Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » Opinion & Analysis
Viewing all 1664 articles
Browse latest View live

ፓርቲዎች በምርጫ አንሳተፍም ቢሉ….. 

$
0
0

በምርጫ አለመሳተፍ መብት ነው !በኢትዮጵያ ያለው ጭላንጭል የፖለቲካ ምኅዳር ሲታይ፣ይህ ውሳኔ የሕግ፣የፖለቲካ እና የሞራል ድጋፍ አለው፡፡ሆኖም ግን በምርጫ ያለመሳተፍ መብት በራሱ-የራሱ የሆነ ተግዳሮቶች አሉትና፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የትርፍ-ኪሳራ ሥሌት የግላቸው ነው የሚሆነው፡፡

 

ይድነቃቸው ከበደ

(ይድነቃቸው)

(ይድነቃቸው)

ይህ ጹሑፍ በምርጫ አለመሳተፍ መብት መሆኑን ከህግ አንፃር ለማየት እንጂ፣ የሚጪው አገረ አቀፍ ምርጫን አስመልክቶ “ኢሕአዴግ ለመርጫ አልተዘጋጀም !” እና “የ24 ሰዓት ተቃውሞ በአዲስ አበባ !” በሚል ዕርሶች ከዚህ በፌት በፃፍኳቸው ፁሑፍ የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ፣ ገዥው መንግስት ለነፃ እና ፍትሃዊ ምርጫ እራሱን አዘጋጅቶ፣ ውጤታማ ምርጫ ማካሄድ እንደማይቻል የግል እምነቴን ገልጫለው፡፡

ወደተነሳሁበት ዕርስ ስገባ፡- ማንኛውም ሰው በፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ እንዲሳተፉ አይገደድም፣ባለመሳተፉ ግን ተቃውሞን የመግለፅ እና ደግፋ የመስጠት መብት ይነፈጋል ማለት አይደለም ፡፡ይህም በመሆኑ የትኛውም የዲሞክራሲ ሥርዓት የተሟላ ተሳትፎ በህብረተሰብ ካልተደረገበት ውጤታማነቱ ደካማ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡የዲሞክራሲ ሥርዓት ማሳያ መስታዎት ከሆኑት ውስጥ አንዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በነፃነት መንቀሳቀስ ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ያለምንም ፍርሃት በፈለገው ወይም በፈለገችው ፓርቲ ውስጥ አባል የመሆን ዕድልና አማራጭ ማግኘት የግለሰብ መብት ነው፡፡ግለሰቦች በፈለጉት የፖለቲካ ፓርቲ የመደራጀት እና የመሳተፍ ነፃነት ሲኖራቸው ለዲሞክራሲ መሠረት ይሆናል፡፡

ይህ አይነቱ የዲሞክራሲ ሥርዓት በአገራችን ምን ያኸል ተፈፃሚ ነው ? ተብሎ ቢጠየቅ ምላሹን ለማወቅ ብዙም አድካሚ አይደለም፡፡ውጤቱ አሉታዊ ነው፡፡እርግጥ ነው በሕገ መንግስት አንቀፅ 31 ማንኛውም ሰው ለማንኛውም ዓለማ በህግ “የመደራጀት” መብት እንዳለው በግልፅ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ይሄን መነሻ በማድረግ በአገር አቀፍ እና በክልል ደረጃ የተቋቋሙ የፖለቲካ ፓርቲዎች መኖራቸው የሚታወቅ ነው፡፡የእነዚህ ፓርቲዎች መብት እና ግዴታ እንዲሁም ሊከተሏቸው የሚገባ መርህዎች፣ በሕገ መንግስቱ፣በፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ አዋጁች እዲሁም በመተዳደሪያ ደንብቻው ብቻ ነው፡፡

በዚህም መሠረት ተቋቁመው እየተንቀሳቀሱ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በአገራችን ቁጥራቸው በርካታ ቢሆንም፣ ቢሚፈለገው ሁኔታ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ግን በቁጥር አነስተኛ ፓርቲዎች ሲሆን፣ የተቀሩት የምርጫ መጣ ወይም የመግለጫ አሯሯጮች pacemaker መሆናቸው በግልፅ የሚታወቅ ነው፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ዋንኛ ዓላማ በመርጫ ተወዳድረው በማሸነፍ የፓለቲካ ሥልጣን በመያዝ የቆሙለት ዓላማ በስልጣን ዘመን ተግባራዊ ማድረግ ነው፡፡

ምርጫ በዲሞክራሳዊ አካሄድ ለሚወከል መንግስት የጥንካሬ መለኪያ ነው፡፡ይህን ለማለት የሚያስችለው ተመራጮች መብታቸው እና ግዴታቸውን ሙሉ በሙሉ ከመራጩ ሕዝብ ስለሚያገኙት ነው፡፡እንዲ አይነቱ በሕዝብ ተሳትፎ ሥልጣን የሚቀየርበት ዋናው መንገድ ነፃና ሚዛናዊ የሆነ ምርጫ ሲደረግ ብቻ ነው፡፡ በአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ በኢሕአዲግ/ በህወሐት መንግሰት የ24 ዓመት የስልጣን ዘመን በተደረጉ ምርጫዎች ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለመሆን አልቻለም፡፡ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ በዋነኛነት የሥርዓቱ አስከፊ ድርጊት ቢሆንም፣ በተጨማሪ ጠንካራ የሆኑ በመላው ኢትዮጵያ የሕዝብ ድጋፍ ያለው የተቃዋሚ ፓርቲ አለመኖሩም ጭምር ነው፡፡ እርግጥ ነው በ1997 ዓ.ም በቅንጅት የታየው የተቃዋሚ ፓርቲዎች መነቃቃት፣ በአገራችን የዲሞክራሲ በዓል አንድ እርምጃ ወደፊት ከነበረበት ያንቀሳቀሰው ቢሆንም፣ በገዥው ሥርዓት ቀጥተኛ ተፅኖ፣ እንዲሁም በቅንጅት ፓርቲ ውስጥ በታየው ድክመት እና የስልጣን ሽኩቻ የለውጥ እንቅስቃሴውን ገትቶታል፡፡

አሁን ላይ በአገራችን የሚንቀሳቀሱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ከበፊቱ “በቆምክበት እርገጥ” አይነት የተቃውሞ እንቅስቃሴ ተላቀው ምን ያህል “ወደፊት” እየሄዱ ነው የሚለውን ምላሽ ይህን ጹሑፍ ለሚያነቡ እና ለጉዳዩ ቅርብ ነኝ ለሚሉ ወገኖች የምተወው ሃሳብ ነው፡፡ ሆኖም ግን በአገር ውስጥ የሚንቀሣቀሱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ከ6 ወር በኋላ አገር አቀፍ ምርጫ ይጠብቃቸዋል፡፡ፓርቲዎች የምርጫ ፓርቲ ቢሆኑም ፣በምርጫ አለመሳተፍ መብታቸው በሕግ የተጠበቀ መሆኑን አውቀው ግራ ቀኛቸውን ቢመለከቱ፣ዝም ብሎ ገዥውን ፓርቲ በምርጫ ከማጀብ ይላቀቃሉ፤አሊያም በእኩል ተሳትፎ ወደ ምርጫው የሚገቡበትን መንገድ ተገዳድረው ማመቻቸት ይቻላል፡፡

የተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ አዋጅ ቁ .573/2000 አንቀፅ 39 ቁ.2 ሐ.“ የፖለቲካ ፓርቲ ለሁለት ተከታታይ የምርጫ ዘመን የጠቅላላ ወይም የአካባቢ ምርጫ ወድድርን ሳይሳተፍ የቀረ እንደሆነ ” ምርጫ ቦርድ በአዋጁ መሠረት ውሳኔ በማስተላለፍ ከመዝገብ ሊሰርዝ ይችላል፡፡የሚል የህግ ድንጋጌ አለ፣ይህን ድንጋጌ ከተነሳንበት ዓላማ ጋር በማገናኘት ምክንያት እና ውጤቱን መመልከት ተገቢ ነው፡፡

በመሠረቱ የፓርቲ ነፃነት በእንዲ መልኩ መገደብ አጠቃላይ የአዋጁ ችግር ዋንኛ ማሳያ ነው፡፡የትኛውም ፓርቲ በምርጫ የመሳተፍ ወይም ያለመሳተፍ መብት ካለጊዜ ገደብ ለራሱ ለፓርቲ የሚተው ስራ እንጂ ፣በህግ ገደብ የተጣለበት መሆን የለበትም፡፡ይህን ለማለት የሚያስደፍረው የግል እንዲሁም የጋራ መብት የሚጋፋ በመሆኑ ነው፡፡ለዚህም ማሳያ የመምረጥ እና ያለመምረጥ መብት የተጠበቀ ነው፡፡ ለምሳሌ እኔ በመጪው ምርጫ አልመርጥም ፣አልመረጥም ይህ በህግ ክልከላ ተደርጎብኝ ሳይሆን የእኔ መብት በመሆኑ ነው፡፡ልክ እንደኔ የግል መብት ያላቸው ሰዎች ተሰባበስበን የጋራ መብታችን ለማቋቋም በምንቀሳቀስበት ወቅት በግሌ ማድረግ የምችለውን በጋራ እንደማጣት ይቆጠራል፡፡ከዚህ አንፃር ይህ ድንጋጌ በእኔ እይታ ተገቢ መስሎ አይታየኝም፡፡

አሁን ባለው ነባራዊ ሃቅ በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች የሚተዳደሩት በዚህ አዋጅ ነው፡፡በመሆኑም አዋጆን መሠረት በማድገረግ በምርጫ አለመሳተፍ ገደብ ቢኖረውም ለፓርቲዎች የተሰጠ መብት አለ፡፡ ማንኛው ፓርቲ ለሁለት ተከታታይ የምርጫ ዘመን ሳይሳተፍ የቀረ እንደሆነ ይሰረዛል፡-ይህ ማላት፣በ2002 አገር አቀፍ ምርጫ በማንኛውም ምክንያት በምርጫ ያልተሳተፈ “ሀ” የተባለ ፓርቲ በ2007 የማይሳተፍ ከሆነ ይሰረዛል ማለት ነው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ይሄ “ሀ” የተባለው ፓርቲ በ1997 ምርጫ አልተሳተፈም ብንል ፣በ2002 ተሳትፏል ካልን በ2007 ምርጫ አለመሳተፍ የ”ሀ”ፓርቲ መብት ነው፡፡ይህም በማድረጉ ከምርጫ ቦርድ ምን አይነት ጥያቄ ለዚህ ፓርቲ አይቀርብም፡፡በዚህ መሠረት ፓርቲዎች ለሁለት ተከታታይ የምርጫ ዘመን በምርጫ ካተሳተፉ የመሰረዝ እጣቸው በእጃቸው ነው፡፡ሆኖም ግን የምርጫ ዘሙኑ ተከታታይነት ሳይኖረው በምርጫ አለመሳተፍ በአዋጁ መሠረት የሚያስከትለው ውጤት አይኖረውም፡፡

ይህ ከላይ የቀረበው ማሣያ፣ ለአገር አቀፍ እንዲሁም ለአካባቢ ምርጫ የሚያገለግል ነው፡፡በአሁን ወቅት ሁለቱ ምርጫዎች በተመሳሳይ የምርጫ ዘምን ባለመካሄዳቸው እረሳቸውን ችለው የሚቆጠሩ የምርጫ ዘመን ነው፡፡በኢትዮጵያ አሁን ባለው የምርጫ ስርዓት ፣የአንድ የምርጫ ዘመን አምስት ዓመት ነው፡፡ስለዚህም በአገር አቀፍ እና በአካባቢ የምርጫ ዘመን የ2 ዓመት ልዩነት አለ ማለት ነው፡፡በመሆኑም በዘንድሮ የአገር አቀፍ ምርጫ ዘመን ከባለፈው ሁለት ዓመት ከተካሄደው የአካባቢ ምርጫ ዘመን ፈፅሞ የሚገኛኝ አይደለም፡፡

በሕገ መንግሥት አንቀፅ 38 ቁ.1 ሐ.“ በማናቸውም ደረጃ በሚካሄዱ ምርጫ፣የመምረጥ እና የመመረጥ ፣ምርጫው ሁሉ አቀፍ፣በእኩልነት ላይ የተመሰረት እና መራጩ ፈቃዱን በነጻነት የሚገልፅበት ዋስትና የሚሰጥ መሆን አለበት፡፡”በማለት የህጎች ሁሉ የበላይ ሕግ በሆነው ሕገ መንግሰት በግልፅ ተቀምጧል፡፡

ሆኖም በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ሕገ መንግስቱን መሰረት ያደረገ ምርጫ ስለመካሄዱ አጠራጣሪለው የሚል ፓርቲ፣እንዲሁም ምርጫው ከመካሄዱ በፌት በምርጫው ሄደት ላይ ቅደመ ሁኔታ እስካልሟላለት ድረስ የታሰበው ምርጫ ነጻ፣ፍትሃዊ፣ ተኣማኒና አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አይደለም በማለት ከበቂ ምክንያቶች ጋር በማዛመድ ከላይ በተገለፀው የተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ አዋጅ መሰረት፣ በምርጫ ያለመሳተፍ መብት በሕግ ድጋፍ ያላው መብት ነው፡፡

ይህ መብት ከሕገ መንግሰቱ እና ከላይ በተገለፀው አዋጅ የመነጨ ሲሆን፣ ከዚህ ውጪ ያሉ ማናቸውም አሰራሮች፣ልማዳች እንዲሁም መመሪያ ይህን መብት የሚጋፉ መሆን እንደሌለባቸው የታወቀ ነው፡፡እናም ፓርቲዎች ሁሌም የፖለቲካ ምኅዳሩ ተዘግቷል፣ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄድ አልቻልንም፣መሰብሰቢያ አዳራሽ ተከለከልን……..ወዘተ እያሉ ከሚናገሩ፣ምኅዳሩ እንዲሰፋ ከገዥው ፓርቲ ጋር በመነጋገር ማስተካከል ካልተቻለ፣በጊዜ ከምርጫው ታቅበው ገዥው ፓርቲ እራሱ ደግሶ እራሱ ለብቻው ይስተናገድበት ዘንድ በመተው እውነታውን ለህዝብና ለዓለም ቁልጭ አድርጎ ማሳየት ነው፡፡እስከ መቼ በምርጫ መጭበርበር !

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !


