም “አሁን ግብጽ ላይ በተፈጠረው ችግር ካልደነገጥንና ለሚቀርበው የእርቅ ጥያቄ መልስ ለመስጠት የማንዘጋጅ ከሆነ አደጋው የከፋ ሊሆን ይችላል” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ጥያቄው የስልጣን ሳይሆን አገሪቱ ላይ ያንዣበበውን የሞት አደጋ የመግፈፍ አንደሆነ፣ ይህ አሁን ያንዣበበው የቀውስ ደመና ባስቸኳይ ካልተገፈፈ መከራው የሁሉም ወገን እንደሚሆን ጥርጥር እንደማያሻው የጠቆሙት አቶ ኦባንግ “ንጹህ ልብናና ንጹህ ህሊና ያላችሁ ውጡ፣ ለእውነተኛ እርቅ እንስራ፣ አገሪቱንም እናድን፣ የእሳት አደጋ ብርጌድ የለንምና እኛው አገራችንን በማስቀደም እንታደጋት” ሲሉ ከወትሮው በተለየ ጥሪ አስተላልፈዋል።
በምርጫ ፕሬዚዳንት ሆነው በዓመጽ መፈንቅለ መንግሥት የተደረገባቸው ፕሬዚዳንት ሙርሲን የሚደግፉ የሙስሊም ወንድማማች ፓርቲ ደጋፊዎች ላይ የሃይል ርምጃ ከመወሰዱ በፊት በግብጽ ይህ ችግር ሊደርስ እንደሚችል የወተወቱ ነበሩ። ፕሬዚዳንት ሙርሲ ከስልጣን የተወገዱበት አግባብ ቀውስ ሊያስነሳ እንደሚችል ቢነገርም ሰሚ ባለማግኘቱ ቀውሱ ግብጻዊያንን እርስ በርስ አጋደለ። ግብጾች ግብጾችን ጨፈጨፉ። እስከ ሁለት ሺህ የሚደርሱ ሰዎች የተገደሉበት ይህ ቀውስ እንዴት ሊቆም እንደሚችል ፍንጭ የለም። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፣ የሰዓት እላፊ፣ ግድያና እስር ዓመጹን ሊገታው አልቻለም። ይልቁኑም መሳሪያ የታጠቁ ተቃዋሚዎች ግብጽን በጥይት እያመሷት ነው። እየገደሉም ነው።
በኢትዮጵያም በተለያዩ ወቅት የተነሱ የህዝብ ጥያቄዎችን በጸረ ሽብር ህግ፣ በእስር፣ በድብደባ፣ በግድያ፣ በማስፈራሪያና በጡንቻ የማስተናገዱ አዝማሚያ ከእለት እለት መጠናከሩ የሚከፋቸውን ሰዎችና ቡድኖች እያበራከተ ነው። የተፈናቀሉ ወገኖች ተበራክተዋል። በተፈናቀሉና መሬታቸው እየተቸበቸበ ያሉ ወገኖች ምሬት የከፋ ደረጃ ደርሷል። ሚዛናዊ ያልሆነው የአስተዳደር መዋቅርና የኢኮኖሚ ልዩነት የፈጠረው ቅሬታ በቃላት የሚገለጽ አልሆነም። እንደ አቶ ኦባንግ ሁሉ እርቅ አስፈላጊ እንደሆነ በማመን እየሰሩ እንደሆነ የሚናገሩትና ለጊዜው ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ ታዋቂ ምሁር ለጎልጉል እንደተናገሩት “በአሁኑ ወቅት ጥላቻው ከርሮ ህዝብ በገሃድ ስምና ብሔር እየለየ ፊት ለፊት መናገር ጀምሯል፤ የኑሮው ውድነት፣ የመብት ረገጣው፣ ዕንግልቱ፣ … የጥላቻውን መጠን አደባባይ ላይ እንዲታይ እያደረገው መጥቷል። አገራችን ያለችበት መንገድ አደጋ አለው። እርቅ የግድ ነው” ብለዋል፡፡
እኚህ ምሁር “ኢህአዴግ ውስጥ እርቅ አስፈላጊ እንደሆነ የሚያምኑና አሁን በየአቅጣጫው ያለው ችግር የሚያሳስባቸው ወገኖች ስላሉ እነዚህን ወገኖች በመቅረብ ለእውነተኛ እርቅ ለመስራት ጊዜው አሁን፣ ለዚያውም ሳይረፍድ በቶሎ ሊሆን ይገባል። ይህንን ካላደረግን ሁላችንም እናዝናለን። ይቆጨናል። በቀላሉ ልናልፈው ወደ ማንችልው ጣጣ ውስጥ ሳንገባ እንረባረብ” በማለት ተናግረዋል። አስተያየት ሰጪው በቅርቡ ራሳቸውን ገልጸው አስተያየት እንደሚሰጡ፣ ለጊዜው የተጀመሩ ስራዎችን በነጻነት ለመስራት ሲሉ ራሳቸውን ከመግለጽ የተቆጠቡበትን ምክንያት ተናግረዋል።
“አገር እንደ ሰው አካል ነው። አንድ ቦታ ሲታመም ስሜቱ የሙሉው አካሉ እንጂ የተጎዳው አንድ ክፍል ብቻ አይደለም” በማለት የማጠቃለያ አስተያየት የሰጡት አቶ ኦባንግ፣ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ሲቋቋም ዓላማው ሁሉም ነጻ የማውጣት ታላቅ ዓላማ አንግቦ በመሆኑ በዚህ ረገድ በቅርቡ የእርቅ ተግባሩን ሊከውን የሚያስችለውን እቅዱንና የድርጊት መርሃ ግብሩን ይፋ እንደሚያደርግ፣ ለዚሁም ተግባራዊነት ኮንፍራንስ እንደሚያዘጋጅ አመልክተዋል።
በነጻ አውጪ ስም መደራጀትና መታገል ሙሉውን አካል /አገር/ ሊያድን እንደማይችል ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “አሁን ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ አማራ፣ ጉራጌ፣ ወላይታ፣ ከንባታ፣ ሲዳማ፣ ከፊቾ … እያልን በተበጣጠሰ አመለካከት ከማነከስ የአገራችንን ህልውና በአንድ ትልቅ አጀንዳ ውስጥ በማካተት ለመስራት ድርጅታችን ለሚያቀርበው ጥሪ ህዝብና ጥሪ የሚደረግላቸው ወገኖች ሁሉ ቀና ምላሽ ሊሰጡ ይገባል” ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ሙስሊም፣ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ፣ ፕሮቴስታንት፣ ወዘተ በማለት ከብሄርና ጎሳው ልዩነት በተጨማሪ መለያየት መፈጠሩ የአገሪቱን እጣ ፈንታ አሳዛኝና አደጋ እንኳ ቢፈጠር ለተግሳጽ የሚፈራ ሰው እንዳይኖር ማድረጉ አሳሳቢ የሆነባቸው በርካታ ዜጎች አሉ። አቶ ኦባንግ እንደሚሉት ግን ሁሉም ቦታ የፖለቲካ ኮተት የሌለባቸው፣ ንጹህ ልብና ያላቸውና ህሊናቸውን የሚያከብሩ አሉ። እነዚህ ወገኖች ብቸኛ አማራጭ በሆነው እርቅ ላይ አበክረው መስራት እንደሚገባቸው አመልክተዋል። እሳቸው የሚመሩት አኢጋንም ለእንደዚህ አይነቶቹ ንጹሃን በሩ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል።
በመጨረሻም “አሁን ችግር በተባባሰባቸው ቦታዎች ሁሉ ‘እርቅ’ እንደ መፍትሄ የሚቀርበው፣ ዓለም አሁን ከመቻቻል ሌላ አማራጭ ስለሌላት ስለሆነ እኛም እርቅ ላይ ያለአንዳች ማቅማማት መስራት ይገባናል፤ ይህ ዕርቅ ግን በደፈናው ምህረት የሚያሰጥ ሳይሆን በፍትህ ላይ የተመሠረተ ነው” ያሉት አቶ ኦባንግ “ድርጅታችን እርቅ ላይ ያለው ሃሳብ ከሌሎች በተለየ የተቋቋምንበት፣ የሰፋና የተፈጠርንበት መሰረት በመሆኑ ይህንን ሃላፊነት በመውሰድ እስካሁን የሰራናቸውን ስራዎች ውጤት ለህዝብ ይፋ እናደርጋለን፤ ይህም እንደወቅቱ ሁኔታ ተለዋዋጭ ሳይሆን የጋራ ንቅናቄው ገና ከጅምሩ የወጠነውና እስካሁን ለዓመታት ሲሰራበት የቆየ ጉዳይ ነው። ኢህአዴግም ሰላም ስለሚያስፈልገው፣ ባለስልጣኖቹም መኖር ስለሚፈልጉ፣ ደጋፊዎቹም ዋስትና ስለሚያሻቸው የተቃዋሚ ወገኖችም አገራቸውን ስለሚያስቀድሙ፣ ሁሉም ወገኖች ቀና ምላሽ ይሰጣሉ ብለን እናምናለን” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።
በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
“አቶ እያሱ አለማየሁና አቶ ፍሰሐ በለጠ ኢሕአፓን አይወክሉም”–ከኢሕአፓ የእርምት እንቅስቃሴ
በዚህ ሐገራችን በምትገኝበት እጅግ አሳሳቢና ውስብስብ የታሪክ አጋጣሚ የኢሕአፓ አባላት ጥንካሬና ብቃት ወሳኝ ሆኖ ሳለ፣ አሁን ድርጅታችን በሁለቱ የአመራር አባላት እና ታማኞቻቸው ታፍኖ እየነጎደ ያለበት መስመር እጅግ የተሳሳተ መሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ከሆነ ቆይቷል። ከእለት እለት ራሳቸውን በእውቀት በማዳበር ፈንታ ግዜያቸውን በአልባሌ አሉባልታ የሚያሳልፉ፣ ስድብን እንደትግል የሚቆጥሩ፣ በጸያፍ ስነ ምግባር ትግሉን የሚያውኩ ግለሰቦችን እያሰባሰበ፣ ነባር እና በጸረ ወያኔው ትግል በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸውን አባላት የሚበትን ድርጅት እራሱን ለትግል ሳይሆን ለውድቀት ያዘጋጀ መሆኑም ግልጽ ነው።
ሙሉውን ጽሑፍ በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
የአቶ መለስ የሙት ዓመት ልዩ ዝግጅት (ESAT efeta 21 August 2013)
ሃይማኖትና ፖለቲካ በኢትዮጵያ –ከዶ /ር ብርሃኑ ነጋ
ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ
1. መግቢያ:
ካለፈው ሁለት አመት ግድም ጀምሮ “መንግሥት በዲናችን ጣልቃ አይግባብን” በሚል ሰፊ ማእቀፍ ውስጥ በሰላማዊ መንገድ በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እየተደረገ ያለው ትግል፤ በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ደግሞ ሁለት አስርት አመታትን ያስቆጠረ ከቀኖናው ውጭ መንግሥት የቤተክርስቲያኑን መሪ አይምረጥብን በሚል በመሰረታዊ ሀሳቡ ከሙስሊሙ ጥያቄ ጋር ተመሳሳይ በሆነ ጉዳይ በተነሳ ውዝግብ ቤተክርስቲያኒቱ ለሁለት ተከፍላ ያለችበት ሁኔታና በዚህም ምክንያት በመንግሥት የተገፋው “ስደተኛው ሲኖዶስ” በራሱ ላይ የደረሰውን ሁከት በመቃወም የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ተዳምረው ምናልባት ለመጀመሪያ ጊዜ ጤነኛ የሆነው የሀይማኖትና የፖለቲካ ግንኙነት ምንድን ነው? ወይንም ደግሞ የመንግሥትና የሀይማኖት ግንኙነት ምን መሆን አለበት? የሚለውን ጥያቄ ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው የሀይማኖቱ ተከታዮች አልፎ ያጠቃላይ የፖለቲካ ማህበረሰቡ (የሀገሩ) ትልቅ የመወያያ አርዕስት እየሆነ ነው:: ይህ ጉዳይ ግን ጥቅል ከሆነ ያመለካከትና የንድፈ ሀሳብ ጥያቄ በተጨማሪ ጥልቅና አስቸኳይ የሆነ የተግባር ፖለቲካ ጥያቄም ነው ይዞ የመጣው::
ሙሉውን ጽሑፍ በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
የሰማያዊ ፓርቲ ያላቻ ጋብቻ (ከይድነቃቸው ከበደ)
የሰማያዊ ፓርቲ ያላቻ ጋብቻ
መንግስት ተግባሩን ሣይወጣ ቀርቶ መንደርተኛና ቧልተኛ ሲሆን እንዴት ያሳፍራል ! ይህን ለመፃፍ ያነሣሣኝ አዲስ ዘመን ጋዜጣ “ የሰማያዊ ፓርቲ ጥቁር ተግባራት ” በሚል በገፅ 3 አጀንዳ ላይ እንዲሁም በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪን በተጨማሪ ዛሚ ሬዲዮ ጣቢያ የክብ ጠረጴዛ ውይይት እና በሬዲዮ ፋና በዜና እና በልዩ ዘገባ የሚተላለፉ ፕሮግራሞች፤በተለያዩ አካባቢዎች በሚካሄዱ ጥቃቅን አነስተኛ ስብሰባዎችና ሰልፎች የሚሰሙ መፈክሮች የመንግስትን ፍርሃቱን እና ውንጀላ በሚገባ የሚያሳዩ በመሆናቸው ነው፡፡