የማለዳ ወግ …የተዘጋውን የአረብ ሀገራት የኮንትራት ሰራተኛ አቅርቦትን ለመክፈት የወጣው ረቂቅ ! (ነቢዩ ሲራክ)

$
0
0
* ስለ ሰራተኞች መብት ጥበቃ መነሳቱ አልተዘገበም
* በተወያይ ኤጀንሲዎች በኩል ግን ረቂቁ ውዝግብ አስነስቷል
* ከዚህ ቀደም ያለ በኮንትራት ለተበተኑትስ ዜጎችስ ምን ታስቧል ?Nebiyu Sirak አዲሱን መረጃ ያገኘሁት ሃገር ቤት ከሚታተመው ከአድማስ ጋዜጣ ላይ ነው ፣ እንዲህ ይላል ” ወደ አረብ አገራት የሚሄዱ ሰራተኞች ላይ የሚደርሰውን ችግርና እንግልት ለማስቀረት በሚል ከአንድ ዓመት በላይ ተቋርጦ የቆየውን አሰራር ለማስጀመርና ለመቆጣጠር የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ውዝግብ አስነሳ፡፡ ”  … ወረድ ብለን ዝርዝር መረጃውን ስንቃኝ በዋናነት መታየት ያለበት አንኳሩ የሰራተኞች ይዞታና የመብት ጥበቃ ጉዳይ በዘገባው ላይ አልተካተተም። ይህም ይሁን ብለን ዝርዝሩን ስንቃኝ ከዚህ ቀደም በነጻ ያገኙትን ቪዛ በደላላ በየገጠር ከተሞች ሰብስበው እህቶቻችንን ከመላካቸው አስቀድሞ ፈቃድ ሲያወጡ ለመንግስት ያቀረቡት የገንዘብ መያዣ በደል ደርሶባቸው ለሚመለሱ ዜጎች ካሳ ሲከፈል አላየንም አልሰማንም ። ከሁሉም የሚያመው ሰራተኞች ሲላኩ ለሚደርስባቸው አደጋ  ኢንሹራን ሳይቀር ገንዘብ አስከፍለው የላኳቸው ቢሆንም በተበደሉበት በደል ተፈጽሞባቸው ሃገር ቤት ሲገቡ በከፈሉት ኢንሹራን ተጠቃሚ አይደረጉም። የሰራተኞችን መብት አሟልተው ስራ ለማሰማራት እንግዲህ ውል ገብተው በወሰዱት ፈቃድ ልክ ውል ሲያፈርሱ ህግ አስፈጻሚ አካላት በኩል በዝምታ የታለፉት የእኛ ስራና ሰራተኛ አገናኝ ደላላ “ኤጀንሲዎች ”  በአዲሱ ረቂቅ ያነሱት ተቃውሞ ” ቅድመ ሁኔታዎች አያሰሩንም” የሚል መሆኑን እያመመኝ አነበብኩት!  እንቀጥል …በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ሰራተኞችን የሚልኩ ኤጀንሲዎች ያሰሙት ቅሬታ የስራ ፈቃዱን ለማግኘት ” ከአንድ ሚሊዮን እስከ አምስት ሚሊዮን ብር ካፒታል ሊኖረው ይገባል ” መባሉና “ለሰራተኛው መብትና ደህንነት ዋስትና ማስከበሪያ የሚውል 100 ሺህ ዶላር ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ በዝግ ሂሳብ የማስቀመጥ ግዴታ አለበት ” መባሉ ነው ። ጋዜጣው ኤጀንሲዎች ለስራ ወደ ውጭ አገር የላኳቸውን ሰራተኞች በሚሔዱባቸው ሃገራት ላሉ ኢንባሲና ቆንስል መስሪያ ቤቶች በ15 ቀናት እንደሚያስታውቁ ይጠቁማል ።

የኤጀንሲዎች የአዞ እንባ …

ኤጀንሲዎች  ይህ መሰሉ ረቂቅ ህግ እንደማያሰራቸው እንዲያውም “በውጭ ሃገር ስራ ለማሰማራት የሚፈልጉትን ዜጎች እድል ያጠባል ፣ ህገ ወጥነትን የሚያባብስ ነው ” ሲሉ ህመሙን የመከረኞቹ ህመም በማድረግ የአዞ እንባ የማንባት አይነት ቅሬታ መሰማታቸውን በአድማስ ጋዜጣ ዘገባ ተጠቅሷል ። እንደ ጋዜጣው ዘገባ ኤጀንሲዎች ረቂቁን ህግ በወይይቱ የተቃወሙበትና ያልደገፉበት ዋንኛ ምክንያታቸው የተደነገገውን ቅድመ ሁኔታ ለማሟላት እንደሚከብድ መሆኑንም ጋዜጣው ያስረዳል ።

ዳግም እንዳናነባ …!

ከወራት በፊት ጀምሮ “ወደ አረብ ሃገራት የተዘጋው የኮንትራት ቪዛ ይከፈታል !” የሚል መረጃ በሰፊው በመሰራጨት ላይ እንዳለ በሹክሹክታ ከሰማን ወዲህ ረቂቁ ለውይይት መቅረቡን ይህው ሰማን ። ከዚሁ ጋር ባያያዝኩት የ EBC TV ዘገባ እንደ ምትመለከቱት የዜና ዘገባ ከወራት በፊት የተባበሩት ኢምሬትን የጎበኙት ፕሬዘደንት ዶር ሙላትና የኢምሬት አምባሳድር አቶ አብድልቃድር የተዘጋውን የአረብ መንገድ መቸ እንደሚከፈት ተጠይቀው ሲመልሱ  ህግ ሆነ መመሪያ እየወጣ መሆኑን ጠቁመው ነበር ። ከዚህ ጋር በማያያዝ በሰጡት መግለጫም ከአሁን ቀደም  ከአረብ ሃገራት ጋር ያልነበረው የሁለትዮሽ ስምምነት በቀጣይ መከወን እንዳለበት ገልጸውም ነበር ። ይህ መግለጫ በተነገረ ማግስት በቪዛው ንግድ ተሰማርተው ከገጠር እስከ ከተማ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ እህቶቻችን ለሳውዲ ” ገበያ”  ያቀረቡት ባለ ኤጀንሲ ደላሎች ጅዳና ሪያድ መምጣት መጀመራቸው መረጃ ቢጤ አቅርቤም ነበር  ።  አሁን በውስጥ አዋቂዎች የሰማነው ፣ የተባለው ሁሉ  እውን እየሆነ ፣ እውነቱ እየጠራ የሄደ ይመስላል  !

ከዚህ ቀደም በሁለት ሃገራት መካከል ስምምነትና በቂ ዝግጅት ሳይደረግ በሳውዲ ብቻ ከግማሽ ሚሊዮን የሚበልጥ ዜጋ  የህግ ሽፋን ህጋዊ ፈቃድ ባላቸው ኤጀንሲዎች በየገጠር ከተሞች ተግዘው በተለያዩ ከተሞች ተበትነዋል። ዛሬ በኮንትራት የመጡት ” ያሉበትን ይዞታ እንዲህ ነው” ብሎ መረጃ መስጠት ቀርቶ ፣ የትና በምን ሁኔታ እንደሚገኙ የሚያውቁ ኤጀንሲዎችም ሆነየ የመንግስት ተወካዮች የሉንም የምለው በእርግጠኝነት ነው ።  በተደጋጋሚ ከሚደርሱኝ መረጃዎች መረዳት እንደ ቻልኩት በአሁኑ ሰዓት መግቢያ መውጫው ጠፍቶባቸው ፣ በደልን እያስተናገዱ የሚንገላቱት በርካታ እህቶች በየቤቱ እንዳሉ አውቃለሁ።  በዚህ መሰሉ የተወሳሰበ ችግር ዜጎች እየተሰቃዩ ፣  መብታቸው የሚያስጠበቅ ስራ እየተሰራ በሌለበት ሁኔታ ሌላ እንባ ልናነባ የተቃረብን ይመስላል !  የኮንትራት ሰራተኞችን አበሳ ብዙ ነው፣  የሚሰራው ታስቦና ተጠንቶ ስላልሆነ ፣ መብታችን የሚያስጠበቅልን ስለጠፋ ተዋርደናል ። አሁን ድረስ በዚህ ዙሪያ ያገባናል ብለን  ስንጽፍና ስንናገረው እንደ ተቃዋሚ እየታየንም ቢሆን ግፍ ሰቆቃና ስቃዩን ሊያሰለች በሚችል ስፋትና ጥልቀት ጽፈነዋል ፣ ተናግረናል!  ሰሚ ግን የለም !

በህግ መመሪያ የተቀመጠው የመንግስት ዲፕላማቶች ቀዳሚ ስራ ባሉበት ሃገር የሚገኙ ህጋዊም ሆኑ ህገ ወጥ ዜጎችን ሰብአዊ መብት ረገጣ እንዳይደርስባቸው መከላከል ቢሆንም ይህ እተሰራበት አይደለም።  የህገ ወጦችን ቀርቶ በኮንትራት ሰራተኛና አሰሪ ስምምነት የመጡ ዜጎችን  መብት ማስከበር አልቻሉም ! የቪዛ ውል ማስፈጸሚያ ገንዘብ እየሰበሰቡ ባጸደቁት የኮንትራት የስራ ውል ላይ የተጻፉት ስምምነቶች የዜጎች  ይዞታ የመከታተልና የማስፈጸም ሃላፊነትን ሲወጡ አላየንም !እውነቱ ይህ በመሆኑ ሰብዕናችን መርከስ ይዟል ፣  ግፍ እየተፈጸብን ነው ። በዚህ ሁኔታ ረቂቁ ጸድቆና በተግባር ውሎ ዳግም እንዳናነባ ያሰጋል  !
ግልድ መሆን ያለበት ነባራዊው እውነታ …የረቂቁ ጉዳይ በእንዲህ እንዳለ ከኢትዮጵያ መንግስት አስቀድሞ ከኢትዮጵየ የኮንትራት ሰራተኞች እንዳይመጡ ያገደው የሳውዲ መንግስት እገዳውን እስካሁን አላነሳም። በዚህ ላይ መንግስት ከአረብ ሃገራት በኩል እግዱ ተነስቶ ሰራተኞች እንዲያቀርብ ጥያቄ እየቀረበለት መሆኑን ደጋግመን ሰምተናል ። ከአረቦች በኩል ግን የምንሰማው ለየቅል ነው !ወደ ረቂቁ ስንመለስ ፣  ብዙዎቻችን የሚያሳስበን በማህበራዊና ሰራተኛ ሚኒስትር ለኤጀንሲዊች ውይይት የቀረበው ረቂቅ ህግ በሰራተኞች ይዞታና መብት ጥበቃ ዙሪያ የተነሳ ጉዳይ አለመኖሩም ነው ። በአድማስ ጋዜጣ ጋዜጣ ዘገባ በማህበራዊና ሰራተኛ ሚኒስትር በቀረበው ረቂቅ ኤጀንሲዎች መወያየታቸውን ሲያስረዳ ፍቃድ ለመውሰድ የተጣለባቸውን ከፍተኛ ገንዘብ የማስያዝ ፣ ሰለሰራተኞች እድሜ የትምህርት ደረጃ ገደብ እና ሰራተኞችን በሚሄዱበት ሃገር ኢንባሲና ቆንሰል መ/ቤት በ 15 ቀን ውስጥ ከማስመዝገብ ቅድመ ሁኔታ ያለፈ አለመወያየታቸውን የቀረበው ዘገባ ያስረዳል ።

በረቂቁ ላይ ሰራተኞች ቢያንስ እስከ ስምንተኛ ክፍል በላይ የሆኑት ብቻ እንደሚያካትት ከመጠቆሙ ባለፈ ሰራተኞች ማግኘት ስላለባቸው በቂ ስልጠናና ተዛማጅ ቅድመ ዝግጅት በቀረበው ረቂቅ ቀርቦ ለውይይት አለመደረጉ ያሳስባል።  ከዚህ ቀደም ድህነትና የኑሮ ውድነቱን ተከትሎ በልጆቻቸው ህይወታቸውን ለመለወጥ የቋመጡ ወላጆች በደላሎች ቀቢጸ ተስፋ ተታልለውና የተሳሳተ የእድሜና የትምህርት መረጃና  የመጓጓዣ ሰነድ አቅርበው ከሃገር እንዳይወጡ የተሰራውን ስራ የሚከላከል ዘዴ በረቂቁ አልቀረበም።  አለም አቀፍ የሰራተኛ ህግንና ሰብአዊ መብት ማስከበሪያ ድንጋጌዎችን ባገናዘበ መልኩ ሰራተኞች ስለሚከፈላቸው ክፍያ ፣ ስለጤና ፣ ስለ እረፍት ሰአታቸው እና ስለመሳሰሉት መሰረታዊ የኮንትራት ሰራተኞች አንገብጋቢ ጥያቄዎች  ውይይት ሳይደረግበት ስለኤጀንሲዎች ፈቃድ ማግኘት ቅድመ ሁኔታ ውይይት መቅረቡ ያሳስባል። በረቂቁ ውይይት ከመደረጉ አስቀድሞ ኤጀንሲዎች  ከዚህ በፊት ስላቨጋገሯቸው ዜጎች ነባራዊ ይዞታና ሁኔታ ፣ አድራሻና ያሉበትን ሁኔታ በዝርዝር መረጃ አላቀረቡም። በላኳቸው ሰራተኞች ላይ ለተፈመውና እየተፈጸመ ላለው በደል ተጠያቂው ሳይታወቅ ስለመጭው ፈቃድ አወጣጥ ከኤጀንሲዎች ጋር በረቂቁ ዙሪያና መስፈርት ዙሪያ  መወያየቱ ጠቃሚ አይመስለኝም።

የኮንትራት ሰራተኞች ጉዳይ ሲነሳ በየአረብ ሃገራት ያሉትን ኢንባሲና ቆንስል መስሪያ ቤቶች ለዜጎች በሚሰጡት ያልተሟላ ግልጋሎትና ያልሰመረ የመብት ማስጠበቅ ይጠቀሳል። ይህ ለምን ሆነ ሲባሉ የሰራተኛና በበጀት እጥረት እንዳለባቸው አዘውትረው ይናገራሉ። በዚህ  መንገድ አሁን ድረስ ስለሚንከላወሱት የኢንባሲና የቆንስል መ/ቤቶች ረቂቁ ምን ይላል ? የሚለው እንዳለ ሆኖ በሃገር ቤት ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ዝግጅት ፣ ኃላፊነትና ተጠያቂነት በረቂቁ ውይይት አልተነሳም።

…እልፍ አእላፍ የኮንትራት ሰራተኞች አሁን ያሉበት ይዞታ በውል ሳይመረመርና ሳይታወቅ እየተንገዋለለ ባለበት ሁኔታ  የተዘጋውን ለመክፈት ሂደት ግልጥልጥ አለማለት  ያስፈራል። ከዚህ በፊት በኮንትራት የገቡት ጉዳይ ገለል አድርጎ ስለ አዲሱ ህግና መመሪያ እንነጋገር መባል ችግሩን ያገዝፈዋል እንጅ አይቀርፈውም ። ይፋ መውጣት የጀመረው ረቂቁ ህግና በዚህ ጫፍ ያለው  ዝግጅት የተዳከመ አለያም የለም የሚባል አይነት መሆኑ አሁንም የዜጎችን አበሳ በቅርብ ለምንመለከተ ውን  ዜጎች ያሳስበናል። መፍትሄው በአረብ ሃገራት ያሉትን ዜጎች ጨምሮ  የሁሉም ባለድርሻ አካላት በረቂቁ ህግ ተሳትፎ ሊያደርጉበት ይገባል። በፈለገው መንገድም ይሁን በረቂቁ ህግና መመሪያ ዙሪያ ግልጽና ጥልቅ ውይይት ካልተደረገ አሁንም ዳግም እንደምናነባ ልብ  ያለው ልብ ይበል  !

ጄሮ ያለው ይስማ  !

ቸር ያሰማል  !

ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 24 ቀን 2007 ዓም

 

“ለመተማመን እንነጋገር!” ኢትዮጵያውያን “ከዘረኝነት ይልቅ ለሰብዓዊነት” ቅድሚያ ሰጡ!

$
0
0

 

smneበቅርቡ በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ አካባቢ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በአገራችን ውስጥ ስላለው ችግር መፍትሔ ለማምጣት ይጠቅማል በሚል በጠራው ውይይት ላይ ኢትዮጵያውያን ከአውሮጳ፣ ከአሜሪካና ከካናዳ ተጠራርተው በመምጣት በዓይነቱ ለየት ያለ ውይይት አድርገዋል፡፡ “ሰላም፣ ፍትሕ፣ ዕርቅና መከባበር የሰፈነበት ማኅበረሰብ ለመመሥረት” አንዳችን ስለሌላችን በመናገር ሳይሆን እርስበርስ ስለችግራችን መወያየት አለብን በሚል መሪ ሃሳብ ኢትዮጵያውያኑ ግልጽና በቅንነት ላይ የተመሰረተ ውይይት አካሂደዋል፡፡ “ከዘረኝነት ይልቅ ለሰብዓዊነት ቅድሚያ” የመስጠት አስፈላጊነትም በስፋት ውይይት የተደረገበት ጉዳይ ነበር፡፡

በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ኤምባሲ የስብሰባው አካል እንዲሆን ለአምባሳደር ግርማ ብሩየንቅናቄው ዋና ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ የላኩ ቢሆንም ከኤምባሲው በኩል የተሰጠ ምላሽም ሆነ በውክልና በስብሰባው ላይ የተገኘ አለመኖሩ በጋዜጣዊው መግለጫ ተወስቷል፡፡ የመግለጫው ሙሉ ቃል ከዚህ በታች ቀርቧል፡

 [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—–

 

 

”ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች!”–ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት (የጉዳያችን ማስታወሻ)

$
0
0

እናት አርበኞች

”ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች” ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ሰሞኑን ፓርቲው እና ዘጠኙ አጋር ፓርቲዎች በጋራ በጠሩት በመጪው ቅዳሜ እና ዕሁድ (ህዳር 26 እና 27/2007 ዓም) በአዲስ አበባ የተጠራውን የ 24 ሰዓት የተቃውሞ ሰልፍ አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የተናገሩት ንግግር ነው።

ይህ ንግግር አሁን ላለው ትውልድም ሆነ በኢትዮጵያዊነቱ ለሚያምነው ሁሉ ከሰማይ የገዘፈ፣ ሲያስቡት በትንሿ አእምሯችን ልንሸከመው የሚከብድ ግን ከእውነትም በላይ የሆነ እውነት ነው።
arebegnoch
ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ካቆሟት ነገሮች ውስጥ አንዱ ለዘመናት የኖረው ሕግ ነው።ዓለም እንደ ዛሬው ስለ ሕግ ብዙ ሳይናገር በቤተ መንግስቱ እና በሕዝቡ መካከል የሚያገናኙ ሕጎች ነበሩ።የተበደለ ፍትህ የሚያገኝበት፣አቤት የሚልበት ቦታ ነበረው።በዳኝነት የተቀመጠውም ህሊናውን እና አምላኩን የሚፈራበት መመዘኛ ነበረው።ፍፁምነት በእራሱ ከሰው ልጅ ባይጠበቅም እንደ ማህበረሰብ፣እንደ ሕዝብ እና እንደ መንግስት ኢትዮጵያ እና ህዝቧ ለሺህ ዓመታት ሲዳኝ የኖረው ከፈረንሳይ ሀገር በመጣ ወይንም ከእንግሊዝ በመጣ ሕግ አይደለም። ሃይማኖታዊ መሰረቱን በያዘ፣ህሊናን እና ህዝብን ታሳቢ ያደረገ ሕግ እና ፍርድ ለዘመናት አኑረውናል።

ይህንን ሕግ እና በነፃነት የመኖር ፀጋን አባቶቻችን በነፃ አላገኙትም።ወጥተው እና ወርደው ደምተው እና ቆስለው ያቆዩት እኛነታችን ነው።ለእዚህ ነው ዛሬ ላይ ሆነን ለነገ ለማስተካከልም ሆነ የምናወራው ስለ ምን ዓይነቷ ኢትዮጵያ እንደሆነ ለማስታወስ ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት ሀገር መሆኗን ለአፍታም አለመርሳቱ ተገቢ የሚያደርገው።ብዙ የተደከመባት ብቻ አይደለም ብዙ ታላልቅ ሰዎች የተሰዉላት ሀገር ነች።ኢንጅነር ይልቃል ያስታወሱን እኔም በአምሮዬ ሲመላለስ የከረመው አረፍተነገር ይህ ነው።

ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች

ኢትዮጵያ ንግስት ሳባ በሴት አቅሟ በረሃ ለበረሃ ተንከራታ ኢየሩሳሌም ድረስ ሄዳ ታቦተ ፅዮንን ያመጣችላት ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ ንጉስ ካሌብ እስከ የመን የሀገሩን ስም ይዞ ሄዶ በባርነት የተያዙትን ናግራውያንን ነፃ ያወጣባት ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ የመሐመድ ቤተሰቦች ተሰደው በክብር ተቀብላ መጠለያ ሰጥታ እስልምና ሃይማኖትን ለዛሬ አማኝ የሰው ልጆች በሙሉ ከመጥፋቱ በፊት የታደገች ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ በዘመነ ዮዲት (ጉዲት) ለአርባ ዓመት የመከራ ዶፍ ሲወርድባት ከመከራው ጋር የነደዱ፣በእሳት የተቃጠሉ፣በጦር የተወጉ ለሀገራቸው እና ለህዝባቸው ክብር በሰይፍ የተቀሉ ጀግኖች የሞቱባት ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ ክብር ፣ለሌሎች ነፃነት እና ለእምነታቸው ፅናት የተጉ እነ አፄ ዳዊት፣ነገስታቷ ግብፅ ያሉ ህዝቦች ተጨቆኑ ብለው በሱዳን በረሃ ተንከራተው የግብፅን ሕዝብ ከመከራ የታደጉ ሲመለሱም የክርስቶስን መስቀል ይዘው የተመለሱ በመንገዳቸው መከራ ህመምን ታቅፈው ሀገራቸው ድንበር ላይ የሞቱባት ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ ባዕዳን እንግሊዞች ሀገራችውን እና ወገናቸውን በከዱ ባንዳዎች እየተመሩ ሲመጡ እጅ አልሰጥም፣ኢትዮጵያን መሳቅያ አላደርግም ብለው የገዛ ሽጉጣቸውን ጠጥተው የሞቱባት አፄ ቴዎድሮስ የተሰዉላት ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ ራስ አሉላ ”ፈረሴ የቀይ ባህርን ውሃ ሳይጠጣ አይመለስም” ብለው በባህረ ነጋሽ በረሃዎች ተንከራተው የሀገራቸውን ክብር ያስጠበቁ የተሰዉላት ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።
ኢትዮጵያ አፍሪካን በጠረንጴዛ ዙርያ ተሰብስበው ለመቀራመት ከተስማሙ በኃላ ሊወራት የመጣውን ጣልያንን ለመዋጋት ለወራት በእግራቸው እስከ አድዋ ድረስ ተጉዘው መስዋዕት የተቀበሉባት ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ ኢጣልያ ዳግም በ1928 ዓም ሲወራት ከሊቅ እስከ ደቂቅ በረሃ ለበርሃ ተንከራተው ከውስጥ አርበኛ እስከ ዓለም አቀፍ ሙግት ገብተው፣ከጳጳሳቷ እስከ ሕፃን ሰማዕት የሆኑባት፣በአዲስ አበባ በየካቲት 12 ቀን ብቻ ከአስር ሺህ በላይ የንፁሃን ደም በአካፋ እና በዶማ ጭምር የፈሰሰባት ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ እነ ሞገስ አስገዶም እና አብርሃም ደቦጭ በአርበኝነታቸው ተይዘው ጥፍራቸው እየተነቀለ ተሰቃይተው የሞቱላት ሀገር ነች ኢትዮጵያ።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

Ethiopians on Sunday celebrated the 118th anniversary of the Adowa battle when an untrained Ethiopian army routed a better equipped Italian invasion army. Photo Credit: Turkish Press

Ethiopians on Sunday celebrated the 118th anniversary of the Adowa battle when an untrained Ethiopian army routed a better equipped Italian invasion army.
Photo Credit: Turkish Press


ኢትዮጵያ በሮም ጣልያን አደባባይ ጎራዴ መዘው የጣልያንን ፋሽትትን የቀሉ በመጨረሻም ለሞት ሰማዕት የሆነላት ዘርአይ ድረስን ያበቀለች ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ ከጣልያን እስር ቤት አምልጦ በገዛ የጣልያን በረሃ ሸፍቶ ፋሽትን ያርበደበደ በመጨረሻም በድል የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ እያውለበለበ ሮም የገባ እና ከአዲሱ የጣልያን ፕሬዝዳንት የገዛ የእጅ ሰዓታቸውን አውልቀው የሸለሙት ጀግና አብዲሳ አጋን ያፈራች ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ የተሻለ አስተዳደር ያስፈልጋታል።ብለው እራሳቸውን የሰጡ ጀግና የጦር ኃይል አባላት እነ ጀኔራል መንግስቱ ንዋይ እና ገርማሜ ንዋይ በስቅላት አንገታቸውን ለገመድ የሰጡላት ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ አሁንም የተሻለ አስተዳደር ያስፈልጋታል፣”ሕዝባዊ መንግስት አሁኑኑ!” ያሉ በሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች ለሞት እራሳቸውን የሰጡባት ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ የዚያድባሬ ሱማልያ ”ቁርስ ድሬዳዋ፣ምሳ አዲስ አበባ” ብላ በምትፎክርበት ወቅት ከሶስት መቶ ሺህ በላይ ወዶ ዘማች ባጭር ጊዜ ለኢትዮጵያ እሞትላታለሁ ብለው የተሰለፉላት እና ሺዎች በፈንጅ ላይ እየተራመዱ ሞተው ሀገራቸውን ለክብር ያበቁ ዜጎች የወለደች ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ አንድነቷ አይናጋም፣አትቆራረስም፣በጎሳ እና በዘር አትከፋፈልም ብለው ሰማዕት የሆኑላት እንደ ምፅዋ በነበረው የእርስ በርስ ውግያ ሳንጃ በሳንጃ እየተሞሻለቁ ከአፈር የተደባለቁላት ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

ኢትዮጵያ አሁንም ከአምባገነናዊ አገዛዝ ትላቀቅ ብለው ተነስተው በመጨረሻ ሰንደቅ አላማዋን ተጠቅልለው በመከላከያ ሚኒስትር ቢሮ ውስጥ የተሰዉላት እነ ጀነራል መርድን፣በሰሜን እኔ ብ/ጄነራል ደምሴ ቡልቱን፣ኮለኔል ታሪኩን ያፈራች መሬት ነች።ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች።

አዎን ! ዛሬ በጎሳ እና በከፋፋይ አገዛዝ እጅ ወድቃ ብትቆስልም ኢትዮጵያ ብዙ ደም የፈሰሰላት፣ብዙዎች የደከሙላት ወደፊትም የሚደክሙላት ሀገር ነች።ዛሬ ኢትዮጵያን ስናስብ ይህንን ሁሉ ድካም እና እንደጎርፍ የፈሰሰው ደም ሊታወሰን ይገባል።

ይህንን ሁሉ ነው የኢንጅነር ይልቃል ንግግር ያስታወሰኝ።ይህንን ስናስብ ነው በሀገራችን ምን ያህል እንደቀለድን ሀገራችንን ለአልባሌ እዚህ ግባ ለማይባል ዘረኛ ቡድን ሰጥተን ግማሾቻችን ለስደት የቀረነው ለህሊና እስረኝነት መዳረጋችን የሚያንገበግበው።

አዎ እያወራን ያለነው ስለ ኢትዮጵያ ብዙ ስለተደከመላት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች ስለተሰዉላት ሀገር ነው።አዎን!! ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች! ይህ ትውልድ የሀገሩን ክብር ማስመለስ ያለበት ወሳኝ ጊዜ ላይ ነው።ሁሉ እንጀራ ጋጋሪ አይሆንም።ሁሉም ወጥ አይሰራም።ባለን በችሎታችን ለሀገራችን ካልሰራን ከሞቱት አንሰናል።ብዙዎች የደከሙላት እና የሞቱላት ሀገር ላይ ቸል የማለት መብት የለንም።

ጉዳያችን
ህዳር 24/2007 ዓም (ደሴምበር 3/2014)

ከ5 ሚሊዮን የማያንሰው ዐማራ ዬት ደረሰ?

$
0
0

moreshየትግሬ-ወያኔ ለ17 ዓመታት በሽፍትነት፣ ለ23 ዓመታት ደግሞ በገዢነት ተፈናጦ በዐማራ ሕዝብ ባደረሰው የዘር ማጽዳት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ ምን ያህል ንፁሃን ዐማሮች እንደተጨፈጨፉ የተለያዩ አስተያዬቶች ሲደመጡ ቆይተዋል። ሞረሽ ወገኔ ባደረገው ዝርዝር የሕዝብ ብዛት ቆጠራ ትንተና መሠረት ከ1983ዓ.ም. ወዲህ ደብዛቸው ከምድረ-ገፅ እንዲጠፉ የተደረጉት ዐማሮች ብዛት ከ5 ሚሊዮን እንደማያንስ ይጠቁማል። ይህ ምንን ያመለክታል? ከጥናቱ ውጤት የሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ጎልተው ይወጣሉ።

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው አገር አቀፍ ብሔራዊ የሕዝብ ቆጠራ የተካሄደው በ1976 ዓ.ም. ነበር። በወቅቱ ኤርትራን እና የአሰብ አስተዳደርን ጨምሮ ጠቅላላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ብዛት 42,616,876 ያህል ነበር። በኤርትራ እና በአሰብ አስተዳደር ኗሪ የነበሩት ዜጎች ቁጥር ሲቀነስ በቀሪዋ ኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ሕዝብ ብዛት 39,868,572 ይሆናል። በወቅቱ በሕዝብ ብዛት አንደኛ የነበረው የኦሮሞ ነገድ ብዛቱም 12,387,664 ሲሆን፤ እንዲሁም ዐማራ በሁለተኛ ደረጃ12,055,250 ያህል ተወላጆች ነበሯቸው። ስለሆነም በወቅቱ በሁለቱ ነገዶች ተወላጆች ብዛት መካከል የነበረው የቁጥር ልዩነት 332,414 ይሆናል ማለት ነው። የመጀመሪያው የሕዝብ ቆጠራ ከተደረገ ከ23 ዓመታት በኋላ፣ ማለትም በ1999 ዓ.ም. በተደረገው ሦሥተኛው የሕዝብ ቆጠራ ውጤት መሠረት ዐማራው ቁጥሩ በአዝጋሚ ሁኔታ ወደ 19,867,817 ሲጨምር የኦሮሞዎቹ ብዛት ግን ከእጥፍ በላይ አድጎ ወደ 25,488,344 ደርሷል። ስለዚህ በኦሮሞ እና ዐማራ ተወላጆች ብዛት መካከል ያለው የቁጥር ልዩነት 5,620,527 አሻቅቧል ማለት ነው። በዐማራው እና በኦሮሞው መካከል የነበረው የቁጥር ልዩነት ተመጣጣኝነት እንዳለ እንደተጠበቀ ይቀጥል ቢባል እንኳን ከ23 ዓመታት በኋላ ሊኖር የሚችለው ልዩነት ከ664,828 አይበልጥም። በመሆኑም ከ5ሚሊዮን የማያንሰውን ዐማራ ዬት እንዳደረሱት የሚያውቁት የትግሬ-ወያኔዎች እና ሎሌዎቻቸው ናቸው።