መንግስት ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ለጥያቄ አቅራቢዎች የሚያስርበት እና የሚያሰቃይበት አዋጅ ማውጣት ይቀለዋል፤ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም መነሻውን 4 ኪሎ የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት መድረሻውን ኢትዮ-ኩባ አደባባይ ያደረገ ታላቅ የተቃውሞ ሠልፍ ተደርጓል፡፡ በዕለቱም ለመንግስት የቀረበለት ጥያቄ የሰብዓዊ ጥሰቶች እንዲስተካከሉ፣የታሰሩ የፖለቲካና የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ፣በዓይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባት እንዲቆም በዚህም ምክንያት የታሰሩት እንዲፈቱ፣የኑሮ ውድነቱ ማሻሻያ እንዲደረግበት እና የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ የሚል ጥያቄዎች ናቸው፤እጅግ በሰለጠነ እና ሠላማዊ በሆነ መንገድ ጥያቄው ለመንግስት የቀረበ ሲሆን መንግስትም ለዚህ ምላሽ የሦስት ወር የጊዜ ገደብ ተሰጥቶታል፡፡
ይሁን እንጂ መንግስት ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ስም ማጥፋት ዘመቻውን ቀጥሎበታል፤መንግስት ስም ለማጥፋት ብሎ ያነሳቸው አንኳር ሀሳቦች መሰረታዊ የሰው ልጅ ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ናቸው፡፡ መንግስት ይህን ለመረዳት ተጨማሪ 22 ዓመታት ቢያስፈልገውም ህዝብ ግን ያጣውን ነፃነት ለማግኘት ትግሉን ይቀጥላል፤ ለህዝብ የመብት ጥያቄ የሆኑት መንግስት ለመወንጀል የሚያነሳቸው ሃሳቦች በጥቂቱ እንመልከት፡፡
1ኛ. “በ1997 ዓ.ም በቅንጅት ተሳትፎ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው ዛሬ ደግሞ በአዲስ ኮፍያ የሚንቀሳቀሱ” የተባለው ቁጥር አንድ ውንጀላ ነው፤ ምላሹ ደግሞ ፡- ይህ ሀሳብ ከእውነት የራቀ አይደለም ከዛሬ 8 ዓመት በፊት በሺዎች የሚቆጠሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ይቅሩና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ለነፃነት እና ለመብት ከፍተኛ አስተዋፅኦ የተደረገበት ወቅት ነው፤ በወቅቱ ለሚፈለገው ነፃነት ደም ተከፍሎበታል፡፡ አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ባዶ እጁን አደባባይ ወጥቶ “ድምፃችን ይከበር” በማለቱ አገርን ሊወር እንደመጣ ጠላት በመከላከያ ሠራዊት ለዛውም በሰለጠኑ ነፍሰ ገዳይ ታሪክ ሁሌም የሚዘክራቸው ኢትዮጵያውያን በግፍ ገሏል፤ በዚህም ምክንያትና በሌሎች የሚፈለገው ነፃነት ታጥቷል፡፡ እናም ያኔ ያጣነውን ነፃነትና መብት መንግስት በአዲስ ኮፍያ ቢለውም እጅግ በሠለጠነና ሠላማዊ በሆነ መንገድ በአዲስ እስትራቴጂ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በፈቀደው መልክ ተደራጅቶ ይህን አምባገነን ስርዓት ታግሎ ለማሸነፍ የሚያደርገው ጥረት ወንጀል የሚሆነው ምኑ ላይ ነው?
2ኛ. “በውጭ ከሚገኙ ፅንፈኛ አክራሪ ኃይል ጋር በመቀናጀት በአረቡ ዓለም የታየውን አብዮት ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት” ይህ ሁለተኛው ውንጀላ ነው፤ ሌባ አባት ልጁን አያምንም የሚባለው ተረት ለዚህ ውንጀላ ተስማሚ ይመስለኛል ምክንያቱም ያሁን መንግስት የበፊት አማፅያን (ወያኔዎች) ከሱዳን፣ ከሶሪያና ከግብጽ ከመሳሰሉት አገራት የጦር መሣሪያና ስልጠና እንዲሁም መሸሸጊያ በማግኘት አዲስ አበባ ቤተ መንግስት መግባታቸውን የሚታወቅ ነው፤ እነሱ በክደት የፈጸሙት ሁሉ ሌላው ያደርገዋል የሚል ከንቱ አሳብ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ የተመሠረተው በኢትዮጵያውያን ነው ትግሉም ሆነ ዉጤቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው፤ ሌላው ደግሞ በአረቡ አለም የታየው አብዮት ኢትዮጵያውያን ከ8 ዓመት በፊት በአስደናቂ ሁኔታ የተገበርነው ነው፡፡ ዛሬ ደግሞ ከ8 ዓመት በፊት ያጣነው አብዮት መንግስት አልሰማና አልለወጥ ካለ የአረቡን አብዮት በኛ አገር ተጨባጭ ሁኔታና ማህበራዊ ንቃተ ህሊና ሠላማዊ በሆነ መንገድ በመስቀል አደባባይ ወጥተን ብናደርገው ወንጀሉ ምኑ ላይ ነው?
3ኛ. “ከውጭ አሸባሪ ግንቦት ሰባት ቴሌቪዥን ጣቢያ ‘ኢሳት’ ጋር በመቀናጀት” ይሄ ደግሞ ሦስተኛ ውንጀላ ነው በመሠረቱ በአገር ቤት ያለው የዳኝነቱ ስርዓት እውነተኛ ፍትህ የሚሠጥ ቢሆን ኖሮ “መልካም ስምና ዝናን በማጉደፍ በተጨማሪም መረጃን የማግኘት መብት በመንፈግ” የወንጀል ክስ መመስረት ይቻል ነበር ግን ምን ዋጋ አለው?፡፡ ይህን ለማለት የፈለኩት አንደኛ ኢሳት መረጃን ለተጠሙ በዓለም ላይ የሚገኙ ኢትዮጲያውያን አይንና አንደበት የሆነ ሚዲያ እንጂ የግለሰብ ወይም በተወሰኑ ቡድኖች የሚንቀሳቀስ ሚዲያ አይደለም፡፡ እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ሚዲያው የእገሌ ድርጅት ነው መባሉ የስም ማጥፋት ወንጀል ነው፡፡ በሁለተኛ ደረጃ መረጃን ማግኘት ህገ መንግስታዊ መብት ነው፤ ይሁን እንጂ በአገራችን እኛ የመረጥነው ሳይሆን መንግስት የመረጠልን ሚዲያ ነው የምንመለከተው፣ የምንሰማውና የምናነበው ለዚህም ማሳያ በአገር ውስጥ ትክክለኛ መረጃ የሚያስተላልፉ ጋዜጠኞች መጨረሻቸው ስደት ወይም እስራት ነው፤ ከሀገር ውጭ ያሉ ሚዲያዎች ደግሞ ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ ይታፈናሉ በዚህ ምክንያት መረጃ የማግኘት መብታችን በኃይል ተከልክለናል፡፡
4ኛ. “የጥቂት ሙስሊም አክራሪዎች አጀንዳ በመደገፍ አደባባይ ይዞ መውጣት” አራተኛ ውንጀላ መሆኑ ነው፤ ጥቂት፣ አነስተኛ፣ ጥቃቅን የመንግስት አፍ መፍቻ ከሆኑ ሰነባብተዋል፤
“ጥቂቶች ቆራጦች ያልተንበረከክነው
ዛሬን እንሞታለን ነገ ታሪክ ምስክር ነው”
የሚለው የእናንተ የትግል መዝሙር አስታወሰኝ እባካችሁ ትላንትና ለጥቂቶች የነበራችሁ ከፍተኛ ግምት ዛሬ የት ገደል ገባ? የሙስሊም ወንድሞቻችን ትግል የጥቂቶች አይደለም የአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ሙስሊም የሀይማኖት ነፃነት ጥያቄ ነው፡፡ በመሆኑም ለአገር የቆመ ፓርቲ ለመብትና ለነፃነት በሰላማዊ መንገድ እታገላለሁ እያለ መብትና ነፃነታቸውን ለማስመለስ ደከመን ሰለቸን ሳይሉ “ድምፃችን ይሰማ” ለሚሉ እውነት ነው ድምፃቸው ይሰማ ብሎ ሰማያዊ ፓርቲ ድምፁን ቢያሰማ የሚያስወነጅለው ምክንያቱ ምንድን ነው?
5ኛ. “ሰማያዊ ፓርቲ ሠልፍ ላይ መካከለኛ እድሜ ላይ ያሉና አዛውንቶች ጭራሹንም በሰልፉ ላይ የሉም በአብዛኛው ለአክራሪዎች ወግኖ የቆመ ኃይል ነው” ይሄ በአምስተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ከውንጀላ ይልቅ በኢህአዴግ ቋንቋ የሠልፉን ገፅታ ጥላሸት ለመቀባት ነው፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ታላቅ የተቃውሞ ሠልፍ ሁሉንም የህብረተሠብ ክፍል ያካተተ እንደነበር የአለም ሚዲያ የዘገበው ነው፤በጣም የሚገርመው በ1997 ዓ.ም አደባባይ የወጣውን ወጣት “ አደገኛ ቦዘኔ ” በማለት ሠልፈኛውን እና የሠልፉን ዓላማ የተለየ ለማድረግ መንግስት ያልፈነቀለው ድንጋይ የለም፡፡ አሁን ደግሞ ከ8 ዓ.ም በኋላ በተካሔደው የተቃውሞ ሰልፍ ወጣቱ ብቻ ነው የተገኘው በማለት ለወጣቱ ያለውን ንቀት መንግስት በድጋሚ አረጋግጧል፡፡ እኔ የምለው! ወጣቱ ስለሀገሩ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳይ አያገባውም እንዴ? በተጨማሪም ተገፋን፣ ተበደልን ከሚሉ ሰዎች ጋር ወግኖ መቆም ጥፋቱ ምን ላይ ነው? በኢትዮጵያ ውስጥ በመንግስት ታስቦና ታቅዶ የሚፈፀም በደልና መገፋት በኔ አልደረሰም ተብሎ እንዴት ይታለፋል፤ ዛሬ ከተገፉትና ከተበደሉ ወገኖች ጋር ወግኖ ያልቆመ ነገ ለሱ ማን ሊቆምለት ነው?
በአጠቃላይ ከላይ የተገለፁት ሀሳቦች በመንግስትና ካድሬዎች እና ሚዲያዎች የሚነዙ አሉባልታ ወሬዎች መሆናቸውን ለማሳያት ለመንደርደሪያነት የቀረበ ፅሁፍ ነው፡፡ መንግስት ከሰሞኑ የተያያዘው ነገር ቢኖር ከስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍ ባለ ሁኔታ የሃይል እርምጃ መውሰድ ነው፤ለዚህም ማሳያ በተለያዩ ከተሞች በእስልምና እምነት ተከተዮች ላይ ግድያ እና ድብደባ እንደሁም እስራት እየተካሄደ ነው፤ ቀጣዩ ደግሞ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትና አመራሮች መሆናቸው የዘፈን ደርዳርታ እስክስታ ነው እንደሚባለው ከጠቅላይ ሚኒስተሩ ጀምሮ እስከታችኛው የስልጣን እርከን የተቃዋሚ ፓርቲ በተለይ ሰማያዊ ፓርቲን መንግስት የነገር አባት ( ሽማግሌ) በመሆን በቅርብ ከማያገኛቸው ነገር ግን እንዲህ አይነቱን ውንጀላ ለመፈረጅ ከሚመቻቸው ከግንቦት ሰባት እና ከሙስሊም አክራሪዎች ጋር ፓርቲውን እየዳሩት ይገኛል ፤ጋባቻው ግን ያላቻ ጋባቻ ነው፡፡
በመሆኑም መንግስት በተሠጠው ጊዜ አላፊነቱን በመወጣት እኛ ተበዳዮቹ ብቻ ሳንሆን እናተም በዳዮቹን በጋር በነፃነትና በእኩልነት የምንኖርበት አገር በማቅናት ሁሉ በህግ ፊት እኩል ሆኖ የሚዳኝበትን ጊዜ እናቅርበው፤ አለበለዚያ የምትፈሩት ህዝባዊ አብዮት መምጫው ቀን እሩቅ አይደለም፡፡
ይድነቃቸው ከበደ
የሰማያዊ ፓርቲ የህግ ጉዳይ ሃላፊ
ዋ! እዮብ መኮንን! –‹‹እግዚአብሔርን ባገኘው የምጠይቀው የዘላለም ሕይወት እንዲሰጠኝ ነው››
ጊዜው ከአምስት ዓመት በፊት ነው፤ በሚሊኒየሙ፣ ሚያዚያ ወር የመጀመሪያ ሳምንት፡፡ ሠራበት በነበረው ጐግል ጋዜጣ ‹‹ጥበብ›› አምድ ላይ እንግዳ ላደርገው ረፋድ ላይ ወደ እዮብ መኮንን የእጅ ስልክ መታሁ፡፡ መልካም ፈቃዱን ገለጾ… አንጃ ግራንጃ ሳያበዛ ‹‹ከተመቸህ ዛሬ መገናኘት እንችላለን›› አለኝ፡፡ ትንሽ መዘጋጀት እንዳለብኝ ነግሬው ዛሬ ከሆነ ምሽት ላይ መገናኘት እንደምንችል ነገርኩት፡፡ ጥያቄዎች ሳሰባስብ እና ሳሰላስል ዋልኩ፡፡ የቀጠሮ ቦታ ስላልቆረጥን ከመገናኘታችን በፊት ልደውልለት ተስማማን፡፡ ደወልኩለት!