ባለፉት 23 ዓመታት ከ4,751,333 በላይ የዐማራ ነገድ ተወላጅ የጠፋው ወያኔ ገና የትጥቅ ትግል ሲጀምር «የትግራይ ሕዝብ ደመኛ ጠላት ዐማራ ነው፤» « ዐማራን፣ የአማርኛ ቋንቋን እና የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖትን ማጥፋት አለብን!» ብለው የተሰለፉ በመሆናቸው የዐማራውን ነገድ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ በመግደላቸው ነው። በግልፅ እንደሚታወቀው ወያኔ የዐማራውን ነገድ በሚከተሉት ሥልቶች አጥፍቷል። እያጠፋም ነው፥

  • በተለያዩ ሰበቦች በጅምላ በመግደል፦ በወልቃይት፣ በጠገዴ፣ በጠለምት፣ በሠቲት፣ በአርማጭሆ፣ በራያ ሕዝብ ላይ የፈፀሙት የግፍ ግድያ፣
  • በአሰቦት ገዳም፣ በአርባ ጉጉ፣ በወተር፣ በበደኖ በሌሎችም የሐረርጌ እና አርሲ አካባቢዎች ይኖሩ በነበሩ ዐማሮች ላይ የፈፀሙት የግፍ ጭፍጨፋ፤
  • በወለጋ፣ በኢሉባቡር፣ በጅማ ያካሄዷቸው ዐማራን በጅምላ የመግደል ዘመቻዎች፤
  • ከ1983 -1987 ዓ.ም. ድረስ በሕወሓት ሠራዊት አማካይነት በሸዋ፣ በወሎ፣ በጎጃም እና በጎንደር ኗሪ በሆኑ ዐማሮች ላይ የ«ሽፍታ ምንጠራ» እና «ብረት ማስፈታት» የሚሉ የሽፋን ዘመቻዎች በማካሄድ በፈፀሟቸው ጭፍጨፋዎች፤
  • ዐማራውን በተለያዩ ተፅዕኖዎች በማስፈራራት ዐማራነቱን ክዶ የሌላ የነገድ ማንነት እንዲቀበል በማስገደዳቸው፤
  • ዐማራውን እየለዩ ከሥራ በማባረር በርሃብ በመጨረሳቸው፤
  • «የመሬት ድልድል» በሚሉት እና ዐማራን «መሬት አልባ የትግሬ-ወያኔ ጭሰኛ» ለማድረግ በቀየሱት ፖሊሲ ዐማራው ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ተለይቶ በየትኛውም የአገሪቱ ክፍል አርሶ እና ሠርቶ እንዳይኖር በማድረጋቸው፤
  • ነባሩን የወባ መከላከያ ድርጅት ዘግቶ ድርጅቱን ወደ ትግራይ በማዛወር የዐማራውን ነገድ ተወላጆች የወባ መከላካያ አገልግሎት በማሳጣት አያሌ ዜጎች እንዲያልቁ በማድረጋቸው፣ በተለይም በጎጃም ሕዝብ ላይ ከ1985-1989 ዓ.ም. ያደረሱት እልቂት በምሣሌነት ይጠቀሣል፤
  • የዐማራውን ነገድ ተወላጆች በዘር ጠላትነት ፈርጀው የኤች.አይ.ቪ./ኤድስ ቫይረስን በመርፌ በማስተላለፍ በገፍ እንዲያልቁ በማድረጋቸው፤
  • የዐማራውን ተወላጆች መሠረታዊ የጤና አገልግሎት በመንፈግ በተለያዩ ተላላፊ በሽታዎች እንዲያልቁ በማድረጋቸው፤
  • በወሊድ ቁጥጥር ስም የነገዱን አባሎች መካንና ታማሚ በማድረጋቸው፤
  • ከዐማራ የጸዱ ክልሎችን ለመፍጠር በተያያዙት የዘር ማፅዳት ዘመቻ «ኦሮሚያ፣ ደቡብ ብሔር-ብሔረሰቦች፣ ቤንሻንጉል-ጉምዝ፣ ጋምቤላ፣ አፋር እና ሶማሌ» ብለው በከለሏቸው «ባንቱስታን-መሠል» ግዛቶች ይኖሩ የነበሩት ዐማሮችን በግፍ እና በገፍ በማባረር፣ በመግደልና በመደብደብ ለተደራራቢ ችግሮች በማጋለጣቸው፤

ለዐማራው ነገድ ቁጥር መቀነስ ዋና እና ተያያዥ ምክንያቶች ናቸው። ስለሆነም ያለምንም ማወላወል የዐማራው ነገድ በትግሬ-ወያኔ በተከፈተበት የማያባራ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ዘመቻ ሰለባ መሆኑን ትውልዱ ሊገነዘበው ይገባል።

በተለይ ለዐማራው ነገድ ተወላጆች እና ለሃቀኛ ኢትዮጵያውያን የቀረበ ጥሪ፦

ይህን መረጃ በማባዛት ለዓለም ሕዝብ ባሉት የመገናኛ መሣሪያዎች በመጠቀም በማሰራጨት፣ ሆን ተብሎ የዘር ማጥፋት ወንጀል ለተፈጸመበት የዐማራ ነገድ ድምፅ ልንሆን ይገባል። ለተበደሉ እና የመኖር ሰብአዊ መብት ለተነፈጋቸው ሰብአዊ ፍጡሮች ድምፅ መሆን ዘረኝነት ወይም ጠባብነት አይደለም። በመሆኑም የዐማራው ተወላጆች ብቻ ሣይሆኑ፤ ለሰብአዊነት የቆሙ ሁሉ ለዚህ ነገድ ድምፅ ከመሆን አልፈው፣ በኢትዮጵያውያን ላይ ይህን ዓይነት የከፋ ወንጀል የሚፈፅሙትን ለፍትኅ አደባባይ ለማቅረብ ለተያያዝነው ትግል፥ የመረጃ፣ የምክር፣ የዕውቀት እና የገንዘብ ልገሣ እንድታደርጉልን በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

 

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!

የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት ዳግም ትንሣዔ በቆራጥ ልጆቿ ተጋድሎ ዕውን ይሆናል!

ብሔራዊ ደዌአችን በፈውስ ዋዜማ ላይ ይሆን?

$
0
0

ከሚካኤል ዲኖ

ይህ ፅሁፍ በጥልቅ ጨለማ ውስጥ ከወደቀ መንፈስ የፈለቀ ነው፡፡ በዓለሙ ሁሉ የሚከናወነው ግፍና በደል እንዲሁም የሰብዓዊነት መጣጣል እለት በእለት ወደ ጥልቁ ከሚደቀፅቃት መድረሻ ቢስ ስንኩል ነፍስ በጣር ወደህዋው የተወነጨ በህቅታ የታጀበ እውነት ነው፡፡
hana and sayat

ምስኪኗ ሀና
አንቺ የዓፉዐን ናሙና
ወግቶኛል ህመምሽ
ቆጥቀቁጦኛል እንባሽ
አምናለሁ
ፍርድ ከላይ ነው
ግምድል ነው ከታች ያለው
አምናለሁ
አካልሽ ቢዝልም በርኩሳን ሥራ
ነፍስሽ ግን ታርፋለች በቅዱሳን ስፍራ›

በርትራንድ ረስል «ማኅበረሰብ ያለሴተኛ አዳሪ መኖር አይችልም» ይላል አስቀያሚ እውነት ነው፤ በሌላ መልኩ ሰው ሀጥያት ሳይሰራ ሊኖር አይችልም ማለትም ነው፡፡ የኛ ማህበራዊ ተራክቦም ከዚህ እውነታ አያፈነግጥም፡፡ በአስፈሪ ሁኔታ እየተንኮታኮተ ለሚገኘው የስነ- ምግባር ምሰሷችን አይነተኛ ማሳያ ለመሆኑ ምስክር የሚያሻው አይመስለኝም፡፡ ‹‹ሀይማኖተኛ ነኝ›› እያለ በሚመፃደቀው ሕዝባችን መሃል በስውር ህልውና ይንሳፈፍ የነበረው የዝሙት ተግባር ጨለማን ተተግኖ መሬት ከመርገጥ አልፎ በቀን ብርሃን በተለያየ ሽፋን ቢሮዎችን ከፍቶ፣ ከግዜ ወደግዜ ቁጥራቸው እየናረ የሚሄደውን ደንበኞቹን በትጋት እያገለገለ ይገኛል፡፡ ባሳለፍነው እሁድ ረፋድ በሸገር ካፌ በርቀት ታድሜ በዚህች ታዳጊ ቅጭት ዙሪያ የሬዲዮ ጣቢያው ጭንቅላት የሆነችው መዐዛ ብሩና ዶ/ር ምህረት ደበበ ያደረጉትን ውይይት አዳምጫለሁ፡፡

በውይይት ጠረጴዛው ከውጤቱ ይልቅ ወደፍንጩ ለማተኮር መሞከሩ ተገቢ ነው፡፡ከጭካኔና ከኋላቀርነት ጋር የተላቆጠውን ባህላችንን በርህራሄና በዕውቀት እያነጠሩ መልካሙን አጥልሎ ዝቃጩን በማስወገድ ፈንታ ሌላ ወገን ላይ ለመደፍደፍ ሲሞከር ይታያል፡፡ ከነጮቹ አለም በርካታ በካይ ነገሮች ወደ ውስጣችን መዝለቃቸው አያጠያይቅም፡፡ ይህም ሆኖ በገዛ ድንቁርናችን ያዛነፍነውንና በስንፍና ያስቀጠልነውን ባዕድ ላይ መላከክ አይጠቅምም፡፡ በዚህ መሠሉ የእሮሮ አውድ ከሚቀርቡ ልጠፋዎች አንዱ ሴተኛ አዳሪነትን ያመጣብን ጣልያን ነው የሚለው አንደኛው ነው፡፡ እንደ እውነቱ ግን ከጣልያን ወረራ በፊትም በንፅህና የኖርን ሕዝቦች አይደለንም፤ ከወረራው በፊት በነበረው ባህላችን የሰው ሚስት መወሸም፣ ባለትዳር ቢኮንም ተጨማሪ ሴትን በተጠባባቂነት ማስቀመጥ፣ የጭን ገረድ፣ በተገኘው አጋጣሚ መወስለት እንደነበር አያጠያይቅም፡፡ጣልያን በአምስት አመቱ ያልተረጋጋች ህልውናው ያደረገው ነገር ቢኖር እንዲህ ተበጣጥሶና መልክ አልባ ሆኖ የከረመውን ሀጢያት ተቋማዊነት ማላበስ ብቻ ነው፡፡

አምላኩን ከሰርክ ተግባሩ አባሮ በሃይማኖት ለበስ ድግሱ እንዲሁም በምላሱ ብቻ ቦታ የሰጠ ማህበረሰብ ሀጥያተኛ እንጂ ወንጀለኛ መሆን አልነበረበትም፤ ነገር ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ድርብ ውድቀትን ተላብሷል፡፡ አሳዛኙ እውነታም ይኼው ነው፡፡ ከእምነትም፣ ከህሊናም በመለስ ስናስብ ሴተኛ አዳሪዎች ለማህበረሰቡ ደህንነት እጅግ አስፈላጊ ናቸው፡፡ ነውሩ የወጠረውን ክልፍልፍ በተረገመው መንገድ ተደራድረው ሃጥያቱን በማስፈሰስ፤ ይሄ አማራጭ ባይኖርለት ኖሮ በማህበረሰቡ ውስጥ ይፈጥር ከነበረው ትርምስ ራሱንም መንጋውንም ይታደጉታል፡፡ ይሄ ያልተጠና ድንበር፣ በሚያስደነግጥ መልኩ የሌለ ያህል እየተጣሰ ቀሪውም ማህበረሰብ ከማንና መቼ እንደሚከፈትበት የማያውቀውን ጥቃት እያሰበ በፍርሃት ይማቅቃል፡፡ አምላኩን ቸል ያለ ሃጥያተኛ፣ ህሊናውን ያዳፈነ ነውረኛ፣ ሕግን ያልፈራ ወንጀለኛ ….. የዛሬው ማንነታችን እውነተኛ መልክ ነው፡፡ ዛሬ በየትኛው ዝምድና
መተማመን ይቻላል? አባት ልጁን ይተኛል… ወንድም እህቱን ይጎዳኛል…. አያት የልጅ ልጁን ያስረግዛል … ልጅ እናቱን ይቃብዛል… በሰቀቀን እየኖርን ነው፡፡ ሁላችንም ለሰለባነት ታጭተናል፡፡ ወንድ መሆን ከጥቃት እንደማያድን አይተናል፡፡ ዳዴ ማለት በሰይጣን ክንፎች ከሚበረው ንስር እይታ
ውጪ እንዳልሆነ ሰምተናል፡፡ በእርጅና ዝሎ በዱላ ለመራድ መንገታገትም መስፈርት ሆኖ ከመቅሰፍቱ አላዳነም፡፡ በአንድ ማንነት ውስጥ ካለው ሁለትነት ጋር ተስማምቶ ለመተግበር የሚከብደውን ነውር፣ ሁለት ሶስት ሆነን በመመካከር ሰውን በቁሙ ወደ መብላት ተሸጋግረናል፡፡

በዚች ምስኪን ላይ የደረሰው ግፍ ይፋ ከሆነ በኋላ በወንጀለኞቹ ላይ ከማህበረሰቡ ከፍተኛ ውግዘት የፍርድ ሀሳብ ጭምር እየተሰነዘረ ይገኛል፡፡ የአስተያየቶቹ መግፍኤ የድርጊቱ ዘግናኝነት እና የልጅቷ ፍፃሜ አሳዛኝነት እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ መረሳት የሌለበት ነገር ግን ሕግ አለ፡፡ የትኛውም ወንጀል፣ ምንም አስከፊ ቢሆን ሕጉ ካስቀመጠው የቅጣት ጣራ በላይ ሊያስቀጣ አይገባም፡፡ በስሜት ለተፈፀመ ጭካኔ የስሜት ቅጣት ለመስጠት መሞከር ለነገ አንዳች ትርፍ አይኖረውም፡፡ ለዚህም በምሳሌነት በቅርቡ ኖርዌይ ውስጥ አንድ አውቶማቲክ መሣሪያ የያዘ ወፈፌ ወደ አውራ መንገድ ብቅ ብሎ ወደሰባ አካባቢ ሰዎች የጨፈጨፈበትን ታሪክ ማንሳት ይቻላል፡፡ የሀገሪቱ ህግ ከፍተኛ የቅጣት ዘመን ሀያ ሁለት አመት በመሆኑ የተፈረደበት ይኸው ነው፡፡ ይህን ተከትሎ ግን ህጉን በመከለስ ቅጣቱን ከፍ አድርገውታል፡፡ በሌላ መልኩ በዚህ የወል ኩነኔ ውስጥ ራስን የማፅደቅ፣ እጅን በ “ከደሙ
ንጹህ ነኝ” ዘይቤ የመታጠብ ውስጣዊ አላማም ይታየኛል፡፡ “ከናንተ መሀል ንፁህ ነኝ ብሎ . . .” የሚል ተጋፋጭ እንደሌለ ተገንዝቦ ለወገራ ማሰፍሰፍም ይስተዋላል፡፡