‹‹ፒያሳ አካባቢ ነኝ፡፡ እዚህ መምጣት ትችላለህ?›› (እዮብ)
‹‹መልካም ግን ትንሽ እንዳልቆይብህ መገናኛ አካባቢ ነኝ፡፡ መሀል ላይ መገናኘት ከቻልን መልካም ነው፡፡ አለበለዚያ ግን ልምጣ››
‹‹እሺ! የት እንገናኝ? መኪና ይዘሀል?››
‹‹መኪና? ይሄ አራት ጎማ ያለው ነገር?››
‹‹ይስቃል››
‹‹አለኝ ግን butter fly ነው፡፡ (የልብስ ስፌት መሆኑን ልብ ይሏል፡፡) ከቤት ውጪ አልነዳውም››
እየሳቀ ‹‹እሺ! የት ልምጣልህ››
‹‹ዑራዔል አካባቢ አማካይ ስፍራ ነው፡፡ ፕላዛ ሆቴል እንገናኝ?›› እውነት ለመናገር እኔ የነበርኩት ፕላዛ አካባቢ ይገኝ የነበረው ቢሯችን ውስጥ ነበር፡፡ የጀመርኩትን ሥራ ሳጠናቅቅ፣ ኮምፒውተር ስዘጋጋ፣ እንዳልቆይበት ብዬ ግርጌዬ ላይ እንዲመጣ ጨከንኩበት፡፡ የሚገርመው እኔ ቢሮ ስድበሰበስ እሱ ቀድሞ ፕላዛ ደረሰ፡፡ ሮጥ ብዬ ስደርስ ሆቴሉ ግቢ ውስጥ ጥቁር ቪታራ መኪናውን እየዘጋጋ ነበር፡፡ ሆቴሉ ምግብ አዳራሽ ውስጥ ገበታ ሳይቆርሱ መስተናገድ ባይፈቀድም ቃለ ምልልስ ለመስራት ሳስፈቅድ ይሁንታ አገኘሁ፡፡ የሆቴሉ ባልደረቦች ድሬድ ጸጉሩን የተሸለተውን እዮብን እያዩ ‹‹እሱ ነው/አይደለም›› እየተባባሉ ነበር፡፡
አማርኛ፣ ትግሪኛ፣ ኦሮምኛና ሱማሊኛ ቋንቋዎችን አቀላጥፎ እንደሚናገር የነገረኝ እዮብ ቃለ ምልልሱን ከመጀመሬ በፊት ማስጠንቀቂያ አስቀመጠ፡፡
‹‹በድምጽ መቀዳት ስለማልፈልግ፣ ወረቀት እና እስክሪብቶ አውጣ››
‹‹ለምን››
‹‹ከዚህ በፊት ያላልኩትን ብለው መጽሔት ላይ ስላወጡ ይሄን ስህተት መድገም አልፈልግም፡፡ ስለዚህ እየጠየቅከኝ መልሱን ጻፍ!››
‹‹እኔ እንዲህ እንደማላደርግ ከመቶ ፐርሰንት በላይ ቃል ልገባልህ እችላለሁ››
‹‹ኖ! አይሆንም››
ላሳምነው ሞከርኩ፡፡ ሊዋጥለት አልቻለም፡፡ በዚያው ሰሞን አንድ መጽሔት ያልዘፈነውን ራጋ ‹‹የራጋ ስልት ያለው እንትን የተሰኘ ዘፈኑ›› እያለ አልበሙን ጥንብ ርኩሱን አውጥት ስለነበር ፕሬሱ ላይ ያለው እምነት የበለጠ እንዲሸረሸር አድርጎታል፡፡ የመጨረሻ አማራጭ ልሰጠው ጉሮሮዬን ጠረግኩ፡፡
‹‹እውነት ለመናገር መልስህን በቃል እየጻፍኩ አልዘልቀውም፡፡ በዚህ ላይ እኔ እስክፅፍ ስትጠብቅ ሃሳብህ ይቆራረጣል፡፡ ለዛ ቢስ ቃለ ምልልስ ይሆናል፡፡ ማድረግ ያለብኝ [ተገቢ ነው ብዬ ባላምንም] እስከዛሬም ለማንም አድርገነውም ባናውቅም ድምጽህን ወደ ወረቀት ከገለበጥኩ በኋላ (After transcription) አምጥቼ ላሳይህ እችላለሁ፡፡ አለበለዚያ ግን በቃል…››
አመነታ፡፡ እንደምንም አሳመንኩትና ‹‹ሽጉጤን›› ተረክ አደረግኳት [ለእንደ እኔ አይነት ጋዜጠኛ ተብዬ ሽጉጡ ድምጽ ማስቀሪያው ነች፡፡] አወራን፡፡ በቀጣዩ ቀን ምሽት ላይ ይሰራበት የነበረው ፋራናይት ክለብ (ልምምድ ላይ የነበረ ይመስለኛል) ወስጄ አሳየሁት፡፡ አነበበውና ምንም ሳያንገራግር በደስታ ሸኘኝ፡፡ ከዚያም የሚያዚያ 10/2000 ዓ.ም ጐግል ጋዜጣ ላይ ጨዋታውን ዳርኩት፡፡ ካወራናቸው ውስጥ ጥቂቱን እንካችሁ፡፡
የተለያዩ አይነት የሬጌ ስልቶች አሉ፡፡ አንተ የምትጫወተው የትኛውን አይነት ነው ትክክለኛ (Pure የሆነውን) ሬጌ ትጫወተዋለህ
ሬጌ የተለያየ አይነት ስታይል አለው፡፡ ሩትስ፣ ስካ፣ ዋን ድሮፕና ሌሎችም አሉ፡፡ የምቱ ሁኔታ ነው ሩት፣ ስካ… ሊያስብለው የሚችለው፡፡ እኔ ሁሉንም የሬጌ ቶን እጫወታለሁ፡፡ ስለ እኔ መናገር ቢከብደኝም ሙዚቃ የሚያውቁ ሰዎች በአብዛኛው በትክክል እንደምጫወተው ይናገራሉ፡፡
‹‹ይዞ የመጣው ለአገራችን አዲስ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊያሰልፈው የሚችል አዘፋፈን ነው፡፡ ሬጌ የሚፈልገው ነገር አለው፡፡›› ተብሎ ስለ አንተ የተጻፈ ጽሁፍ አንብቤያለሁ፡፡ በዚህ ትስማማለህ?
ጸሐፊው ያመነበትን ጽፏል፡፡ እኔ ከምናገር አድማጭ ቢፈርድ ጥሩ ነው፡፡
በሙዚቃ ስራህ ላይ ተጽዕኖ ያሳደረብህ ሰው አለ?
አሊ ቢራ እና ቦብ ማርሌይ በጣም የምወዳቸው ድምጻዊያን ናቸው፡፡ የእነሱ ተፅዕኖ አለብኝ፡፡ የሁለቱንም ዘፋኞች ዘፈን ከልጅነቴ ጀምሮ እሰማም፣ እዘፍንም ነበር፡፡
ሬጌ ሙዚቃ መጫወት ያለበት ሰው ምን ማሟላት አለበት?
መጀመሪያ ሙዚቃውን ማፍቀር አለበት፡፡ ከዚያም በደንብ መስማትና ደጋግሞ ልምምድ መሥራት ይኖርበታል፡፡
በአልበምህ ላይ የሰራሀቸው ዜማዎች ተመሳሳይነት አላቸው ይባላል፡፡
በፍጹም አይመሳሰሉም፡፡ ለአንድ የውጪ አገር ዜጋ የትግሪኛ ዜማ ብታሰማው ሁሉም አንድ ዓይነት ነው የሚመስለው፡፡ የእኔም እንደዚያው ነው፡፡ አሰማማችን ነው እንጂ ዜማዎቹ አይመሳሰሉም፡፡
አልበምህ ያሰብከውን ያህል ተደምጧል?
ገና ነው ብዬ ነው የማስበው፡፡ ሰውም በበቂ ሁኔታ የሰማው አይመስለኝም፡፡ የተወሰነ ሰው ግን ሰምቶታል፡፡
ለምሳሌ የሚካያ በኃይሉ አልበም ከወጣ ጀምሮ (1999 ዓ.ም.) የወደዱት ቢሆንም ይበልጥ የተሰማው እየቆየ ሲሄድ ነው፡፡ ያንተም አልበም እንደዚያ…
እመኛለሁ ግን እንደዚያ ይሆናል ብዬ አላስብም፡፡ አምላክ ነው የሚያውቀው፡፡
‹‹እዮብ በአብዛኛው የሚጫወተው የሬጌ ዘፈኖችን ስለሆነ ጸጉሩ መለያው ነበር፡፡ ሲቆረጠው ዘውዱን የተገፈፈ ንጉስ መስሏል ያሉኝ አሉ፡፡
ለእነሱ የሚታያቸው እንዳልከው ሊሆን ይችላል፡፡ እኔ ግን በመቆረጤ ደስተኛ ነኝ፡፡
መቼና ከማን ጋር ስትሆን ደስ ይልሀል?
ለብቻዬ፣ ከጓደኞቼ ጋር ስሆንና መጽሐፍ ቅዱስ ሳነብ ደስ ይለኛል፡፡ ሁሌም አዲስ ስለሆነ ባነበብኩት ቁጥር ይገርመኛል፡፡ ያነበብከውን መተግበር ስትጀምር ይበልጥ አዲስ ይሆንብሀል፡፡ ሌላ መጽሐፍ ማንበብ ትቼያለሁ፡፡
ትልቁ ራዕይህ ምንድን ነው?
አላውቀውም፡፡ ዛሬን ብቻ መኖሬን ነው የማውቀው፡፡ በፕሮግራም ነገ እንዲህ አደርጋለሁ አልልም፡፡ አስተማሪና መካሪ ዘፋኝ ብሆን ደስ ይለኛል፡፡ ስለ ነገ የሚያውቀው እግዚአብሔር ነው፡፡
አሁን የምትኖረው ሕይወት እና ያለህበት ደረጃ የምትፈልገውን ዓይነት ነው?
ኑሮዬ ይበቃኛል ማለት ትልቅ ነገር ነው፡፡ ደስተኛ ነኝ፡፡ ሕይወት ደግሞ የምትጣፍጠው አማራጭ ስታጣ ነው፡፡ በሕይወቴ ከዚህ በላይ ብሆንም ካለሁበትም ዝቅ ብልም ምንም አይመስለኝም፡፡ አማራጩ እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
በቆይታችንየእግዚአብሄርንስምደጋግመህአንስተሀል፡፡ብታገኘውበቀዳሚነትየምታነሳለትጥያቄምንድንነው?
የዘላለም ሕይወት እንዲሰጠኝ ነዋ!