እኛስ ግን ማን ነን? ወንድን በንጉስነት ሴትን በባርነት የበየነ ባህል ባለቤቶች አይደለንም እንዴ? ሴት ልጅን አናንቀን ወንድን ልጅ አተልቀን የምናሣድግ ቤተሰቦች አይደለንምን? ንቀት እና ጭካኔ መግበን እንዲህ ያሉ አረመኔዎችን አብቅለን ስናበቃ፣ መሠቀያቸውን ለማዋቀር ደፋ ቀና ማለት እኛን ያነፃናልን? ደፍረን መድፈር ባንችል በትዳራችን ላይ አንወሰልትም? በስሜት ተነድተን በጓደኛችን ላይ አንሄድም? ዝምድናን አንሰብርም? “በጨለማ ያደረከውን በብርሃን አወጣዋለሁ” መባሉን ዘንግተን በምሽት ሴተኛ አዳሪ አልጎበኘንም? ሌላው ቢቀር በመንገድ በምኞት ተሞልተን የቆንጆ ሴት ቀሚስን በምናብ ገልጠን አልቃዥንም? ታዲያ እኛ . . . ? ? ? ደፍሮ ከደፈረው፣ ያኮበኮበው እጅግ ይበልጣል፡፡ ዛሬም ሀናዎች እልፍ ናቸው፡፡ በእርግብ ንፅህና ገላጣ ሜዳ ላይ ይርመሰመሣሉ . . . ቁራዎችም አመቺ ወቅት ፍለጋ በላያቸው ያንዣብባሉ፡፡ በብዙ መልኩ እየዘቀጥን ነው፡፡ ይሄ
አንደኛው መልክ ብቻ ነው፡፡ ምናልባትም ለራሱ ክብር የማይሰማው፣ አምላኩ መኖሩንም ከጭርታው ይሻላል በማለት የተቀበለ ሰዋዊነቱንም ከእንስሳዊ እውነታው አሻግሮ መመልከት የማይሻ መንጋን አኗኗር በማሳያ ለማስደገፍ ሲባል ብቻ የሚጠቀስ አይነት ብቻ ነው፡፡

በሚደንቅ ሁኔታ በመገናኛ ብዙሃን ስለዚህ ጉዳይ በተነገረ መጠን ውግዘቱና እርግማኑ ተገልብጦ አንደማስታወቂያ እያገለገለ ይገኛል፡፡ መሻቱ ተዳፍኖ ለሚግለፈለፍበት ያገነፍልለታል፡፡ ጭራሽ ውጥኑ የሌለው ላይ ደግሞ ሃሳብ ያጭርበታል፡፡ በየመስኩ ያለውን የኢትዮጵያውያን ሁኔታ ጠቅለል አድርጌ ስመለከተው እጅግ ተስፋ አስቆራጭ ነው፡፡ በተስፋ ለማፍጠጥ የምሞክረው ድቅድቅ ያለ ጨለማማ ዋሻ ውስጥ ሆኜ ነው፡፡ በጨለማው ከማልቀስ ብዬ የምለኩሳት ሻማም ዙሪዬን በሚርመሰመሱት ዞምቢዎች ትንፋሽ ትጠፋለች፡፡ አንዳንዴ አንደውም በማይገፉት የተንሰራፋ ጨለማ ምስኪን ብርሃን መለኮስ ራስን ኢላማ ውስጥ መክተት ይመስለኛል፡፡ ሰው በመሆን መሰልቸት፣ በኢትዮጵያዊነት ችግር ሃዲድ ላይ ለዘመናት መንኳተት ሳቢያ ሙትትት እያለ ካለው መንፈሴ ውስጥ በልብ ትርታ ምት የምትመሰል ስልምልም ተስፋ ግን አንዲህ ትለኛለች . . . “ግን ምልባት ድቅድቅ ያለው ጨለማ
በንጋት ድንበር ላይ እንደሆነስ? ምናልባት ድንዛዜው ከንቃት ጥቂት ርቀት ላይ እንደሆነስ? ብሔራዊው ደዌ በፈውስ ዋዜማ እንደሆነስ….? ምናልባት …..” ትርታው ወደ ድለቃ ሲያድግ ይሰማኛል፡፡ ማን ያውቃል ለመኖር ያለኝን የፍላጎት እስትንፋስ አፍኖ ሊገድላት የደረሰው ተስፋ መቁረጥ እየተምዘገዘገ ከነበረበት የገደል መሬት ሳይላተም ነጥሮ ዳርቻው ላይ በማረፍ የህይወትን ዙሪያ ገባ በተስፋ አይን ይማትር ይሆናል፡፡ ማን ያውቃል???

ዘመን ሞቷል –ኃይሉ አትበሉ (ወለላዬ ከስዊድን)

$
0
0

hai2

ማስታወሻው ጠፍቶ ምስሉ

ተገርስሶ ወድቆ አካሉ

ተሰርዞ ቃለ ውሉ

ዘመን ሞቷል ኃይሉ አትበሉ።

 

ታሪክ የለም አምልጦናል

ዘመን ቆመን ሞቶብናል

ሁሉም አልቆ ተጠቃሏል

ጋሼ ኃይሉ ይዞት ሄዷል

 

ለዘመን ነው እንባ ማፍሰስ

ለታሪክ ነው ከል መልበስ

ለጊዜ ነው ፊት መከስከስ

ለጋሽ ኃይሉ ይብቃን ማልቀስ

 

የዘመንን በሞት ማምለጥ

የጊዜውን መገላበጥ

ገና በፊት ጋሼ ኃይሉ

ተናግሮታል በአፉ ሙሉ

መጣ ብለን ሚሊኒየም

በክብሩ ላይ ልንታደም

ወዲያ ወዲህ ስንሯሯጥ

ምድር ስንቀድ ሰማይ ስንፈልጥ

ከረምንና አገር ወጥቶ

ተበልቶና ተጠጥቶ

ጋሼ ኃይሉ ብቻ ቀርቶ

ምነው ጠፋህ? በዚህ በዓል

አንተ ብቻ ብሎ ሲባል

ያልኖርኩትን አላከብርም

ይሄ በዓል የኔ አይደለም

መች ኖሬ ነው የማከብረው

የኔ ዘመን ሞቷል ተወው

ብሎ ነበር መልስ የሰጠው

 

ጋሼ ኃይሉ እንዲህ ልቆ

ከዘመኑ ተራርቆ

ከጊዜው ጋር ተናንቆ

አንድ ራሱን ብቻ ችሎ

አንድ ራሱን ብቻ ጥሎ

ቢገላገል ቢሄድ ከፍቶት

አረፈ እንጂ ሞተ አትበሉት

 

ታሪክ የለም አምልጦናል

ዘመን ቆመን ሞቶብናል

ጋሼ ኃይሉ ይሄን አውቋል

ቀደም ብሎ መኖር ትቷል

 

ማስታወሻው ጠፍቶ ምስሉ

ተገርሶ ወድቆ አካሉ

ተሰርዞ ቃለ ውሉ

ዘመን ሞቷል ኃይሉ አትበሉ።

 

ትልቁ ሰው ጋሼ ኃይሉማ

ገና ድሮ ይዞ ዓላማ

ተልኮውን እስኪጨርስ

አጠገቡ ሞት እንዳይደርስ

ብዙ ሮጧል ብዙ ሰርቷል

አሸንፎት ሞትን ኖሯል

አሁን ግና ሰርቶ ደክሞት

ቤቱ ድረስ ሲመጣ ሞት

ተቀብሎ በሩን ከፍቶ

ሳይከፋ ተደስቶ

ስለሄደ ተሰናብቶ

ይበቃናል እንባ ማፍሰስ

በረፍቱ ላይ አንላቀስ

ወዲያ ወዲህ አናዋክበው

በኡኡታ አናጅበው

በዋይታ አንቀስቅሰው

በጥሞና በእርጋታ

እንሸኘው በዝምታ

 

ጋሼ ኃይሉን የምታውቁት

ወዳጆቹ ምታከብሩት

የበፊቱን አታስታውሱት

እባካችሁ እንባ ተዉት

ታሪክ ቆመን የሞተብን

እውነት ፊቱን ያዞረብን

ዘመን ጥሎን ያመለጠን

እሱ ሳይሆን እኛ እኮ ነን

ጋሼ ኃይሉ ሞቱን አውቋል

ቀደም ብሎ ተሰናብቷል

እየኖረም መኖር ትቷል

 hai3

ማስታወሻው ጠፍቶ ምስሉ

ተገርስሶ ወድቆ አካሉ

ተሰርዞ ቃለ ውሉ

ዘመን ሞቷል ኃይሉ አትበሉ።

***

ወለላዬ ከስዊድን (welelaye2@yahoo.com)

ስምንት ጠቃሚ ነጥቦች ከእስራኤላውያን -ክፍል 5 (ዮፍታሔ)

$
0
0

ከዚህ ቀደም በነበሩት 4 ክፍሎች የእስራኤልን ታሪክ በአጭር በመቃኘት ስለአንድ ማዕከላዊ ድርጅትና ስለተቋማት አስፈላጊነት፣ ትግሉን ዓለምአቀፋዊ ስለማድረግ፣ ስለዳያስፖራው ወሳኝ ሚናና የጋራ ቋንቋ ለአንድ አገር ያለውን ጥቅም በሚመለከት ተገልጿል። ክፍል 5 በአገር ጉዳይ የሀይማኖት መሪዎችና አገልጋዮች ሊኖራቸው ስለሚገባው የመሪነትና የማስተባበር ሚና ከእስራኤል ታሪክ በማጣቀስ ያብራራል።

 

  1. የሀይማኖት መሪዎችና አገልጋዮች ሚና

 

Jewish+Ethiopians+Reunited+Families+Israel+o1h5oGhsf2Vlበኢየሩሳሌም የነበረው ቤተመቅደስ በሮማውያን ፈርሶ እስራኤል በየአገሩ ከተበተኑ በኋላ ብዙ የአይሁድ ካህናት አልነበሩም። ምክንያቱም ቤተመቅደስ በሌለበት ካህን ሊኖር ስለማይችል ነው። ሆኖም ይህ ባይቻልም ብዙዎች መምህራን (ረበናት) ሆኑ። በአይሁድ ታሪክ ውስጥ እነዚህ የአይሁድ መምህራን የነበራቸው አስተዋጽኦ ሁሌም ገንቢ ባይሆንም እጅግ ከፍተኛ ነበር። በየሄዱበት ፈጽሞ እምነቱ እንዳይጠፋና አይሁድም የሚሰባሰቡበትና እየተገናኙ በዓላትን የሚያከብሩበት የአምልኮ ስፍራዎች (Synagogues) ከማቋቋም ጀምሮ በማንኛውም አገርን የሚመለከት ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳይ ሁልጊዜም ከፊት የሚገኙት እነዚህ መምህራን ነበሩ።

 

ያቋቋሟቸው ቤተመቅደሶች እምነቱ ባህሉና የእብራይስጥ ቋንቋ (በንግግርም ባይሆን በጽሑፍ) ፈጽሞ እንዳይጠፋ ዋና ምክንያት ነበሩ። አይሁዳውያን በተጠቁ ጊዜ መጠለያ፣ በትግሉ ጊዜ መሰባሰቢያ ወዘተ ሆነው አገልግለዋል።

 

እነዚህ የሀይማኖት መምህራን በዚህ ብቻ አልተወሰኑም። ጠንካራ ማኅበራትን በማቋቋም በትግሉ ውስጥ የመሪነትና የአስተባባሪነት ሚና ተጫውተዋል። በአንደኛው የዓለም ጦርነት (እ. ኤ. አ በ 1914) በኦቶማን ቱርኮች ጭቆና ሥር የሚማቅቁትን አይሁድ ለመታደግ ሲባል በአስቸኳይ በተፈለገ 50,000 ዶላር መነሻ ከአሜሪካ ግዛቶች ብቻ የተሰባሰቡት አይሁድ በተወሰነ ጊዜ ውስጥ ከ 78 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማዋጣት የቻሉት በእንደዚህ ዓይነት ማኅበራት (ኦርቶዶክስ አይሁድ በአብዛኛው የሚገኙበት American Jewish Distribution Committee ዋናው ነው) የተሰባሰቡ ነበሩ። ይህ ማኅበር ለተፈናቀሉ ርዳታና የመልሶ ማቋቋም አገልግሎት ከማበርከቱም በላይ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ከመቀስቀሱ በፊት በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ አይሁድ ጀርመንን ለቀው እንዲወጡ በማድረግ ሕይወታቸውን ታድጓል። በ 1943 (እ. ኤ. አ) ከአራት መቶ በላይ ከተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች የተሰባሰቡ የአይሁድ መምህራን በአውሮፓ በአይሁዳውያን ላይ የሚደርሰውን ግፍ በመቃወምና የተባበሩት መንግሥታቱ ኃይል ግፉን ለማስቆም የወሰደውን ርምጃ በመደገፍ በአሜሪካን አገር ያደረጉት ሰልፍ በጊዜው የዓለምን የመገናኛ ብዙሐን ቀልብ በመሳብ  የአይሁድ ሕይወት በስደት ምን እንደሚመስል ለዓለም ሕዝብ ያስገነዘበና በእስራኤል የትግል ታሪክ ሁልጊዜም ሲጠቀስ የሚኖር ነው።

 

በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የቤተክርስቲያንና የመስጊድ አገልጋዮች ከአይሁድ ጋር የሚመሳሰሉት በየሄዱበት ከሕዝቡ ጋር በመተባበር አብያተክርስቲያንንና መስጊዶችን በማቋቋም ያበረከቱትና አሁንም እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ነው። እነዚህ የሀይማኖት ተቋማት ለሕዝቡ መንፈሳዊ አገልግሎት ከማበርከት በተጨማሪ እንደመሰባሰቢያ በመሆንም ያገለግላሉ።

 