በደረሰበት ደንገተኛ ህመም ቅዱስ ገብርዔል ሆስፒታል ሲታከም የነበረው ከዚያም ለተሻለ ሕክምና ወደ ናይሮቢ አቅንቶ ሳይነቃ በሳምንቱ መጨረሻ ሕይወቱ ያለፈው ተወዳጁ ድምጻዊ እዮብ መኮንን ጋ ያኔ በተገናኘንበት ወቅት አልበሙ እንዲህ ይገናል ብሎ አላሰበም፡፡ ‹‹ታያለህ እንደ ሚካያ አልበም ነው የሚሆነው›› ብዬ ‹‹ስጠነቁል›› አልመሰለውም ነበር፡፡ ሥራው ከገነነ በኋላ ‹‹አላልኩህም ነበር!›› ብዬ ከመፎከር አልቦዘንኩም፡፡ አንድ ቀን አጋጣሚ ቦሌ አካባቢ አግኝቼው አንድ ካፌ ትንሽ ተቀምጠን አወራን፡፡ አወራን ከማለት ይልቅ መጽሐፍ ቅዱስ ሲሰብከኝ ነበር ማለት ይቀላል፡፡ ልቡ ተሰብሮ፣ ግንኙነቱ ከአምላኩ ጋር ብቻ ይመስል ነበር፡፡ ዛሬ በ9 ሰዓት በሥላሴ በተፈጸመው የቀብር ስነ-ስርዓቱ ላይ ጥቅምት 12/1967 ዓ.ም. መወለዱ የተነገረው እዮብን ሁኔም በማይሰለቹ ዜማዎቹ እናስታውሰዋለን፡፡ በርካታ ሰውም በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በመገኘት ሀዘኑን ገልጿል፡፡ እንደተመኘውም በላይኛው ቤት ‹‹የዘላለም ሕይወት እንዲሰጠው›› እመኛለሁ፡፡ ዋ! እዮብ! ከልቤ አዝኛለሁ! ነፍሱን ይማረው!
መለስና ደሃ ዘመዶቹ
ክፍሉ ግርማ
ሰሞኑን የቀድሞውን የዲክታትር መለስ ዜናዊ የሞተበትን አንደኛ ዓመት በማስመልከት በየድረገጹ የተለያዩ የተቃውሞም የድጋፍም ጽሁፎች እየወጡ ነው ከሁሉ ግን አውራምባ ታይምስ በተሰኘው ድረገጽ ላይ አንድ ስለ መለስ ወንድምና እህት የሚገልጽ ፊልም አየሁ ነገሩ ሁሉ በጣም ገረመኝ ብዙ አስተያየቶችንም አነበብኩ ለእኔ ግን የማይውጥ ነው!! በጣም ስለድሃ ይሚያስብ ታላቅ መሪ…. ዘመዶችን እንኳን ለሃገሩ ሲል የረሳ መሪ…..ወ.ዘ.ተ እነዚህን የመሳሰሉ ውደሳዎችን የሚወዱት ኮሚኒስቶች ብቻ ናቸው
አንድ ሃይማኖት ያለው ወይም በትክክል የሚያስብ ሰው እንዴት ዘመዶችን ይረሳል በክርስትናም ሆነ በሙስሊሙ እምነት እናትና አባትን ከዚያም ወንድምና እህትን ማክበር መረዳዳትም እንዳለብን ያስተምራል.. አሁን እስቲ ይታያችሁ የመለስ እህት ጠላ መሸጥ ማለት መለስ ታላቅ መሪ ማለት ነው ? እዚህ አሜሪካን ሃገር በቀን 16 ሰዓት ከባድ ስራ እየሰሩ ወይም በአረብ አገር እህቶቻችን 24 ሰዓት በሰው ሰራተኛነት እይተቃጠሉ ወንድምና እህቶቻቸውን የሚስተምሩ ከቻሉም በብዙ ሺ የሚቆጠር ብር እየከፈሉ ከሃገር ወጥተው ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደርጉት ቤተሰባቸውን ለመቀየር አይደለምን? በሃገራችንም አንዱ ከቤተሰብ የተሻለ ቦታ ካለ ሌላውን መርዳትም የተለመደ ባህላችን ነው ወደ ቁም ነገሩ ለመለስና በእኔ እምነት መለስ እነዚህን ደሃ ወንድምና እህቱን አይውዳቸውም ወይም ያፍርባቸዋል ያልተማሩና ደሃ ስለሆኑም ይሆናል ወይም ሌላ ሚስጢር አለ እንጂ ለነዚህ ሚስኪን ሰዎች መለስ ትንሽ ቦታ አጥቶ አይደለም ለመሆኑ እነዚህ ወንድምና እህት ቤተመንግስት ለቅሶ ለመቀመጥ ተፈቅዶላቸው ይሆን በቀብር ስነ ስረአቱ ላይስ….ወ/ሮ አዜብስ ኤፈርት ካሰራቸው ብዙ ፋብሪካዎች በአንዱ ተቀጥረው ትንሽ ከጠላ ሻጪነት ብትገላግላቸው ጥሩ ነበር ኤፈርት የትግራይ ህዝብ ሀብት አይደለም እንዴ? ለመለስ እህት ያልሆነ ለማን ሊሆን ነው?
ከክፉ ውንድም ይጠብቅዎ
ፍልሙን ለማይት
አምስተኛው ባርነት –ከፋሲል የኔዓለም (ጋዜጠኛ)
በጥንቱ ስርዓት፣ አንድ ሰው ከአራቱ በአንዱ መንገድ ባሪያ ይሆናል። የመጀመሪያው በጦርነት ተሸንፎ ከተማረከ ፣ ሌላው እዳውን መክፈል አልችል ብሎ በእዳ ከተያዘ ፣ ሶስተኛው ከባሪያ ቤተሰብ የተወለደ ከሆነ በውርስ፣ አራተኛው ደግሞ ባሪያ ፈንጋዮች ይዘው ከሸጡት ነው። በዚህ ዘመን የባሪያ ንግድ ቢጠፋም፣ ባርነት ግን አልጠፋም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እንዲያውም አምስተኛውን የባርነት መንገድ እያየን ነው፤ ይሄ ባርነት በባህሪው እስከዛሬ ከታዩት ሁሉ የተለየና አስገራሚም ነው። እመለስበታለሁ።
ባሪያ ማለት፣ የጌታውን እጅ አይቶ የሚያድር፣ በራሱ ነጻነት የሌለው፣ ሰምቶ የመቀበል እንጅ ሰምቶ የመመለስ መብት የሌለው፣ በግዑዝና በነጻ-ሰው መካከል ያለ ፍጥረት ነው። ባርያ ሰውን ሰው የሚያደርገውን ነጻነት ሙሉ በሙሉ የተገፈፈ በመሆኑ፣ ከሰው ተርታ የሚመደበው ስለሚመገብ፣ ስለሚለብስ፣ መጠለያ ስላለው፣ ቋንቋ ስለሚጠቀም እና አውራጣት ስላለው ብቻ ነው፤ ከዚያ በተረፈ ግን የጭነት እንስሳ ማለት ነው። ባሪያ በእግዚአብሄር አምሳል በመፈጠሩ ክፉና ደጉን የመለየት ስልጣን ቢሰጠውም ፣ ስልጣኑን በጌታው በመነጠቁ ፣ ሁልጊዜ የጌታውን ደግ ነገር ብቻ እያየ እና እያመሰገነ የሚኖር ፍጥረት ነው።
በአሁኑ ጊዜ የሚታየው አምስተኛው የባርነት መንገድ 40 በ60 ከሚባለው የቤት ግንባታ ጋር የተያያዘ ነው፤ በዚህ የባርነት መንገድ ለመጓዝ የወሰነው ደግሞ ዲያስፖራው ( በውጭ የሚኖረው) ኢትዮጵያዊ ነው። መንግስት ለዲያስፖራው 40/በ60ን ሲያዘጋጅ ሁለት አላማዎችን ታሳቢ አድርጎ ነው- ዲያስፖራው ጥሮ ግሮ ያገኘውን ሀብት ሰብስቦ ደቋናውን ለመሙላት እና ዲያስፖራው ስለነጻነቱ እንዳይጠይቅ ወይም መንግስትን እንዳይቃወም አፍ ለማዘጋት።
40 /በ60 የተመዘገበ ዲያስፖራ እናት እና አባቱ፣ እህትና ወንድሙ፣ በአጠቃላይ የአገሩ ሰዎች ቢገደሉ፣ ቢታሰሩ ፣ ቢሰደዱ፣ ቢራቡ ፣ ቢጠሙ፣ ” ለምን?” ብሎ አደባባይ ወጥቶ የመጠየቅ እና የመቃወም ነጻነት አይኖረውም፤ ነጻነቱን በ40/በ60 ተገፎአል። ለሌላው መብት ሊሟገት ቀርቶ፣ በጥፊ ቢመታም እንኳን፣ “ጥፊው እንዴት ይጣፍጣል፣ እባክህ ግራ ጉንጨንም ድገምልኝ” ከማለት ውጭ፣ “ለምን ትመታኛለህ?’ ብሎ የአባትና እናቱን ወኔ ቀስቅሶ ብድሩን የመመለሻ ልብ አይኖረውም። እስክንድር ነጋ፣ አበበ በለው፣ ብርሀኑ ነጋ፣ እና ሌሎችም፣ ከስጋቸው ድሎት ነጻነታቸውን ያስቀደሙ በርካታ ኢትዮጵያውያን፣ ባርነት በቃን በማለታቸው፣ ጥረው ግረው ያፈሩትን ሀብት ተነጥቀዋል።
40/በ60 የተመዘገበ ዲያስፖራ ስለወገኑ ለመጮህ ከእንግዲህ በአውሮፓ እና በአሜሪካ ከተሞች እጅግም አይታይም፣ ለይሉንታ ቢታይ እንኳ ፊቱን በወረቀት ሸፍኖ ከሁዋላ ከመሰለፍ የዘለለ ሚና አይኖረውም። በነጻነት አገር እየኖሩ ገንዘብ ከፍሎ፣ በፍላጎት ባርነትን መምርጥ ማለት ይህ አይደለምን? የሚገዛ የለም እንጅ እነዚህ ሰዎች እኮ መንግስት ቢሸጣቸው እንኳ ምንም የሚናገሩ አይደሉም። ገንዘብ ተከፍሎ ባሪያ አድርጉን ብሎ የሚጠየቅበት አሰራር በታሪክ ታይቶ ይታወቃልን?
በአገር ቤት ያለው ህዝብ ለ 20/በ80 ቢመዘገብ አይገርመኝም፤ በባርነት ውስጥ የሚኖር ህዝብ በመሆኑ፣ አንድ ቀን ራሱን ነጻ እስኪያወጣ፣ ለጊዜው ተመችቶት ይኑር። ባሪያም እኮ ልብሱን ይቀይራል፣ የምኝታውን ሳር ተባይ ሲወርበት በሌላ ሳር ይተካዋል፤ ባበርነት ስር ያለው የአገር ቤት ሰው በነፍሱም በስጋውም ሊበደል አይገባውም፤ ቢያንስ እስከ ጊዜው በስጋው ይደሰት። ዲያስፖራው ግን የኢትዮጵያን ምድር ከለቀቀባት ጊዜ ጀምሮ ከባርነት ነጻ ወጥቷልና በነጻነት መኖር የሚችለበት እድል አለው፤ ለራሱ ብቻ ሳይሆን ለሌላውም ነጻነት ለመታገል ሁኔታው ተመቻችቶለታል፤ ይህን ነጻነቱን ግን እራሱ ገንዘብ ከፍሎ ሊሸጠው ይደራደራል። ፍርፋሪ እየተጣለለት ወደ ቄራ የሚወሰድ እሪያ መጨረሻው ሞት እንደሆነው ሁሉ፣ 40/በ60 የተመዘገበ ዲያስፖራም መጨረሻው ባርነት ነው። አምስተኛው ባርነት!
የሥላሴዎች እርግማን (ሦስት) ፦ አዳክሞ ማደህየት –ከፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ከፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ሐምሌ 2005
አንድ በጣም የተገረመ ደቡብ አፍሪካዊ ይህንን ሁሉ መንገድና ሕንጻ በአንድ ጊዜ ለማሠራት ገንዘቡን ከየት ነው የምታገኙት? ብሎ ጠየቀኝና ከወርቅ-ቡና አልሁት፤ ሳቅ አለና እኔኮ ከልቤ ነው የምጠይቅህ አለኝ፤ እንግዲያው ዘክዝኬ ልንገርህ አልሁት፤ ለወትሮው ብዙ የምክር ዋጋ የሚያስከፍል ቢሆንም ለመንግሥትህ እንዳትናገርና የዚሁ ዓይነት ሥራ በደቡብ አፍሪካ እንዳይጀመር ቃል ግባልኝ አልሁትና ቀጠልሁ፤ ከጥቂት ሳምንታት በፊት በመንግሥት ባንኮች ደጃፍ ላይ የነበረውን መጨናነቅ አይተሃል ወይ? ብዬ ጠይቄው ማየቱን ካረጋገጥሁ በኋላ ጉዳዩን እንደሚከተለው አስረዳሁት፡፡
አገዛዙ መሬቱንም ሆነ ቤቶችን የራሱ ካደረገና ባለቤትነቱን ካረጋገጠ በኋላ በየመንገዱ ዳር እንጀራ፣ ዳቦ፣ ቆሎ፣ ጠላና ትናንሽ ነገር እየሸጡ ልጆቻቸውን የሚያሳድጉ ሴቶች፣ በየቤቱ እየሠሩ በነዚህ ቤቶች ተዳብለው ኪራይ እየከፈሉ የሚኖሩ ሴቶች በብዛት ነበሩ፤ በነዚህ ደሀዎች ላይ ቀበሌዎች በየጊዜው እየዘመቱ ቤቱ እንደሚፈርስባቸው እያስፈራሩ ደሀዎችን ያሸብራሉ፤ በዚህ ዓይነት ፍርሃትና ስጋት ውስጥ ለጥቂት ወራት ካቆዩአቸው በኋላ ክረምትን ጠብቀው በግድ ያስለቅቁአቸዋል፤ በዚህ ምክንያት በአዲስ አበባ ውስጥ የተፈናቃይ ቁጥር በየዓመቱ እየጨመረ በአንዲት ትንሽ ክፍል ውስጥ የሚኖረው ሰው ቁጥር እየበዛ ለጤንነት ክፉ ጠንቅ እየሆነ ነው፤ ይህ ችግርና ስቃይ ትልቅ የሀብት ምንጭ ሆኖአል፤ ደሀ የሚበላው አንጂ የሚከፍለው አያጣም፤ ነጭ ደሀ ነጭ ማር ይከፍላል፤ እነዚህ ባህላዊ አነጋገሮች ተጠንተው በተግባር ላይ እየዋሉ ነው።
እንዴት? ማለት ጥሩ ነው፤ እነዚህ (ቤቶቻቸው ከማለት ይልቅ) መጠለያዎቻቸው የፈረሱባቸው ሰዎች ከረሀቡ ሌላ በብርድና በጸሐይ በመጉላላታቸው የመጠለያ ችግራቸው በጣም ከባድ ስለሆነ በቀላሉ የሚበዘበዙ ናቸው፤ ችግሩን መፍቻ የሚመስል የደሀውን ነፍስ በጉጉት ሰንገው የሚይዙበት ኮንዶሚንየም የሚባል ማቁለጭለጫም አለ፤ ደሀ ሁሉ ኮንዶ አግኝቶ የሚያልፍለት ይመስለዋል፤ ስለዚህ ሁሉም ይፈልጋል፤ ስለዚህ የኮንዶ ፈላጊው ሰልፍ በጣም ረጅም ነው፤ ስለዚህ በመስገብገብ እየተተኮሰ ዋጋው በጣም ከፍ ያለ ነው።
ማፍረስ ከመገንባት የቀለለ ቢሆንም በአዲስ አበባ የሚካሄደው አብዛኛው የመገንባት ሥራም ከማፍረሱ ሥራ የተሻለ መሆኑ በጣም ያጠራጥራል፤ እንዲያውም የማፍረሱንም ሆነ የመገንባቱን ሥራ የሚመሩት የውጭ አገር (ምናልባትም የቻይና) ሰዎች ናቸው ለማለት ያስደፍራል፤ በኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ነፍስ ውስጥ መሬት እንዳለ፣ በኢትዮጵያ የብዙ ሺህ ዓመታት ውስጥ መሬት እንዳለ፣ በኢትዮጵያ የተጋድሎ ጀግንነት ውስጥ መሬት እንዳለ፣ በኢትዮጵያ የአገር ፍቅር ውስጥ መሬት እንዳለ የውጩ አገር ሰው በምን መንገድ ሊያውቅ ይችላል? አንድ ኢትዮጵያዊ በአገሩ ውስጥ ባለው ቤት ውስጥ ምን ምን ይሠራል? አንዴት ይሠራል? በዚህ ጉዳይ ላይ የውጭ አገሩ ሰው ምንም ያህል አያውቅም፤
ስቱድዮ በወር አንድ መቶ ዘጠና አምስት ብር፣ ባለአንድ መኝታ ሁለት መቶ ሰባ አራት ብር፣ ባለሁለት መኝታ አምስት መቶ ብር እንደሚከፈል ተወስኖአል፤ ይህ ኪራይ ሁላችንም እንደምናውቀውና እንደለመድነው ዓይነት ያለ ኪራይ አይደለም፤ ልዩ ነው፤ አንዱ ልዩ የሚያደርገውም መጠለያዎቹን ሁሉ ያፈረሱትና ችግሩን የፈጠሩት ራሳቸው ኪራይ ሰብሳቢዎች መሆናቸው ነው፤ ዋናው ልዩ የሚያደርገው ግን ለኮንዶዎቹ ኪራይ መክፈል የሚጀመረው ሕንጻዎቹ ተሠርተውና አልቀው ተከራዮቹ ከገቡ በኋላ አይደለም፤ የሕንጻዎቹ ሥራ የሚጠናቀቀው ቢያነስ ከአምስት ዓመት በኋላ ሲሆን ኪራይ መክፈል የሚጀመረው ዛሬ ነው! ደሀዎች ለማይኖሩበት ቤት ኪራይ ይከፍላሉ! ማንም አላስገደዳቸውም፤ ያስገደዳቸው ደካማነታቸውና መናጢ ደሀነታቸው ነው፤ መስገብገባቸው ነው።
ከቀረበው መረጃ ተነሥተን እስቲ ትንሽ ስሌት እንሥራ፤ በአጠቃላይ በአዲስ አበባ ውስጥ ስምንት መቶ ሺህ ያህል ሰዎች ለኮንዶ ተመዝግበዋል እንበል፤ በስቱድዮ፣ በአንድ መኝታ፣ በሁለት መኝታ፣ በሦስት መኝታ በእያንዳንዳቸው የቤት ደረጃዎች ሁለት መቶ ሺህ ሰዎች ቢመዘገቡ ከነዚህ ውስጥ ግማሽ የሚሆኑት በዝቅተኛ የደሀነት ደረጃ ላይ ቢሆኑ፣ ሢሶ የሚሆኑት ደግሞ የደሀነት መሀከለኛ ደረጃ ላይ ቢሆኑ፣ ሌሎቹ ማለትም አንድ አምስተኛ የሚሆኑት በተሻለ ደረጃ ላይ ያሉ ደሀዎች ቢሆኑ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በያመቱ የሚሰበሰበው ገንዘብ እንደሚከተለው ይሆናል፤
ደሀነት ሲበዘበዝ
ኮንዶ | የተመዘገቡ | የወር ኪራይ በደሀነት ደረጃ | የዓመት ኪራይ |
ስቱድዮ |
200 000 |
200 000 x 195= 39 000 000 |
468 000 000 |
1 መኝታ |
200 000 |
200 000 x 274= 54 800 000 |
657 600 000 |
2 መኝታ |
200 000 |
200 000 x 500= 100 000 000 |
1 200 000 000 |
3 መኝታ |
200 000 |
200 000 x 750= 150 000 000 |
1 800 000 000 |
ድምር | 1 000 000 | 279 700 000 | 4 125 000 000 |
እንግዲህ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ከመጠለያ ማጣት ጭንቀት ለማምለጥና ያደረባቸውን የኮንዶ ጉጉት ለማሳካት ከአራት ቢልዮን ብር በላይ እየተራቡ ይገብራሉ፤ በአምስት ዓመታት ውስጥ ገና ኮንዶው ውስጥ ሳይገቡ ላባቸውን ያንጠፈጠፉበትን 20 625 000 000 ብር ይከፍላሉ ግፍ ሌላ ትርጉም የለውም።
ማፍረስም በጣም ትርፋማ ሥራ ሆነ።
በፈረሰው ላይ የሚገነባውስ? ስለኮንዶው ሕንጻ አንዳንድ ጥያቄዎችን ማንሣት በግድ ያስፈልጋል፤ አንደኛ የኮንዶው ሥራ መቼ ተጀምሮ መቼ ያልቃል? ያልቃል ሲባልስ ለመኖሪያ ብቁ የሆነ፣ በሮችና መስኮቶች ተገጥመውለት፣ ወለሉና ጣራው፣ የመታጠቢያ ቤቱ ሁሉ ተሟልቶ ነው ወይስ ባለቤት የሚሆኑት ሰዎች የሚጠብቃቸው ሥራ አለው? ሁለተኛ የኮንዶው ሕንጻ ስንት ክረምትና ስንት በጋ የሚችል ይሆናል? ሦስተኛ ኮንዶው ሰዎችን ወደከፍተኛው ፎቅ የሚያደርሳቸው ‹ሊፍት› አለ ወይስ ሰዎች በእግራቸው በደረጃ ሊወጡ ነው? ይህ ከሆነ ለሽማግሌዎችና አሮጊቶች ምን ዝግጅት ተደርጎላቸዋል? ሽማግሌዎችንና አሮጊቶችን ወደምድር ቤቱ አካባቢ ለመደልደል ታስቦአል ወይ? አራተኛ የውሀ አቅርቦቱ ምን ያህል አስተማማኝ ነው? ውሀ በሚጠፋበት ጊዜ ነዋሪዎቹ ሊጠቀሙበት የሚችሉበት የመጸዳጃ ቦታ ካልተዘጋጀ በጥቂት ጊዜ ውስጥ አካባቢው ለጤና ጠንቅ እንደሚሆን መገመት አያዳግትም፤ ‹‹የአበሻ ኑሮ›› የሚባል ነገር ያለ ይመስለኛል፤ ቡናና ጌሾ መውቀጡ፣ ብቅልና በርበሬ ማስጣቱ፣ ዶሮና በግ ማረዱ፣ አንጀራ መጋገሩ፣ ማኅበሩ፣ ለቅሶው — እነዚህና ሌሎችም ማኅበራዊ ግዴታዎች ኮንዶው ሲሠራ ታስበው ነበር ወይ?
ደሀው ራሱን በማፈራረስ፣ ይበልጡኑ በሚደኸይበት ሥራ እንዲጠመድ፣ በፍርስራሽ እንዲነግድ በምናምን ተይዞአል! የሥላሴዎች እርግማን!
የልማታዊ ጋዜጠኞች አንዝህላልነት እና የአብርሃ ደስታ እማኝነት “የኢትዮዽያውያን ህይወት በዓረብ ሀገሮች “
ባሳለፍነው ሳምንት በሳውዲ አረቢያ ግፍ ተፈጸሞባቸው ወደ ባገር ቤት የሚሸኙ እህቶች የመኖራቸው መረጃ ደረሰኝ ። በተለይም በቅርብ እከታተላቸው የነበሩ አህቶች እንግልት በመጠቆም በዚው በፊስ ቡክ የማለዳ ወግ ዳሰሳየ ላይ አንድ መልዕክት አስላልፊ ነበር! መልዕክቱም ለልማታዊ የሃገር ቤት ጋዜጠኞች ሲሆን የመልዕክቱ ፍሬ ሃሳብ ” የምንናገረውን ማመን መቀበል አቅቷችሁ እንደ ጠላት ከምታዩን ረቡዕ ወደ ቦሌ አየር ማረፊያ ሂዱና ከፍተኛ ግፍ ተፈጸደሞባቸው ከሳውዲ ተጠርፈው ወደ ባገር የሚገቡትን የኮንትራት ሰራተኞችን ተመልክቱ !”የሚል ነበር።
ንቁ እዝነ ልቦንና ያልታደሉት ልማታዊ ጋዜጠኞች በቦታው ሄደው ከቤሩት የተመለሱትን ሻንጣ የደረደሩ እህቶች በቴሌቪዥኑ መስኮት ብልጭ አድርገው ከማጥፋታቸው ባለፈ ከሳውዲ ያለጫማና የረባ ልብስ ተደብድበውና ተደፍረው የተመለሱትን ግፉአን ሊያሳዩን እንኳ አልፈቀዱም! ጋዜጠኞቻችን አልተሳሳቱም!!! የተሳሳትኩት እኔ ነኝ!!! ያን ሰሞን “ስደት ይቅር ” ምንቴስ ሰፊ ሽፋን በየሚዲያው እየሰጡ ፣ የደበቁትን መከራችን እያሳዩ እያሉ ህዝበ አዳም ፣ ሃገሬውን ሲያስለቅሱን የከረሙት ወደ ነፍሳቸው ተመልሰዋል ብየ በማሰቤ ስህተቱ የእኔ ግምት ነው!!! ጉዳታችን እዩት ቀሪው እንዲማርበት ፣ ሃላፊዎቻችን ይዩትና ወደ ዘነጉት የዜጎች ጉዳይ ያተኩሩ ዘንድ የተገፊ ግፉአኑን ጉዳይ ተከታትየ መጠቆሜ በአደባባይ ቃል የገቡትን ይፈጽማሉ ብየ በማሰቤ የተሳሳትኩት እኔ ነኝ!!! ስህተቴ አንድና አንድ ነው!!! የአረብ ሃገሩን የስደት መከራ የሚፈልጉት ለፕሮፖጋንዳ እንጅ ቀሪውን ማስተማርን እንደልሆነ አለማሰቤ ነው ስህተቴ ! በእንዝህላል ልማታዊ ጋዜጠኞቻችን አዝኘም ብቻ ሳይሆን አፍሬ ዝም ማለቴ ግን እውነት ነው! ዛሬ ማለዳ ግን መልካም መረጃም የሚየ ስፈነጥዝ ባይሆንም መረጃው በመሰራጨቱ የተደሰትኩበትን መጣጥፍ ተመለከትኩ ።
ሮብ ነሓሴ 15, 2005 ዓም ከአረብ ሃገር ወደ ሃገር የገቡትን እህቶች አብርሃ ደስታ አግኝቷ እንዳነጋገራቸው በማህበራዊ ድህረ ገጽ ካስተላለፈው መልዕክት ለመረዳት በመቻሌ ደስ አለኝ ! በገዥው የኢህአዴግ መንግስት አስተዳደር ላይ በተለይም ስለ ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ከመቀሌ ሆኖ በሚያሰራጫቸው የሰሉ ሚዛናዊ ሂሶች ተወዳጅነትን እያተረፈ የመጣው አብርሃ ድስታ ግፉአን እህቶቸችን ቦሌ አየር ማረፊያ አግኝቷቸው ያየውን የሰማውን እጥር ምጥን ባለው የለመድነው መረጃ አቀባበል እንካችሁ ብሎናል ። የአብርሃ እማኝነት አስደስቶኝ እኔም ለዛሬ ወግ ዳሰሳ አበቃሁት ! ወዳጃችን አብርሃ ደስታ ሆይ ! የአረብ ሃገሩ የብዙሃን የኮንትራት ሰራተኞች አስከፊ ህይዎት ያጫዎቱህ ወደ ሃገር ለመግባት የታደሉት መሆናቸውን አስረግጨ እነግርሃለሁ ! ያየሃቸው የታደሉት ጥቂት ምሳሌዎች ናቸው ! የመንግስት ተወካይ አለን ለማለት አልደፍርም ! እውነቱ ይህ ነው ! አንተም እንኳን ከግፉአኑ ሰምተህ አሰማህን ! ይህ የማናችንም ሃላፊነት መሆን ሲገባው እያደረግነው አይደለም! የእህቶቻችን ህይዎት በአረብ ሃገር ምስክርነቱ ይህ ነው ! እንዲህ ይኖራል ! የእኔን በዚህ ላብቃና እጥር ምጥን ወዳለችው የአብርሃ ደስታን እማኝነት ከዚህ በታች እንድትመለከቱ ስጋብዝ ለአብርሃ ምስጋና በማቅረብ ጭምር ነው! እነጰ አበቃሁ ! ቸረወ ያሰማን !