ኢትዮጵያውያን የሀይማኖት መሪዎች በሕዝቡ ዘንድ ከማንም ይልቅ ተቀባይነትና ተሰሚነት ቢኖራቸውም ይህን ተቀባይነትና ተሰሚነት እስካሁን ለአገር ጉዳይ በአብዛኛው ሲጠቀሙበት አልታየም ቢባል እውነት ነው። ይህ ደግሞ የአገርን ጉዳይ ብቻ የሚመለከት ሳይሆን መንፈሳዊ (የተጎዱትን የማጽናናት፣ የተጨነቁትንና የተሸበሩትን የማረጋጋት፣ ርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ፈጥነው ርዳታ እንዲያገኙ የማስተባበር ወዘተ) እና ማኅበራዊ አገልግሎቶችን በሚመለከት ነው። ቋንቋን፣ ባህልንና ታሪክን ጠብቆ ለሚቀጥለው ትውልድ የማስተላለፍ ሥራ የነዚህ የሀይማኖት ተቋማት፣ አገልጋዮችና መምህራን ሥራ ሆኖ ለዘመናት የዘለቀ ቢሆንም በአሁኑ ጊዜ መድረክ ላይ ቆሞ ከማስተማር ባለፈ በተጠናና በተዘጋጀ መንገድ ለቀጣዩ ትውልድ (ለልጆች) በበዓላት መዝሙር ሲዘምሩ ከማሳየት ባለፈ ይህን መሰል እውነተኛ አገልግሎት ሲሰጥ አይታይም። በቋንቋና በሀይማኖት ትምህርት በኩል አንዳንድ ሙከራዎች ቢኖሩም ከወላጆችና ከሰንበት ትምህርት ቤቱ የሚያልፍ አይደለም። ይህም በሚገባ በተደራጀና ተከታታይነት ባለው ሁኔታ የሚፈጸም ባለመሆኑ ውጤት አይታይበትም።

 

በውጭ የሚገኙት አባቶች፣ ካህናት፣ የሀይማኖት መሪዎችና አገልጋዮች በውጭ ያላቸውን ነፃነት ተጠቅመው በመንፈሳዊውም ሆነ ከመንፈሳዊው እጅግ የተሳሰረ በሆነው የሕዝቡ ማኅበራዊና የአገር ደኅንነት ጉዳይ በመሪነትና በማስተባበር ብዙ ሊያደርጉ ሲገባ መክሊታቸውን አልተጠቀሙበትም። በየአረብ አገራት (በቅርቡ በሳውዲ አረቢያ የተፈጸመውን ጨምሮ) በኢትዮጵያውያን ላይ ለሚደርሰው የማያቋርጥ ችግር ተባብረው የውግዘትና የተቃውሞ ድምጻቸውን ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ከማሰማትና ለጥቃቱ ሰለባዎች የመንፈሳዊ ማረጋጋትና ማጽናናት አገልግሎት ከመስጠት ጀምሮ ምእመናንንና ዳያስፖራውን በመሪነት በማስተባበር “ሠርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ” ዓይነት ሳይሆን የደረጁ ቋሚ ማኅበራትን በመፍጠር ችግሩ ለደረሰባቸው ወገኖች አስቸኳይ ርዳታ እንዲደርስ ማድረግና ችግሩን ከምንጩ ጀምሮ በማየት የረጅም ጊዜ ዘላቂ መፍትሔ መስጠት ከማንም በፊት የሀይማኖት አባቶችና አገልጋዮች ሥራ ነው። ይህን አላደረጉም። ልጆች በማደጎ ሰበብ ካገር እየወጡ ብዙ ችግር ሲደርስባቸውና አሁንም የልጆች ሽያጭ ሲቀጥል ይህን ለማስቆምና ሌላ አማራጭ መፍትሔ ለማግኘት አንዳችም ነገር አላደረጉም። ከሕዝቡ ፊት መገኘት ሲኖርባቸው የነርሱ ኃላፊነትና ሥራ በሆነው ሁሉ ሕዝቡና የፖለቲካ ድርጅቶች እየቀደሟቸው እነርሱ ከኋላ ሲጎተቱ ታይተዋል።  አንዳንዴም ሀይማኖታዊ ግዴታቸውን ረስተው በጥቅምና በዘር እየተደለሉ ከሚያልፈው ጋር እየተሰለፉ ሊያገለግሉት የሚገባውን እግዚአብሔርንና የእግዚአብሔርን ሕዝብ ከአምባገነኖች ጋር ተባብረው ሲጎዱት ታይተዋል። በዚህም ሕዝቡ ተስፋ ከእነርሱ መጠበቁን ትቶ ከሌሎች መጠበቅ ከጀመረ ቆይቷል። ሕዝቡንና አገርን የመታደግ፣ የመጠበቅና የሕዝቡን ኑሮ በመንፈሳዊም በቁሳዊም የማበልጸግ ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን ግዴታም አለባቸው። ምክንያቱም ቁሳዊው መንፋሳዊውንም ስለሚጎዳው ነው።

 

ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊ የሆኑ ልጆች ማንነታቸውን፣ ባሕላቸውን፣ እምነታቸውን፣ ታሪካቸውንና ቋንቋቸውን እንዲያውቁ ማድረግ የትግሉ አንድ አካል ነው። ግእዝ አዋቂ የሆነው የኢትዮጵያዊው መሪጌታ፣ ካህንና ዲያቆን ልጅ አማርኛ የማያውቅ ከሆነ ችግር አለ ማለት ነው። በአገራችን ላይ እየተፈጸመ ያለው ጥቃት ታሪክን፣ ባሕልን፣ እምነትንና የጋራ ቋንቋ እንዳይኖር በማድረግ አገሪቷን የመበተን ዘርፈ ብዙ ስለሆነ ትግሉም እንደዚሁ ሥርዓቱን ከመቀየር ጎን ለጎን ብዙ ዘርፍ እንዲኖረው ያስፈልጋል። ዘረኛው ሥርዓት ኢትዮጵያን አጠፋለሁ ስላለ አትጠፋም። ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ የሚያደርጓት በዋናነት እነዚህ እሴቶቿ ናቸው። እነዚህ ካልጠፉ አትጠፋም። ነገር ግን እኛም ተባባሪ ሆነን እነዚህን እሴቶች በማቃለል ይልቁንም ለሚቀጥለው ትውልድ ማስተላለፍ ካልቻልን ያን ጊዜ በርግጥ የኢትዮጵያ ሕልውና አደጋ ላይ ይወድቃል። ይህ እንዳይሆን የወላጆች ድርሻ ትልቅ ቢሆንም የሀይማኖት መሪዎች እነርሱ አርአያ በመሆን ወላጆችን በማነሳሳትና በመርዳት ባሕሉ፣ ታሪኩ፣ እምነቱና ቋንቋው ተጠብቆ ወደልጆች እንዲተላለፍ ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

 

እነዚህ አቢያተክርስቲያናት ያላቸውን ተቋማዊ አቅምና የያዟቸውን በተግባር በጉልበታቸው፣ በጊዜአቸውና በገንዘባቸው ላመኑበት ነገር (ሀይማኖት) ወደኋላ የማይሉ ምእመናን ችላ እያለ በዳያስፖራው ትብብር ጠንካራ ተቋማትንና ድርጅቶችን እመሠርታለሁ ብሎ የሚያስብ ማንኛውም አካል የተሳሳተ ነው። ሕወኀት አብያተክርስቲያንን እያበጣበጠ በሥሩ አድርጎ ለመቆጣጠር ሙሉ ኃይሉን የሚጠቀመው ለምንድን እንደሆነ በሚገባ ልንረዳ ይገባል። በጠቅላላ አብያተክርስቲያንን ከዚህ ተጽእኖና ቁጥጥር ነፃ ማድረግና በምትኩ ለአገራቸው አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ መንገዱን ሁሉ ማመቻቸት የትግሉ አንድ ዘርፍ እንደሆነ መረዳት ያስፈልጋል።

 

(ይቀጥላል)

 

ኢትዮጵያ በቆራጥ ልጆቿ ሥራ ታፍራና ተከብራ ለዘለዓለም ትኖራለች!

 


የወያኔ ምርጫ –ጭንጫ። (ሥርጉተ ሥላሴ

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 05.12.2014 /ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ/

እንደላበዛባችሁ እዬሰጋሁ ግን የገጠመኝን መልካም ነገር ቀድሜ ላወጋችሁ ወደድኩኝ። እባክቻሁ ውዶቼ ፍቀዱልኝ? መቼም ዘንድሮ አውጊ አደራ ሁኛለሁ። …. የማንነት ጽጌረዳ ነውና አትቆርጡም ብዬም አስባለሁ።

2007 electionእንደ – በር። አልኳችሁ ትንሽዬ ቀጠሮ ኖራኝ ወደ አንድ የማላውቀው ሰፈር ተጓዝኩኝ – ዕለተ – እሮብ። የምሄድበት ቦታ አዲስ ስለነበረም ከቀጠሮዬ ሰዓት በፊት ሁለት ሰዓት ቀድሜ ነበር የደረስኩት። ከዚህ በኋላ ትንሽ ሻይም ቡናም ከተገኘ ብዬላችሁ ላይ ብል ታች ብል ፈጽሞ ምንም የሚላስ የሚቀመስ ነገር በአድባሩ የለም። እንዲህ ደግሞ ገጥሞኝ አያውቅም። ወደ ላይ ሲኬድ ቀጥ ያለ አስፓልት ወደ ታች ሲወረድም ቀጥ ያለ አስፓልት።

በዛ እንደ ባንዴራ በማተቡ በፀና ሎጋና ዠርጋዳ አስፓልት ዳር ለዳር አንዲት ሩጫ የምትለማመድ ደማም ውብ ጸዳላማ ወጣት አገኘሁና „ሻይ ወዴት ላገኝ እችላለሁ?“ ብዬ ጠዬቅኳት። „በዚህ አቅጣጫ ሁለት ሰዓት ብትጓዢ አንዲት ትንሽዬ ኪወስክ ታገኛለሽ። ቡናዋ ግን አይጣፍጥም። በስተቀር ግን ወደ ከተማ ተመልስሼ ካለሆነ በስተቀር እምታገኚው ነገር ዬለም“ ብላ ቁርጤን ነገረችኝ። አመናታሁና ለምን ከዛው ከተቀጠርኩበት አካባቢ ሰማይና መሬት ያገናኘ ዬሚመስለውን የተንጣለለ ሃይቅ እያዬሁ አልቆይም ብዬ ወደዛው አቀናሁ። ብርዱ ደግሞ አይጣል ነበር። አሳቻ ቦታ ላይ  በጣም ወደ ውስጥ ገባ ባለ የወንዝ የመንገድ ግድግዳ አንድ በር ሲከፈትና ሲዘጋ ስላዬሁ ሰዎች በሚገቡበት አቅጣጫ እኔም ዘው ማለት ….

ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? ቦታው ባር ነገር ነው። በውጪ ምንም የተፃፈበት ነገር የለም። ሙዚቃው ደግሞ ምን ሊሆን ይችላል ብላችሁ እስኪ ገምቱ – በሥርጉተ ሞት? ገመታችሁ? ይግርማችኋል ለ1.30 ሰዓት ያህል ቀጠሮዬ እስኪደርስ ተቀመጥኩኝ። ሳይቋረጥ የኢትዮጵያ የመሳሪያ ቅንብር ሙዚቃ ነበር አድባሩን የተቆጣጠረው። ሻዬን ከያዝኩኝ በኋላ ጠጋ ብዬ አስተናጋጁን „ዬዬት ሀገር ሙዚቃ ነው ስል በትህትና ጠዬቅኳቸው?“ ቀጥዬም „አድራሻውን ሊሰጡኝ ይችላሉን?“ አልኳቸው፤ ቀልጠፍ ብለው። „የመሳሪያ ቅንብሩ ሙዚቃ  የኢትዮጵያ በህላዊ ሙዚቃ ነው። ከፈለጉ ደግሞ ሥሙን እሰጠወታለሁ“ አሉኝ። ግርም ብሎኝ ሌላ ጥያቄ ደግሞ ቀጥልኩ „ከዚህ ከእናንተ ባር ኢትዮጵያውያን ሠርተው ያውቃሉን? ወይንም የሚሠራ ኢትዮጵያዊ አለን?“ ስል ጠዬቅኩኝ ….

መቼም ኢትዮጵውያን የጠረናችን ነገር አይሆንልንምና። „ኢትዮጵያዊ ተቀጣሪ የለንም“ አሉኝ። „ኖሮንም አያውቅም።“ በማለትም አከሉልኝ። ቀጥለው ትንሽ እንደማሰብ ብለው „ ነገር ግን እዚህ የጃፓን፣ የቲቤት፤ የቻይናና የኢትዮጵያ የመሳሪያ ሙዚቃዎች የተለመዱ ናቸው። እንግዶቻችን በፍቅር ይወዷቸዋል“ አሉኝ። እኔም ለካንስ የነዚህ ሀገሮች የመሳሪያ ቅንብር ሙዚቃ ለእኔም በግሌ የሚስቡኝ ተመሳሳይ ዬቃና ቅኝት ስላላቸው ይሆን ብዬ ራሴን ጠዬኩኝ። አዎን የአንገቴን ጌጥ በስንድድ የተሠራውን አረንጓዴ ቢጫ ቀዩን ገለጥ አድርጌ „እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ“ ብዬ ነገርኳቸው። ደፍረው የሚናገሩት፤ አንገትን የማያስደፋ – ባርነት ያልጎበኘው፤ የነጠረ ማንነቴ ኢትዮጵያዊነት አለልኝና። ቀጥዬም … „ይህ አክብሮታችሁ የሰማይ ነው እንጂ የምድርም አይደለም። እግዚአብሄር ይስጥልን አልኳቸው።“ ትክ ብለው በመገረም አይተው „እኔም አመሰግናለሁ“ አሉኝ።

እስከ አሁን ይገርመኛል። ደስታውም አልቀቀኝም። እኛ ያልሠራንበትን ጥበበኛው አምላክ እንዲህ አሳምሮ ይሠራልናል። ያግዘናል – የቃል ኪዳን ሃገሩ ናትና – ኢትዮጵያ! የሚደንቀው ነገር የመሳሪያ ቅንብሩ የእነማን እንደ ሆነ፤ ባንዶችን ሳይቀር በዝርዝር ነበር የነገሩኝ። በተጨማሪም ኢትዮጵውያንና ሆላንዳውያንም የጋራ ባንድ እንዳላቸው መረጃውን ሰጡኝ። እንግዶቻቸውም በጣም የሚወዱት ስለሆነ ሙሉ ጊዜውን ሲያዳምጡት ቢውሉ እንደማይሰለቻቸው ገለጹልኝ። እንዲህ ያልተወለደን በፍቅር የሚገዛ ውስጣችሁን ባላሰባችሁበት ቦታና ጊዜ ሲገጥም ከቶ ምን ትላላችሁ? እጅግ ደስ ያለኝና የወደድኩት ጊዜ ነበር። በጋ ላይም ሥራዬ ብዬ እሄዳለሁ። …. ክብራችን – ፍቅራችን ለመጎብኘት …። እንዲህ እንደ ተፈለገ የማይንዘገዘግ ማንነት ያለው ነው ኢትዮጵያዊነት ማለት። ”ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች!” – ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት (የጉዳያችን ማስታወሻ) http://www.zehabesha.com/amharic/archives/36814 እኔም እላለሁ ኢትዮጵያዊነት ረቂቅ ቅዱስ መንፈስ ነው።

እጅግ የሚገርም ነበር። ውስጤን አብዝቶ ፈተሸኝ። ባህላዊ ምግብ ቤት ገብቼ አዳምጬ ስለማላውቅ ማለት ከሀገሬ ከወጣሁኝ፤ ሀገሬ የገባሁ ያህል ነበር የተሰማኝ ለዛውም በነጮች ባር። ወግ አበዛሁ አይደል ክብሮቼ? ተፈርዶብኝ ነው። ደስ ስላለኝ ነው። ይቅርታ … እኔም ቋጥሬ የሄድኩት የእምዬን ዕንባ ስለነበረ … አገጣጠመችው …. ወፊቱ …

የወያኔ ምርጫ – ጭንጫ።

አሁን ወደ ተነሳሁበት ግን አጠር፣ ደንበል አድርጌ – ጭንጫና ቁም-ነገር መንገድ ላይ እንኳን ተገናኝተው አያውቁም። ጭንጫና ፍቅር ሆነ ጭንጫና አብሮነትም እንዲሁ። ጭንጫና ፍትህ ሆነ ርትህም አይጥና ድመት ናቸው። ውዶቼ እስኪ በርከት ያሉ ጭንጫዎችን ከመዳፋችሁ ላይ ኮልኮል አድርጋችሁ እዮዋቸው። ምን ይመስላሉ? ኮልኩሏቸውም፤ – ይስቃሉን? ለመሆኑ ነፍስ ቢጤ አላቸውን? ይተነፍሳሉን? አባብሏቸው – አቆለማምጧቸው? የሚረዱት የሚገባቸው ነገርስ – ይኖራልን?