ነቢዩ ሲራከ
By Abraha Desta የኢትዮዽያውያን ህይወት በዓረብ ሀገሮች ——————————————— ሮብ ነሓሴ 15, 2005 ዓም ጠዋት ቦሌ ኤርፖርት ነበርኩ። ኢንተርናሽናል ተርሚናሉ ከዓረብ ሀገራት በተመለሱ እንስት ኢትዮዽያውያን ተጥለቅልቋል። የተከፉና የተረበሹ ይመስላሉ። ከሰዓት በኋላ ወደ መቐለ ለመመለስ ወደ ሀገር ውስጥ ተርሚናል ገባሁ። ከነዚህ ጠዋት ረጅም ሰልፍ ይዘው ያየኋቸው ተመላሾች የተወሰኑ አገኘሁ። ስለ ህይወታቸው፣ ስለሚደርስባቸው እንግልት ወዘተ አጫወቱኝ። በዓረብ ሀገሮች የሚኖሩ ኢትዮዽያውያን እንደሰው አይቆጠሩም፤ ብዙ አካላዊና ስነ አእምራዊ ችግር ይደርሳቸዋል። ብዙዎቹ አብደዋል፣ ራሳቸው አጥፍተዋል። ኢትዮዽያውያን በመሆናቸው ራሳቸው ይረግማሉ፤ በመፈጠራቸው ያዝናሉ። የኢትዮዽያ ኤምባሲ ግን ምንድነው የሚሰራው? የዜጎች ደህንነት መጠበቅ’ኮ የመንግስት ሐላፊነት ነው። የኢትዮዽያውያን ስደትና ግፍ ሀገራችን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ ሊመራት ይችላል።
የመለስ ዜናዊ “የሁለት አሐዝ ዕድገት” እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ኑሮ ***
ከበፍቃዱ ዘ ኃይሉ
“ለ7 ዓመታት በተከታታይ 11·6 በመቶ አድጓል” የተባለው የመለስ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ፥ የዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍም ከመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በሚገኘው መረጃ ላይ ቢመሠረቱም “የለም፤ ከ6 እስከ 8 በመቶ ነው ያደገው፣ ቢሆንም ቀሽት ነው” ይላሉ።
“ኢኮኖሚው ሲመነደግ” የሕዝቦች ኑሮ ደረጃስ እንዴት ነው?
ኢትዮጵያ በየአረብ አገራቱ የቤት ሠራተኛ አቅራቢነት ከፍተኛ ደረጃ የደረሰችው በመለስ ዘመን ነው። (ለምሳሌ አሁን ኢትዮጵያውያንን አልቀበልም ያለችውን ሳውዲ አረቢያ የቤት ሠራተኛ ፍላጎት 10 በመቶ ኢትዮጵያ ትሸፍን ነበር።) በየአረብ አገራቱ የኢትዮጵያውያን ስም ከሌብነት እና ሴተኛ አዳሪነትጋ የተያያዘ ነው።
ከኢትዮጵያ ውጪ መውጣት ለሁሉም ዜጋ ቢፈቀድ ዐሥር ሚሊዮን ሰው እንኳን ይቀራል ብዬ መገመት ይከብደኛል። ከተሜውም ገጠሬውም ወደቻለው ቦታ ይፈልሳል። የተማረውም፣ ያልተማረውም ኢኮኖሚያዊ ስደትን የመምረጡ እውነት የኢኮኖሚያዊ ዕድገቱን እውነተኝነት ጥያቄ ምልክት ውስጥ ይከተዋል።
የመሠረተ ልማት ግንባታዎች በተለይ የመንገድ ሥራዎች ሲነቃቁ የግሉ ዘርፍ (ከኢሕአዴግ “የኢንዶውመንት” ቢዝነሶች በቀር) ተዳክሟል። ያሉትም የግል ቢዝነሶች ቢሆኑ በፖለቲካ ጥቅም የሚለመልሙ በመሆናቸው በከተሞች መሐል የሚበቅሉ ብልጭልጭ ሕንፃዎች የሙስና ሲሳይ ናቸው። ከሕንፃዎቹ ጀርባ ያሉት ያው የድሮዎቹ ቆሼ ሰፈሮች ናቸው። እንደ HDI ያሉ የUN የሰብኣዊ ልማት መለኪያዎችም የሚያሳዩን ኢትዮጵያውያን ዛሬም በድህነት እየማቀቁ መሆኑን ነው።
“ስኳር የተወደደው ድሃው ስኳር መብላት ጀምሮ ነው” ያሉት መለስ ስኳሩን የሚልሱት እነማን እንደሆኑ እንኳ ሳይረዱ ያለፉ ይመስለኛል።
አቶ መለስ ምንጩንና መጠኑን ማንም ያልገመተው፣ የባለብዙ ሀብት ባለቤት፣ የትዳር አጋራቸውን ጨምሮ ሌሎች ጥቂት ሀብታሞች ያሉበት የጥቅመኞች ክበብ እየዳጎሰ ብዙኃኑ የሚቀጭጩበትን የቢዝነስ ስርዓት በመፍጠር በቁጥር ጫወታ አድጋችኋል ይሉናል። ድሃ ተኮር ፖሊሲ ቀርጫለሁ፣ ለልማቱ ብዬ ነው ዴሞክራሲን የበደልኩት ብለው ያተረፉልን ነገር ቢኖር አገርክን ጥለህ ብረር፣ ብረር የሚያሰኘው ምስኪን፣ ድሀ ትውልድ ብቻ ነው።
“በህግ አዋቂ ፣ በመብት አስጠባቂ ”ሹም መብት ሲጣስ እንዴት ያማል ?
ነቢዩ ሲራክ
ከሳውዲ አረቢያ
በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከፍተኛ ሃላፊዎችን የያዘ ቡድን በአንባሳደር ውብሸት ተመርቶ ሳውዲ መግባቱን ሰምቸ ነበር ። ከፍተኛ ሃላፊዎችን የያዘው ቡድን ሪያድና ጅዳ የኮንትራት ሰራተኞችን ይዞታ ለማየት እንደመጣ መስማቴ ደግሞ ጉዳዩን እግር በእግር እንድከታተለው ምክንያት ነበር። የጅዳው ጉብኝት ዛሬ ማለዳ ከመድረሱ በፊት የኮባንያ ስራየን በጊዜ ሸካክፊ ወደ ጅዳ ቆንስል አመራሁ … ! በቆንሰሉ መጠለያ ድርሸ ወደ ግቢው በር ስገባ እንግዶቹ ከቆንሰሉ በር ወደ መጠለያው ወደሚገኝበት በር ሲንቀሳቀሱ ደረስኩ። ቀድሜ መጥቸ ስለነበር ቀድሜ የግቢውን በር ተሻገርኩ ። ዘልቄ ልገባ ስል የጅዳው ቆንስል ተሶርፈውም ቢሆን እንደመሳቅ እያሉ ጨበጡኝ ። ጨበጥኳች ። ትከሻየን እየደባበሱ ወደ ውስጥ መግባት እንደማይፈቀድልኝ አስታወቁኝ ። ” ለምን ተከልከልኩ? ” ስል ጠየቅኳቸው ” እሱን ሌላ ጊዜ እንነጋገራለን አሉኝና እንግዶችን እየመሩ ወደ ተፈናቃዮች የሚደርጉትን ጉብኝት ለመከወን በጥድፈት ረምድ ረመድ ብለው ጥለውኝ ሄዱ … እንቅስቃሴውን በርቀት እየተከታተልኩ እያለ የኮሚኒቲው ግቢ የጥበቃ በትህትና ጠጋ ብሎ ሰላምታ ካቀረበልኝ በኋላ እንዲህ አለኝ ”
አቶ ነቢዩ ይቅርታ! ” ሰላምታ አቅርቤለት ምን ልታዘዝ አልኩት” አይ ምንም አይደለም ከይቅርታ ጋር ቆንስል ጀኔራል አቶ ዘነበ ከግቢው እንዳስዎጣት ትዕዛዝ ስለሰጡኝ ልነግርህ ነው! ” አለኝ!የወንድሜ ትህትና ልቤን ቢሰብረውም አቶ ዘነበ ማነጋገር እንደምፈግ በትህትና ጠየቅኩት ፣ በርቀት ሆነው በአይናቸው የሚቆጣጠሩኝን አቶ ዘነበን ጠራልኝና መጡ! ለምን እንደመከለከል አጥብቄ ሞገትኳቸው ፣ የሚመልሱት ባይኖርም በመረጃ ቅበላው ዙሪያ የምስራው ስራ አስነዋሪ እንደሆነ በደምሳሳው በመናገር ” ግድ የለም ግባ !” ሲሉ በገዛ ቤቴ የከለከሉኝ ሹም አቶ ዘነበ ፈቃድ ሰጡኝ!”ህግን ጠንቅቄ አውቃለሁ!” በሚሉት የጅዳ ቆንስል ጀኔራል አቶ ዘነበ የተላለፉት፣ የገሰሱትን መብቴን መልሰው ቢያከብሩትም የምሰራው የፖለቲካ ስራ እንጅ ለዜጎች በመቆርቆር እንዳልሆነ ጉብኝቱ አብቅቶ ከእንግዶቹ መካከል የመብቴን መገፋት ትክክል እንዳልሆነ ሳስረዳቸው ደጋግመው በሰጡኝ ምላሽ ገለጹልኝ !እንግዶችን ከበው እያነቡ በደላቸውን የገለጹትን ተፈናቃዮች እና መላሽ ይሰጡ የነበሩትን ሃላፊዎች ተመልክቻለሁ።
በአውላላው ሜዳ ላይ ጸጉራቸውን አንጨፍርረው የሚንቀዋለሉት ያበዱ እህቶችን ባስሙ ባያዩም ጩኽት ምሬታቸውን ያስተጋቡት ወደ መቶ የሚጠጉትን ተፈናቃዮች አቤቱታ ሰምቻለሁ!እመለስበትማለሁ !የእኒህን እህቶች በደል መናገር ፖለቲከኛ ካስባለ የምሰራው የፖለቲካ ስራ አለመሆኑን ለማሳየት የግፉአኑን በደል የሚያሳዩ ለማየት የሚሰቀጥጡ መረጃዎች ለማቅረብ ልገደድ ነው!! ይህን የማደርገው ከለመድኩት መቀመጫን ለመከላከል ከሚደረገው ተራ ውንጀላ ራሴን ከውንጀላ ለማጽዳት ሳይሆን እውነቱን ልነግራቸሁና ማን በህዝብ እና በሃገር ላይ ግፍና በደል እንደሚፈጽም ፍርድ ትሰጡ ዘንድ ለማሳየት ያህል ብቻ ነው!