ቀጥላችሁ ደግሞ ጭንጫውን ውሃ ውስጥ ጨምሩት። ከቶ ሟሟን? ተቀላቀሉን? እንዲያው ምንስ መልክ ኖረው ከቶ? እ … ቡላማ …. አመዳም? ወይንስ የንፁሁን ውሃ ተፈጥሮ ብክል አደረገው ይሆን? አወና! …. መልከ ጥፉ ስለ ሆነ ደህናውን የውሃንም ተፈጥሮ አጎሽቶ አይሆኑ አደረገው አይደል? አንዷን ጭንጫ አፈፍ አድርጋችሁ ደግሞ በጥርሳችሁ እስኪ ሞካክሯት? ታዲያ እንደ እኔ ፈንጠርጣራ ካልሆነ ነው። ደግሞ በህግ እንዳልጠዬቅ …. ባለ ጠንካራ ጥርሶች ፍንክች አለላችሁ ይሆን ሞገደኛው – ጭንጫ?

ጭንጫ ቀዳዳም አልሰራለትም፤ መተንፈሻ ቧንቧም የለውም። ውስጡንም ከፍቶ ማዬትም አይቻልም። ለግሞ  – ሎግሞ የሚይዘው የራሱን ኩረት ተፈጥሮውን ብቻ ነው። ከራሱ ኩረት ተፈጥሮ ውጪ የሚያስጠጋውም አንዳችም ነገር የለም። ውስጡ በልዞ – አሮ ጠንዝሎ – ቢከስልም ያችኑ እሮውን ተሸከሞ እንደ ኳረት ዘመኑን ይሸኛል።

ጭንጫውን አስተካክላችሁ ወደ አንድ ሰው ዓይን ብትወረውሩት ግን …. አደጋ ያመጣል። አደራ እንዳትሞክሩት። ጭንጫ ለመጉዳት ብቻ የተፈጠረ.፣ ቃና የለሽ፤ ወዝ የለሽ፤ ለዛ ቢስ፤ ምንም የማይገባው፤ ለምንምና ለማንም የማይሆን ብቻ ከብለል እያለ እያሾፈ ዘመኑን በተፋቀ ተፈጥሮው እንደ ከብት የበላውን መልሶ እያወጣ ሲያመንዥክ የሚኖር …. መንቻካ  – ጥጥር ያለ የጓጓለ ተፈጥሮ አለው። በጭንጫ ውስጥ አዲስ ተስፋን ማብቀል ሆነ ማጽደቅ የተከለከለ መንገድ ነው። ፍርፋሪ ወይንም ኦፋ ሊወረውር ይችል ይሆናል። ይህም ቢሆን ከሥጋ በይ እንሰሳ ጥርስ ውስጥ ሥጋን የማስለቀቅ ያህል ጣር ነው —– ጣጣውም ምጥ፤

የአቶ ወያኔ ዬምርጫም ማንፌስቶም ጭንጫማ ነው። አይገመስ፤ አይጋጥ፤ አይጣጣም፤ ብጥቅ የምትል ነገር አተወጣውም። አስልቶ ለማጥቃት ብቻ የተሠራ ወይንም የተድቦለቦለ ቅርጽ – ቀለም – ፎርም – ያልፈጠረለት፤ ስድና መደዴ ነገር ነው። በዚህ እንድርቺ – እንድርቺ ጨዋታው ግን ስልቦ ወይንም ሰንጎ* ፍላጎቱን ያስፈጽማል። ጭንጫ የሚመቸው – ለጭንጫ ብቻ ነው። ጭንጫ ግጥሙ አምሳዬው ጭንጫ ነው። ጭንጫ መልኩ ጭንጫ ነው። ጭንጫ ደምና ሥጋው ጭንጫ ነው። ጭንጫ – ቅልቅሉም ሆነ ግጥግጡ ከጭንጫ ከመሰሉ ጋር ነው – ጋብቻውም። ከአምሳያው ውጪ የሚመጣ ቀናዊ ሂደት እንደ ጸጉረ ልውጥ ያዬዋል። እንደ ጠፍርም እስኪበቃው በቂም በቀል ያሸዋል። ይደቃዋል። ይሰልቀዋል። ይፈጨዋል … እንጂ ብጣቂ ርህራሄ አያጎራርሰውም። ጭንጫ ይሉኝታ የለውም – ፈጽሞ።

ጭንጫ ህግ የለውም። ህግ አልባ ነው። ጭንጫ መርህ የለውም – ዳሪ አዳሪ ነው። ጭንጫ የመንፈስ ጥግ አልፈጠረለትም – ሜዳ በቀል ነው። ህግ አልባነቱ በጥሰት መሄዱ ብቻ ሳይሆን፤ ተፈጥሮው በሆነው ብቀላ ተቀናቃኙን እዬዳጠና እዬዳመጠ ነው የሚጓዘው። ይህ የጭንጫ ውስጥ ደግሞ በበቀልና በቁርሾ ኩረት የተሞላ ነው። ህልሙ ማጥቃትን አስልቶ፤ ማቁሰልን አልሞ በመሆኑ ከእሱ በተቃራኒ ያሉ ማናቸውም ሰዋዊ በጉ ሕይወታዊ ዝንባሌዎች ሆኑ አስተሳሰቦች ሁሉ ካለይግባኝ የጥቃቱ ሰለባ ይሆናሉ። አይምሬ ነውና።

በጎጠኝነት ዶክተሪን ሰብዕዊነት የሚባል ነገር የለም – ፈጽሞ። ደረጃው አይፈቅድለትምና። ጎሰኝነት ወይንም ዞገኝነት እኮ ታች ያለ የአስተሳሰብ የታቆረ ድህነት ነው። በአንዲት ምድጃ ዙሪያ ብቻ የተከለለ፣ በተወሰነ ጉዳይ የታጠረ ወይንም የተከተረ ስለሆነ ስለ ሰፊው ዓለምና ስለ ሥልጡኑ ዓለም ዕይታው ሆነ ነገረ ሥራው ጭንጫማ ነው። ዕድገትም አያውቀውም። ዕድገቱ የምድር እንቧይ* ነው። በዚህ የግንዛቤ ደረጃ ላይ የሚገኝ ቡድን ሌላውን የሚሰማበት ወይንም የሚያዳምጥበት ወይንም የሚያስተውልበት ጸጋውን ላልተመጣጠነ ዕድገት ላለው ለኋለቀር አስተሳሰቡ ገብሮታልና።

ይህ ባህሬው ደግሞ ነጭናጫና ቁጡነትን፤ ተጣራጣሪነትን፣ አድብቶና አነጣጥሮ ማጥቃትን፤ ጥላቻና ክፋትን አብቅሎ …. ዘመንን ጠቀራ ያለብሳል። አልብሷልም። ስለሆነም ጠቀራማውን ዘመን ለመቀዬር የመብት ግዴታው ከጭንጫ ጋር አለመዶለትን፤ ማዕደኛ አለመሆንን በእጅጉ ይጠይቃል። መስሪያው* የተለዬ ነውና። እንዴትና እንዴት … ተብሎ? የማይገናኝ መንገድ የወል አድራሻ የለውም። የማይገናኝ ተስፋም የወል እርገት የለውም። አምሳያ ከአምሳያው ጋር ቢወዳደር ቢፎካከር – ወሸኔ ነው። ማለፊያ! …. ከጭንጫ ጋር ግን ….. ምርቱ ሆምጣጤ ብቻ ነው። ከቶ የጭንጫ ማኒፌስቶ በዬትኛው ተፈጥሮው ነው መርህን አክብሮ በመርህ የሚዳኘው?!

ክብረቶቼ – እርገት ይሁን፤ ከሚጠበቅ ራዕይ ተስፋን መጠበቅ – መልክ አለው። ከማይጠበቅ ምክነት ግን ማለም ተስፋን ማራቆት ወይንም የብዙኃንን ምኞት እርቃኑን እንዲቀር መመቸት ወይንም ዬዕንባን ፍላት ፈቅዶ እራስ ማፈን ይመስለኛል።

የትናንት 04.12.2014 ጸጋዬ ራዲዮ Tsegaye Radio ዝግጅት ሲጀመር ችግር ነበረው – የቴክኒክ። በኋላም 33 ደቂቃ ብቻ ነበር አዬር ላይ የቆዬው። ስለሆነም ታላቅ ይቅርታ በትሁት መንፈስ እጠይቃለሁ፤ ችግሩ እኔ የፈጠርኩት ባይሆንም። የቴክኒክ ችግር ስለ ገጠመ ነበር። በኋላ ግን ከ16 – 17 ቀጣዩን የራዲዮ ዝግጅት ሰርዘው ራዲዮ ጸጋዬ እንደ አዲስ ተጀመረ። ለፈጣኑ እርማትና ለአክብሮቱ ራዲዮ ሎራ እያመሰግነኩኝ ዓይናማዋን፣ ደመ ግቡውን የጋዜጠኛ ተመስገን ወንድም ዬአቶ ታሪኩን እናታችን ፋናዬና ተመስገን በዝዋይ’” መንፈስ ጋር ጸጋዬ ራዲዮ ቆይታውን አድርጓል። ከፈቀዳችሁ አርኬቡ ላይ ማድመጥ ትችላለችሁ።  ኑሩልኝ!

መሸቢያ ሰንበት – ለእኔዎቹ።

መፍቻ።

  • ሰንጎ … በኃይል – በጎልበት – በጡንቻ – በብረት ድጋፍ – አስገድዶ፣ ደም አስፍቶ፣ አንቆ ይዞ ፍላጎትን ማስፈጸም – ለወመኔዎች በትክክል የተፈጠረ ቃል ነው።
  • መስሪያ … በጋራ – በሌማት፤ በሞሰብ – በወልዮሽ፤ በጥራር – በአንድነት፤ ወይንም በትሪ – በአኃታዊነት የጋራ ማዕዶት
  • ጥራር … ከሰንበሌጥ በእጅ የሚሰራ መመገቢያ ባህላዊ ዕቃ … ተወዳጅም።
  • የምድር እንቧይ … እንቧይ ሁለት ዓይነት ተክል አለው። አንዱ በትክክል በቅሎ እንደ አጋም እንደ ቃጋ የሚያድግ እድገቱ የሚታይ ፍሬውም እንደ እንኮይና ኮሽም ዓይነት ሲሆን። ሌላው የምድር ዕንቧዩ ግን እንደ ሥሙ ዕድገቱ መሬት ላይ ነው የሚቀረው። ሀረጉም ብዙ አይጓዝም – ድካም ያሸነፈው ተፈጥሮ ነው ያለው። ፍሬው ቀለሙ ያልበሰለ ወይራ መሰል ቆባ ዱባ ወይንም ዝኩኒ ነገር ነው። ከመሬት በቅሎ ጫጭቶ እዛው ተሰክቶ – አሮም ይቀራል።

ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር ኢትዮጵያዊነት!

ለእኔስ ሰው መሆኔ ብቻ ይበቃኛል!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ – ኑሩልኝ!

ከመተባበርና አንድ ከመሆን በላይ ታላቅነት የለም –የሰማያዊ ከፍተኛ አመራር

$
0
0

ፍኖተ ነፃነት

“አምናለሁ። አንድ ሆኖ ለአንድ ሀገር መቆም ብንችል እውነት ይሄ ታላቅነት ነው። ከዚህ በላይ ታላቅነት አለ ብዬ አላስብጭ፡፡”

“በፍቅር በሰላማዊ መንገድ በመነጋገር የማንንም ሰው ሀሳብ ማሸነፍ ይቻላል ብዬ አምናለሁ።”

ወ/ሮ ሃና ዋልለልኝ ይባላሉ። የሰማያዊ ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ ናቸው። ፍኖተ ነጻነት ባወጣው 86ኛ እትሙ ቃለ መጠይቃ ካደረገላቸው የተወሰደ ነበር። ከቅአለ መጠይቅቁ የተወሰነዉን እንደሚከተለው አቅርበናል።

ፍኖተ ነፃነት፡- በመጪው ምርጫ ላይ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ምንድን ነው የሚጠበቀው?