ለሁሉም ከስሜት ወጥቸ በምቀጥልበት የማለዳ ወግ እናዎራለን!
ቸር ያሰማን ! ነቢዩ ሲራክ
የግብፅና ኢትዮጵያ መጪው ዘመን ምን ሊመስል ይችል ይሆን?

መንግስት የሙት ዓመትና ተዝካር ማለት ትቶ ትኩረቱን ለሐገራዊ መግባባት ቢሰጥ – ግርማ ሠይፉ ማሩ
ትንሽ ስለ ‘መለሲ-ዝም’: ከኢህአዴጎች የምስማማበት ነጥብ
Abraha Desta from Mekele, Tigrai
ሳስበው ሳስበው ስለ ‘መለሲዝም’ ሰበካ የተጀመረ ይመስለኛል። በመለስ ማመናቸው ችግር የለብኝም። ግን መለስ ፈጣሪያቸው መሆኑ እየነገሩን ነው። ብዙ ነገሮች በሱ ስም እየተሰየሙ ናቸው። እነሱ እንደሚነግሩን ከሆነ የኢህአዴግ ፖሊሲ የመለስ ነው፣ መለስ ወታደራዊ መሃንዲሳቸው ነበር፣ መለስ አንቀሳቃሽ ሞተራቸው ነበር፣ የኢህአዴግ ሓሳብና ተግባር የመነጨው ከመለስ ነበር፣ ባጠቃላይ መለስ ሁለመናቸው ነበር።
ለዚህም ነው የኢህአዴግ አባላት አውቀውም ሳያውቁም መለስ የተናገረውን እንደ ፓሮት የሚደግሙት። በራሳቸው ማየት ሳይችሉ መለስ በመራቸው ይጓዛሉ። ለዚህም ነው መለስ ያወጣውን ፖሊሲ መተግበር የማይችሉ። ፖሊሲው መተግበር ያልቻሉበት መንገድ ማየት ስለሚሳናቸው ፖሊሲው ጥሩ መሆኑ ተናዘው ችግሩ ያለው ግን አፈፃፀሙ ላይ መሆኑ ይለፍፋሉ።
ግን አንድ ትክክል ወይ ጥሩ የሆነ ፖሊሲ እንዴት ላይፈፀም ይችላል? ፖሊሲ’ኮ አፈፃፀም ነው። ፖሊሲ ከህልም የሚለይበት ዋነኛው መስፈርት ስለሚፈፀም ነው። ስለዚህ አንድ ፖሊሲ አፈፃፀም ላይ ችግር ካጋጠመው ፖሊሲው ትክክል አይደለም ማለት ነው። ግን የመለስ ልጆች ‘ፖሊሲው ስህተት ነው’ ብለው የማጋለጥ ዓቅሙና ድፍረቱስ አላቸው? አይመስለኝም። ምክንያቱም ፖሊሲው የመለስ ነው። ፖሊሲው ስህተት እንደሆነ መናገር ማለት መለስ እንደሚሳሳት መመስከር ነው። መለስ ደግሞ ፈጣሪያቸው ነው። ለዚህም ነው ከነ ስህተቱ ‘የመለስ ሌጋሲ ወይ ራእይ’ እያሉ የመለስን የተሳሳተ የፖለቲካና የኢኮኖሚ አቅጣጫ ለማስቀጠል የሚባዝኑ።
ከኢህአዴግ አባላት የምስማማበት ነጥብ አለኝ፤ መለስ ሁለመናቸው ነው። እሱ የተናገረውን ያደርጋሉ፣ ይፈፅማሉ። ከነሱ ጋር የምስማማበት ነጥብ ይሄ ነው። ይሄንን ነጥብ ትርጓሜ እንስጠው።
የኢህአዴግ አባላት (እነሱ ራሳቸው እንደሚነግሩን) መለስ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ዕይታ ምንጫቸው ነው። አዎ! ነው። ይህ ማለት አባላቱ ምን መስራት እንዳለባቸውና እንደሌለባቸው መለስ ይነግራቸው ነበር ማለት ነው። እነሱም ‘የታላቁ ባለራእይ መሪ’ ትእዛዞች ተቀብለው ይተገብሩ ነበር ማለት ነው።
የመለስና የአባላቱ ግንኙነት እንዲህ ከነበረ መለስ dictate ያደርጋቸው ነበር ማለት ነው። በእንግሊዝኛው አጠራር ሌሎችን dictate የሚያደርግ መሪ Dictator ይባላል። ስለዚህ ከተግባራዊ ትርጓሜው ተነስተን መለስን ስንገልፀው Dictator ነበር ማለት ነው። “Dictator’ ወደ አማርኛ ስንመልሰው ‘አምባገነን’ (ብትግርኛ ‘ዉልቀ መላኺ’) የሚል ትርጓሜ ይይዛል። ስለዚህ ‘ሁሉም ወይም አብዛኞቹ የፓርቲው ስራዎች የመለስ ነበሩ’ በሚል ከተስማማን ‘መለስ አምባገነን ነበር’ በሚልም መስማማት ይኖርብናል።
እኔ ‘መለስ አምባገነን ነበር’ ሲል ‘የሁሉንም አድራጊ እሱ ነበር’ እያልኩኝ ነው። እናንተም በራሳቹሁ ሚድያና አንደበት ተመሳሳይ ነገር እየነገራችሁን ነው። ስለዚህ ሓሳባችን አንድ ነው። ተስማምተናል። በመለስ ስራና ስያሜ ላይ ልዩነት የለንም።
(ስለ መለስ ላለመፃፍ ዕቅድ የነበረኝ ቢሆንም የመንግስት ሚድያዎች ግን ስለሱ እያስታወሱ አስቸገሩኝ)
በወያኔ “ያደገችዋን” ኢትዮጵያ ዓለም እንዴ ያያታል?- ዶ/ር ዘላለም ተክሉ
ነሐሴ 25 2013
በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢሳት የቀረበውን “ የእሁድ ወግ” ፕሮግራም ሳዳምጥ ነበር:: በዚሁ ፕሮግራም ከቀረቡት ዋና ዋና መወያያ ርዕሶች ውስጥ ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለኢትዮጵያ ህዝብ አጎናጸፉት እየተባለ ስለሚደሰኮረው ዕድገት የተሰጡት አስተያየቶች ትኩረቴን ስበውኝ ነበር:: በተለይ ሰውዬው (ከሳቸው የተማርኩት አባባል ስለሆነ ይቅርታ) ህዝቡን ጥጋብ በጥጋብ አደረጉት፣ ብዙ ሃብታም ገበሬዎችን ፈጠሩ፣ሚሊዮኖችን ከድህነት አረንቋ አላቀቁ ስለሚባለው አቶ ሲሳይ አጌና የሰጠው ምላሽ በጥሩ ትንተና የተደገፈ መሆኑ ያስደሰተኝ ሲሆን በዚች ትንሽ መጣጥፍ የበለጠ ማጠናከሪያ በመስጠት ፕሮፓጋንዳውን ለመሞገትና ምስኪኑ ህዝባችንም እውነታውን ራሱ ፈትሾ እውነቱን እንዲያውቅ ፈለኩ::
አቶ ሲሳይ ሙግቱን (argument) ሲያስረዳ፣ በእውነት የፕሮፓጋንዳ ማሽኖቹ በተደጋጋሚ እደሚነግሩን በእርሳቸው መጀን ኢኮኖሚያችን አድጎዋል ከተባለ ከ 80 በመቶ በላይ የሆነው ገበሬው ህዝባችን ኢኮኖሚው አድጓል ማለት ነው:: የገበሬዎች ገቢ ደግሞ አደገ ከተባለ ያ ሊሆን የቻለው ያመረቱቱትን ብዙ ምርት ወደገበያ አውጥተው ሸጠው ጥሩ ገቢ ሰብስበዋል ማለት ነው:: እነሱ ብዙ የእርሻ ምርት ወደ ሽያጭ አመጡ ማለት ደግሞ በየከተሞቹ በኢንዱትሪና አገልግሎት ዘርፎች እየሰራ የሚተዳደራው ህዝባችን ከበቂ በላይ የምግብ አቅርቦት አግኝቷል ማለት ነው:: ገበሬዎች ገቢያቸው አደገ ማለት ደግሞ ከከተማው ኢንዱስትሪና አገልግሎት ዘርፎች የሚመረቱትን ምርቶች የመግዛት ፍላጎታቸውና አቅማቸው ጨምሩዋል ማለት ነው:: የነዚህ ዘርፎች መነቃቃት ደግሞ ምርታቸውን የበለጠ እንዲያድግ ያበረታታዋል የከተሜውም ገቢ ይጨምራል ማለት ነው:: የምግብና የኢንዱስትሪ ውጤቶች ምርት አቅርቦት (supply) ከፍላጎት (demand) በላይ ከሆነ ዋጋ አይጨምርም:: ወይም ደግሞ የምርት ፍላጎት እና አቅርቦት ከገቢ መጨመር ጋር በትይዩ (parallel) ሊያድጉ ከቻሉ በዋጋ ላይ ምንም ለውጥ አያመጡም ማለት ነው:: በአሁኗ ኢትዮጵያ ያለው እውነታ በተቃራኒው ስለመሆኑ ግን ይህን ሁሉ ትንታኔ ሳያስፈልገው አንድ ተራ ኢትዮጵያዊ እንኳን ሊያስራዳው የሚችለው ነው:: እየኖረበት ስላለው ድህነቱ ለመናገር የሮኬት ሳይንቲስት መሆን አያስፈልግምና::
የከተሜው ህዝብ የሚበላውን ዳቦና እንጀራ ከዛሬ 5 እና 6 ዓመት በፊት ከሚገዛበት ከ 4 እስከ 5 እጥፍ በላይ የሚሸምትበትና ከአለፈው ዓመት እንኳን በ 20 በመቶ ጭማሬ የሚሻማበት፣ የገጠሩ ህዝባችን የሚያስፈልገውን ጨው፣ስኳር፣ ዘይትና ለእርሻ የሚያስፈልጉት ማዳበሪያና ማራሻ መሳሪያዎች በተመሳሳይ ጭማሪ ዋጋ እየተንገታገተ የሚገዛበት ዋናው ምክንያት ገቢው “በአርቆ አሳቢውና ልማታዊው” መሪ አስተዋጽዖ በማደጉ ሳይሆን በተዝራከረከው፣ በጠባብ ብሄረተኛው፣ በሙናስና በተጨማለቀውና በአድሎአዊ አመራር ድክመት ምክንያት ከፍተኛ የምርት ፍላጎትና አቅርቦት ክፍተት (Supply and Demand Gap) በመፈጠሩ ነው:: ይህም ክፍተት የምርትና የሃብት እጥረትን (scarcity) ፈጥሯል:: ይህ እጥረትም ለዋጋ ንረቱ ዋነኛ አስተዋጽዎ አድርጓል:: ስለዚህ የምግብና የኢንዱስትሪ ምርት እጥረት በሰፈነበት አንጻር ዕድገት አለ ብሎ ማናፋት “እናንተ ዓይናችሁን ጨፍኑ እኔ እንደፈለገኝ ላፏልል” እንደማለት ይቆጠራል::
የዓለም ባንክና ዓለምአቀፍ የገንዘብ ድርጅት የአገራችን ኢኮኖሚ “እንዳደገ” ቢነግሩን ሊደንቀን አይገባም:: እነዚህ ድርጅቶች በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ወያኔ የሚሰጣቸውን መረጃ (data) ብቻ እየወሰዱ መልሰው እንደሚነግሩን መገንዘብ ይገባናል:: አንደኛው ሁለቱም የሚታዘዙት በአሜሪካ መንግስት ፍላጎት ነው:: አሜሪካ ከግማሽ በላይ የሚሆነውን የነዚህን ድርጅቶች በጀት የምትች ስለሆነች በድርጅቶቹ ህልውናና በሃላፊዎቹ ቅጥርና ዕድገት ላይ ወሳኝ ሚና አላት:: አሜሪካ ደግሞ አሸባሪነትን ለመዋጋት ወያኔን እንደ ፈለገች ስለምትጠቀምበት እሱን የሚነካባትን ሁሉ ድራሹን ማጥፋት ትችላላች:: በሁለተኛ ደረጃ ወያኔም ይህን ግንኙነትና መስተጋብር ስለሚያውቅ የኢኮኖሚ ፖሊሲህ ወይም የምታቀርበው የዕድገት መረጃህ ትክክል አይደለም ብለው የሚከራከሩ የባንኮቹ ሃላፊዎች ካሉ ከጣፋጩ ሥራቸው እንዲሰናበቱ ሊያደርግ ይችላል:: ስለዚህ ባንኮቹ ጉዳዩን ቢያውቁት እንኳን የተሰጣቸውን መረጃ ይዘው ከማዳረስ ሌላ ምንም አማራጭ የላቸው::
ለነገሩ ይህ የሚነገረን የተቀቀለና የበሰለ የዕድገት መረጃ ለጂኦፖለቲካዊ ፍጆታ ከመዋል በስተቀር ዓለም አሁንም ጠንቅቆ የሚያውቀን እስካሁን በመከራ፣ በድህነት፣ በበሽታ እንደምንማቅቅ ነው:: ይህንንም ያልኩበት ከሰሞኑ ከሥራዬ ጋር በተያያዘ አንድ የ Health Economics መጽሃፍ ሳነብ አንድ አሳዛኝ መረጃ ስላየሁ ነው:: በመጽሃፉ የኢትዮጵያ ምሳሌ የቀረበው እጥረት (scarcity) የተባለውን የኢኮኖሚ ንድፈ ሃሳብ (theory) በተግባር (Application) ለማስረዳት ታስቦ ነበር:: በዚህ ንድፈሃሳብ መሰረት የሃብት እጥረት የትም ሃገር አለ፣ በደሃውም በሃብታሙ ውስጥም አለ ይልና ነገር ግን ከእጥራትም እውነተኛ እጥረት አለ (There is scarcity and there is real scarcity) ያም በኢትዮጵያና በባንግላዴሽ በከፋ ሁኔታ ይታያል ብሎ ከነዝርዝር መረጃው ያስረዳል::
ምንጭ: Folland, S., Goodman, A. G. and M. Stano (2013). The Economics of Health and Health Care. (7th edition). New Jersey: Pearson Education, Inc.
ይህ መረጃ በተጠቀሰው መጽሃፍ ላይ የቀረበው በአለም ዙሪያ ቢዝነስን ለሚማሩና ቢዝነስን ለሚሰሩ ሁሉ ያሁንዋን ኢትዮጵያ ከሌላ ሃገራት ጋር ሲነጻጸር እንዴት ማየት እንዳለባቸው ለማስረዳት ነው:: በሰንጠረዡ እንደታየው በኢንዱስትሪ የበለጸጉት አሜሪካና ጀርመኒ የነፍስ ወከፍ ገቢያቸው ከራሻና ብራዚል ከ3 እስከ 5 ጊዜ እጥፍ፣ከቻይናና አልባኒያ ከ 6 እስከ 8 ጊዜ እጥፍ፣ ከባንግላዴሽና ኢትዮጵያ ከ 83 እስከ 133 ጊዜ እጥፍ እንደሆነ፣ በዚህም ምክንያት ጤንነታቸውን ለመጠበቅ የሚያወጡት ወጪ ከፍተኛ እንደሆነ፣ስለዚህም በበሽታ የመጠቃት ዕድላቸውና የህጻናት ሞት መጠናቸው በጣም ዝቅተኛ እንደሆነ ሲያሳይ:: ኢትዮጵያን ደግሞ በዝቅተኛና እጥረት (በተሞላበት በቀን ከ 1 ዶላር በታች ገቢ) እንኳን ለጤንነታቸው በቂ ሊመድቡ የዕለት ምግብ ፍላጎታቸውን እንኳን ሊያሟሉ ባላመቻላቸው በቲቢ (Tuberculosis) በከፍተኛ ደረጃ ለመጠቃትና ለየህጻናት ሞት መዳረጋቸውንና በዚህ የተነሳ ረጅም ዕድሜ የመኖራቸው ዕድል ዝቅተኛ መሆኑን ያሳያል:: እንግዲህ ያሁንዋን ኢትዮጵያ ዓለም የሚያያት እንደዚህ ነው:: የዓለም ባንክ ሆነ የአሜሪካ መንግስት መጥቶ ይህ የጠላት ወሬ ነው ወይም የአክራሪ ተቃዋሚዎች የተሳሳተ መረጃ ነው ሊል አይችልም፣ወይም አይሞክርም::
ወያኔ የፈለገውን ያክል ያምታታ ወይም ረጂ ሃገራትን ለማባበል የፈለገውን ዓይነት የማክሮ ኢኮኖሚ (Macroeconomic) ማስተካከያ እርምጃ ይውሰድ፣ ነገር ግን ምርት እንዲጨምር ማድረግ ካልቻለና ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል የሚፈጥር መዋቅራዊ ለውጥ ካላደረገ የሚደሰኩረውን ዕድገት በእውን ሊያሳይ በጭራሽ አይችልም:: ዳሩ የሥርዓቱ ይሄ ሁሉ ፕሮፓጋዳ ከምሩ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ዕድገትን ለማጎናጸፍ ሳይሆን በፖለቲካውና በሰባዊ መብት ረገድ የሚሰራውን ግፍ ለመሸፈንና ይህን የዝርፊያና አንድ ብሄርን ብቻ በማበልጸግ አቅጣጫ የተያያዘውን ጉዞ እንዳይሰናከል የሚከላከልበት ዋነኛ መሣሪያው ስለሆነ ነው:: ከነሱ እጅ እውነተኛ ዕድገት ይመጣል ብሎ መጠበቅ የዋህነት ብቻ ሳይሆን ስንፍናና ፈሪነትም ጭምር ነው:: መፍትሄው ከቅርብ ወራት ወዲህ እየተጠናከረ የመጣውን የለውጥ እንቅስቃሴ አጣናክሮ በመቀጠል አገዛዙንና ሥርዓቱ መቀየር ብቻ ነው:: ይህ ብቻ ሲሆን ነው ዓለም አሁን የሚያውቃት መከረኛዋና ችግረኛዋ ኢትዮጵያ ልትለወጥ የምትችለው:: የፕሮፓጋዳ ዕድገት ግን ዘበት ብቻ ነው!!!
አገራችን ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!!
በትዞራለች …ትዞራለች …ሲደክማት ታርፈና አሁንም ትዞራለች !
በአዕምሮ ሁከት የተለከፈችው እህት በጅዳ!
አንድ ወዳጀ መሃመድያ ተብሎ በሚጠራው የጅዳ ከፍል ከኢትዮጵያ አለም አቀፍ ትምህር ቤት አካባቢ ይህችን በፎቶው ላይ የምታዩዋትን እህት አግኝቶ ሊያነጋግራት ቢሞክርም ፈቃደኛ አልነበረችም። ከየት ነው የመጣሽ ? ስትባል” ከመቀለ ” ከማለት ባለፈ ስሟንና የሆነችውን አትናገርም ። ብዙ ሊያግባባት ሞክሮ ያልተሳካለት ይህ ወዳጀ ይህች እህት ያደፈና የተቀደደ ጥቁር “አባያ” ለብሳና መናኛ ነጠላ ጫማ የተጫማችው እህት የአዕምሮ ሁከት እንዳለባት የተረዳው ብዙ ለማነጋገር ሞክሮ በሰጠችው አንዳንድ ምላሽ እንደሆነ ገልጾልኛል! ልጁን ትምህርት ቤት ሊያስመዘግብ በሔደበት አጋጣሚ በጠራራው ሜዳ ስትንከራተት በማየቱና ምንም መርዳት ባለመቻሉ ያዘነው ወዳጀን መረጃ ይዠ የጅዳን ቆንስል ሃላፊዎች ስልክ በመደዎል ይህችን እህት በመጠለያው አምጥተው ሌላው ቢቀር ካሉት የአዕምሮ በሽተኞች ጋር ቀላቅለው ከመኪና እና ከመሳሰሉት አደጋዎች አንዳትጋለጥ ይሰበስቧት ዘንድ ለማሳወቅ ያደረግኩት ሙከራ አልተሳካም!
አንድ ሌላ ወዳጀ ከትናነት በስቲያ የዚህችን እህት አሁን ድረስ በአካባቢው መኖርና ዝም ብላ እንደምትዞር ነገረኝና ወዳለችበት አካባቢ ሔጀ በአካል ለማነጋገር ሞክሬ ነበር ። በጠራራው ጸሃይ የውሃ ፕላስቲክ ባንድ እጇ በሌላ እጇ ፊስታል አንጠልጥላ እየሳቀች እና እየተኮሳተረች ክው ክው እያለች የምትራመደው እህት አገኘኋት። ብዙ ከተከትልኳት በኋላ አረፍ ስትል ጠብቄ አማርኛ ትችያለሸ ? አልኳት “ግደፈኒ” አለችኝ ፊቷን ዘወር እያደረገች! ለማግባባትና ለማቅረብ ሞከርኩ ፣ ልታሰቀርበኝ አልቻለችም! ብዙ ተከተልኳት! … ትዞራለች …ትዞራለች …ሲደክማት ታርፈና አሁንም ትዞራለች ! በቃ ! እንዲህ ሆናለች …
ዛሬም እዚያው አካባቢ እየዞረች እንደምትገኝ ወደ ትምህርት ቤት ለጉዳዩ የሔደ ወንድም አግኝቷት በስልክ ገልጾልኛል። ስትንከራተት አይቶ ሊረዳት የፈለገው ይህ ወንድም እሱም ሆነ ያየውን የዚህች እህት አበሳ ያሳያቸው የትምህርት ቤቱ ሴት ኢትዮጵያውያን መምህራን ተከትለው ሊያነጋግሯትና ሊረዷት ቢፈልጉም ፈቃደኛ ባለመሆኗ ምንም ማድረግ እንዳልቻለ እያዘን ካነሳው ፎቶ ጭምር ልኮልኛል! ዛሬም ይህን መረጃ ለማቀበል ወደ ጅዳ ቆንስል ሃላፊ ወደ ቆንስል ጀኔራል ዘነበ ከበደ እና ቆንስል ሙንትሃ ስልክ ደውየ የነበረ ቢሆንም ሊመልሱልኝ ግን አልቻሉም! ይህ በእንዲህ እንዳለ በተፈናቃይ ሰራተኞች ዙሪያ ጥናት ለማድረግ በአንባሳደር ውብሸት የተመራ ቡድን ዛሬም በጅዳ ከቆንስል ሃላፊዎች ጋር በመምከር ላይ መሆኑን ታውቋል።
ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ
ማን ይናገር የነበረ….. የታኅሣሡ ግርግር እና መዘዙ!

አጠቃቀምና የቃላት አሰካክን የተከተለ ነው፡፡ አልፎ-አልፎ የቀበልኛ ቃላትን ቢጠቀምም እንኳ፣ በግርጌ ማስታወሻ አማካይነት “ፍቻቸው” ተቀምጧል፡፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያለው ጉድለት በዋናነት አንድ ነው፡፡ እርሱም፣ በአረንጓዳ ሳሎን ውስጥ በነገርሜ የተገደሉባቸው የራስ አበበ አረጋይ፣ የራስ ስዩም፣ የሜ/ጄኔራል ሙሉጌታ ቡሊ፣ የአቶ መኮንን ሀብተ ወልድና የሌሎችንም ባለሥልጣመናት ቤተሰቦች አለማናገራቸው ነው፡፡ ከዓመታት በኋላ፣ እነዚህ የሟቾቹ ቤተሰቦች ስለመፈንቅለ መንግሥቱ ያላቸውን ስሜትና እውቀት ሊያካትቱት ቢችሉ ምንኛ ዕጹብ-ድንቅ ይሆን ነበር፡፡ ከአቶ ብርሃኑ አስረስ አልገፉበትም እንጂ፣ ትልቅ ሙከራ አድርገው እንደነበር አያጠራጥርም፡፡ በ1953 ዓ.ም የፍትሕ ሚ/ር የነበሩትን ደጃ/ች ዘውዴ ገ/ሥላሴንና ብ/ጄኔራል መኮንን ደነቀን ለማነጋገር ያደረጉት ጥረት መልካም ነው፡፡ እጅግም የሚደነቅ ነው፡፡ በሰማኒያ ሦስት ዓመታቸው የተለያዩ ጫናዎችን ተቋቁመው ይኼንን የመሰለ ድርሳን ስላቀረቡልን ለአቶ ብርሃኑ አስረስ ያለኝን ምስጋናና ልባዊ አክብሮት በአንባቢያን ስም ይድረሳቸው እላለሁ፡፡ አንባቢያንም፣ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ዋጋው ተፋፍቆ በእጥፍ ከምትገዙት፣ ዛሬውኑ መጽሐፉን በትክክለኛው ዋጋ “የግላችሁ አድርጉት!” በማለት ወንድማዊ ምክሬን አስተላልፋለሁ፡፡ ለአቶ ብርሃኑም መልካም ጤንነትና ሰላምን እመኛለሁ፡፡ (በተረፈ፣ በቸር እንሰንብት!)