10344785_738568506228086_275256779448546603_nወይዘሮ ሀና፡ – ከተቃዋሚዎች የሚጠበቀው እርስበርሳችን በመስማማትና ትንንሽ ልዩነቶቻችንን በማስተካከል ባለችው ቀዳዳ፣ ጠባብ ቀዳዳ ማለት እችላለሁ ሾልከን ለውጥ ለማምጣት መትጋት ነው፡፡ የረጅም ጊዜ ልምድ አለ፤ ከዛ ውስጥ ደግሞ ነጥረው የሚወጡ ሰዎች ይኖራሉ፤ የሚታዩም አሉ። ጥሩ ጥሩ ወጣቶችም እያደጉና እያበቡ ነው። እነዚህን ነገሮች ወደ ተግባር ወይም ወደ ውጤት በመቀየር ለምርጫ ራስን ማዘጋጀት ያስፈልጋል። ምክንያቱም ሀገሪቷ ላይ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በምርጫ የሚመጣ ስልጣን ብናገኝ በእውነት ይህቺ ሀገር ታላቅ ትሆናለች። ጥሩ ነገርም ይታይባታል፡፡ስለዚህም እርስ በእርሳችን በብዙ ፍትጊያ ውስጥ አልፈን በብዙ ዘረኝነት ውስጥ አልፈን እዚህ ደረጃ መድረስ ራሱ ትልቅነት ስለሆነ ይሄን ብናደርግ ደግሞ የተሻለ ትልቅ ሰው እንሆናለን ብዬ አምናለሁ። እርስ በርሳችንም እንከባበራለን፤ እንቻቻላለን፤ መቻቻሉ ግን በመተማመን ውስጥ መሆን አለበት ብዬም አምናለሁ።

ፍኖተ ነፃነት፡- በፖለቲካ ፓርቲዎች አብሮ በመስራት ላይ ሁለት አይነት አስተሳሰቦች በአደባባይ ሲራመዱ እናስተውላለን። ፓርቲዎች አንድ ላይ ተባብረው መስራት አለባቸው የሚል ወገን አለ፡፡ አንዳንዱ ደግሞ ብቻቸውን ነጥረው መውጣት አለባቸው ይላል፡፡ባንቺ አመለካከት አሁን ካለው የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ አውድ አንጻር የትኛው ያዋጣል

ወይዘሮ ሀና፡- ፓርቲዎች ነጥረው ይወጣሉ የሚለው ነገር የእኔም ሀሳብ ነበረ። ጥረቱ ጥሩ ነው። ባልተሄደበት መንገድ መሄድ የአስተዋይነት ምልክት ነው። ባለንበት እንቁምና ባለንበት እንርገጥ የሚል አስተሳሰብ መኖር የለበትም። ሁልጊዜ የሰው ልጅ አዲስ ነገርን ይፈልጋል። አዳዲስ ነገሮችን ማምጣት ይፈልጋል። ስለዚህ ያልተደረጉ ነገሮችን መሞከርና ማድረግ ጤናማነት ነው። ያ ደግሞ የማይሳካበትን ሁኔታ ካወቅን ወይም ደግሞ በፊት አብሮ መስራቱ አይጠቅምም ብለን ከነበረ አሁን ይጠቅማል ወደሚለው ነገር ላይ አስተሳሰባችን ከመጣ ደግሞ ያንን ተቀብሎ ማራመድ ምንም የሚጎዳ ነገር አይደለም።

ሁለቱም ሀገርን ለመጥቀም ለውጥን ለማየት ከመፈለግ የመነጨ እስከሆነ ድረስ ጤናማ ናቸው፡፡ ለየብቻ መስራት የሚያዋጣ ነው ብለን እርግጠኛ ስንሆን ብቻችንን መስራት ይኖርብናል። እኔ አሁን ያለኝ እምነት አብሮ መስራት ታላቅ ያደርጋል ነው። ሁለተኛው ነገር ደግሞ ከአንድ ብርቱ ሁለት መድሃኒቱ የሚለው ተረት ቀላል አይደለም። በሶስት የተገመደ ገመድም ምን ያህል ጠንካራ እንደሆነ እናውቃለን። ከዚህ በፊት ለብቻችን ነጥረን እንውጣ የሚለውን ሀሳብ ከሚያራምዱት ውስጥ ነበርኩኝ። ያም የተደረገበት ምክንያትም ከመገፋት ወይም ደግሞ አቅምንና ያለንን እውቀት ለማውጣትእንዳንችል ከመደረግ አንፃር ነው።ሆኖም ግን ያንን ነገር ለውጠን የአብሮመስራታችንን ብቃታችንን ክህሎታችንን አሳድገን አብሮ በመስራት ለውጥ ማምጣት፣ ራሱን የቻለ ስኬት ነው ብዬ አምናለሁ። አንድ ሆኖ ለአንድ ሀገር መቆም ብንችል እውነት ይሄ ታላቅነት ነው። ከዚህ በላይ ታላቅነት አለ ብዬ አላስብም፡፡ ራስን ለሀገር መሰዋት ማድረግ ያስፈልጋል። በነገራችን ላይ እኔ መስዋዕት የምለው የመሞት የመታሰርን ብቻ አይደለም፡፡ ትልቁ መስዋዕትነት ማለት ፍላጎትን ሁላ ማሸነፍ መቻልን ራስ ወዳድነትን ማሸነፍ መቻልንና ለሌሎች መኖር መቻልን ነው፡፡ ለሌሎች መኖርን መልመድ መቻል አለብን። በአፍ ሳይሆን በተግባር ይሄን ካደረግን የማይፈነቅል ድንጋይ አይኖርም።

ፍኖተ ነፃነት፡- የፓርቲዎች የውስጥ ዴሞክራሲ ምን መሆን አለበት ትያለሽ? በየፓርቲዎቹ ውስጥ ያሉ አስቸጋሪ ባህርያቶችስ ምንድን ናቸው?

ወይዘሮ ሀና፡- ብዙ ጊዜ ችግራችን መደማመጥ አለመቻል ነው ብዬ አስባለሁ። እንደገና ደግሞ እኔ አውቃለሁ የሚሉ ሰዎች ካሉ የሌላውን ሀሳብ የሚገፉ ከሆነ የመናገር መብትን የሚገድቡ ከሆነ ሁልጊዜ ችግር መፈጠሩ አይቀርም፡፡ ከዛ ይልቅ ግን መደማመጥ ቢኖር በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር ቢኖር ስህተት ያለበትም ሰው ስህተቱን እንዲያምን በሀይል በጠብና በቁጣ ሳይሆን በፍቅር በሰላማዊ መንገድ በመነጋገር የማንንም ሰው ሀሳብ ማሸነፍ ይቻላል ብዬ አምናለሁ።

በሀሳብ ላይ መፋጨት በጣም ጠቃሚ ነው። የተሻለና የነጠረ ሀሳብ እንድናመጣም ያደርጋል። ያ ሰው ምንም ቢሆን ሀሳቡንም ማዳመጥ ማክበር ያስፈልጋል። እንደዚህ አይነት ነገሮችን አዳብረን ብንሄድ አሁንም ደግመዋለሁ የማንፈነቅለው ድንጋይ ይኖራል ብዬ አላምንም።

ፍኖተ ነፃነት፡- በመጨረሻ ማስተላለፍ የምትፈልጊው መልዕክት ካለ

ወይዘሮ ሀና፡- ማስተላለፍ የምፈልገው አንደኛ ለፓርቲዬ ማለትም ለሰማያዊ ፓርቲ ነው። ሰማያዊ ፓርቲ በውስጡ ምርጥ ምርጥ ወጣቶች አሉ፡፡ ብዛትም ባይሆን አንድ ሰው ለውጥ ያመጣል ብዬ አስባለሁ። ያንን ሰው ግን በአግባቡ መጠቀም መቻል አለብን ጓደኞቼን በጣም አከብራቸዋለሁ እወዳቸዋለሁ የአስተሳሰብ ልዩነታችንን በጣም አደንቃለሁ፤ በአስተሳሰብ ልዮነታችን ውስጥ ብዙ የተደበቁ ነገሮች ይወጣሉ ብዬ ስለማምን ስላየሁም ማለት ነው። ጥሩ ነገሮች ብቻ ሳይሆን የተደበቁ ስህተቶችም ይወጣሉ። ይህንን በደንብ አይቻለሁ፡፡ ይሄንን ነገር በደንብ አከብራለሁ። በውስጥ የሚሰራውንም ስራ በርቱ ግፉበት እላለሁ፡፡በተለይ በማንም ፓርቲ ውስጥ ያላየነውን የኦዲትና የኢንስፔክሽን ስራ አከብራለሁ ለዚህም በእውነት አድናቆቴን
ማስተላለፍ እፈልጋለሁ። ጥሩ እየሰራ ነው። ፓርቲ ውስጥ ላሉ ችግሮች እስከ ቅጣት ድረስ በመሄድ ለማስተካከል የተሞከረውን ነገር ሳላደንቅ አላልፍም።

በሁለተኛ ደረጃ ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎችንም አከብራለሁ አደንቃለሁ ብዙ ትምህርቶችን እንድማር አድርገውኛል አሁን ለደረስኩበት ብስለት እንድደርስ የእነዚህ ፓርቲዎች መፈጠር ጥሩ አጋጣሚና እድል ፈጥሮልኛል። ሀቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የጭቆናውን አመት
ለመቀነስና በጭንቅ ላይ ያለችን ሀገር ለመታደግ መፍጠን አለባቸው። አሁን የዕንቅልፍ ጊዜ አይደለም፡፡የምንፈጥንበትን የሩጫ ሂደትና ቀስ የምንልበትን እንደገና ደግሞ አሯሯጭ የምንሆንበትን መለየት መቻል አለብን።

የኢትዮጲያ ህዝብንም የምለው ነገር ይኖራል፡፡ የኢትዮጲያ ህዝብ ሆይ! ተስፋ አትቁረጥ፤ ተስፋ የሚቆርጥ የሞተ ብቻ ነው። በቁም ያለ ሰው የሚፈልገውን ነገር እጁ ውስጥ እስካላስገባ ድረስ ተስፋ አይቆርጥም። እስከ መጨረሻ ህልፈተ ህይወቱ ድረስ ማድረግ ያለበትን በሙላ ያደርጋል። ሰው እንሁን፤ ስብእናችንን እንጠብቅ፤ እርስ በእርሳችን እንከባበር፤ እንተማመን፤ መተማመን አንድነትን ያመጣል፤ አንድ ከሆንን ደግሞ የማንሰራው ነገር አይኖርም። ከዓለም በታች ጭራ የሆነችውን ሀገር ከፍ እናደርጋታለን፡፡ለዚህ ደግሞ እግዚአብሔር
ይርዳን ማለት እፈልጋለሁ። አመሰግናለሁ።

ተስፋዬ ተስፋ ሲቆርጥ –ክፍል 3

$
0
0

ከሠናይ ገብረመድህን (ጋዜጠኛ)

ብርጋዴር ጄኔራል ከማል ገልቹ ወታደሮቻቸዉን በህግደፍ የተዘረፉበት ኩነት ብዙዎቻችንን በታሪካችን አንድ አስገራሚ ሆኖ ያለፈ ዜናን ማስታወሱ አልቀረም፡፡ “ኮ/ል መንግስቱ ሀይለማርያም በሱዳን አስተባባሪነት ዜጎቼን በእስራኤል ተዘረፍኩ አሉ” በሚል የተዘገበዉን የአሜሪካ ድምፅ የአማርኛ ፕሮግራም
ዜና ፡፡ ኢትዮጵያዉያኖቹ ቤተእስራኤሎች በድብቅ ወደ እስራኤል የተጉዋጉዋዙበት የሞሰስ ኦፕሬሽን ይሄዉ ሶስት አሰርት ደፈነ፡፡ የቤተእስራኤሎቹን ጉዳይ በተመለከተ ዘረፋ ወይንም የማጉዋጉዋዝ ኦፐሬሽን ተብሎ በዜና ተወርቶላቸዋል፡፡ በህግደፍ ስለተዘረፉት ኢትዮጵያዉያኖች ግን ምንም አልተወራላቸዉም፡፡ ያዉም በዘመነ ኢንፎርሜሽን፡፡ (እኔ እሆን ገና አሁን ስለመዘረፋቸዉ እያወራሁ ያለሁት ?) ከሆነም እኮራለሁ፡፡ ስለወገኖቼ በግፍ መዘረፍና ታጋችነት የሰሚ ያለህ በመናገሬ ፡፡ እነሱ ብቻም አይደሉ ህግደፍን አምነዉ ተጠልለዉ ግና ባልገመቱት ሁኔታ በህግደፍ የታፈኑ ያታገቱና የተዘረፉት፡፡ ጊዜና ሁኔታ እንደፈቀደልን የምናዉቀዉን ያለፍንበትን የእማኝነታችንን አቤት እንላለን፡፡ የነበርን ሰዎች፡፡ ፍርዱንም ለሁለቱም ህዝቦች በጎ አሳቢና አላሚዎች እንተዋለን፡፡ ላሁኑ ይህን እንቀጥል!
የኒያላ ሆቴል ሰፋፊ ሳሎኖች ቀኑን ፀጥታ ስለሚነግስባቸዉ እንደልብ እየተደማመጡ ወግ ለመኮምኮም ይመቻሉ፡፡ ተስፋየ ገ/አብም ፡ ሌ ኮ/ል አበበ ገረሱና ሌ/ኮል አለበል አማረን በጋራም ሆነ በተናጥል እያገኛቸዉ ብዙ ቀናቶችን ወግ የተቀባብሉት እዚያ ነዉ፡፡ ተቀባይ ተስፋየ ሰጪ ሌ ኮ/ሎቹ ፡፡፡ ተስፋየ ደግሞ በቢራ ጀምሮ ለጥቆም በጂን እያቀባበለ ጨዋታቸዉን አወራርዱዋል፡፡ ጨዋታን ጨዋታ ካነሳዉ በአለኮል አጃቢነት የሚወርዱ ጨዋታዎች ጡጦዋ በጨመረች ቁጥር በግነት በስሜታዊነት በቅብዥርዥርነት አይበረዙም ትላላችሁ? ተስፋየ ራሱ እንደነገረኝ እንዲህ ባሉ የጠረጴዛ ምሽቶች የሚመሰጥባቸዉን ጨዋታዎች በዉስጡ ሲያከማች ያመሽና ሌሊት ይፅፋቸዋል፡፡ ወደ አንጎሉ እንደአወጣጣቸዉ ሁሉ እንደወረዱ ስለመፃፋቸዉ ግን እንጃ! የጂን ነገር! (የኒያላ ሆቴልን ነገር ካነሳን ይቺን እንበል ፡፡ አስመራን የረገጡ አያሌ ኢትዮጵያዊያን በኒያላ ሆቴል የትግል ጎራ ተስተናግደዋል፡፡ እኔም አንዳንዴ “እስኪ ኒያላ ሆቴል ግምባር ጎራ ልበል!” እያልኩ ቀልድ ቢጤ ጣል አደርግ ነበር፡፡ የምቀልደዉ በኢትዮጵያዉያን ወገኖቼ አልነበረም፣ በህግደፍ የአጋች ታጋች ተግባር እንጂ፡፡ ኒያላ ሆቴል አፍ ቢኖረዉ … !! ከብ/ጄ ከማል ጦር ጋር ኤርትራ የገባዉ ሌኮ/ል አበበም የአስመራዉ ኦነግ ለሁለት ሲከፈል ከብ/ጄ ከማል ጋር ወገነ፡፡ ብዙም ሳይቆይ በጤና ሳቢያ ከነከማል ቡድን ተሰናበተ፡፡ ህግደፍም ኒያላ ሆቴል እንዲመሽግ ፈቀደለት፡፡ ሰንበትብት ብሎም የራሴን የፖለቲካ ድርጅት መስርቻለሁና በሚዲያችሁ ይለቀቅልኝ አለ፡፡ የማይታሰብ ነበር፡፡ ለህይወቱ ስለሰጋሁ “እረ
ባክህ እዚህ ሆነህ ድርጅት መስርቻለሁ የምትለዉ ነገር ይቅርብህ፡፡ በሰላም ከዚህ አገር መዉጫህን ፈልግ” የወንድምነቴ ተማፀኖ ነበር፡፡ አልሰማኝም፡፡ በኢንተርኔት ለቀቀዉ፡፡ ሌኮ/ል አለበል ደግሞ በከፍተኛ አመራርነት የአማራ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ መመስረቱን ከእኔ ጋር ባካሄደዉ የቴሌቭዥን ቃለመጥይቅ ይፋ አድርጉዋል፡፡ ከኤርትራ እስከወጣሁ ድረስ ይህ ሁኔታ ነበር፡፡ ከተስፋየ ጋር በሚገናኙበት ወቅትም በዚህ ሁኔታ ላይ ነበሩ፡፡ የኒያላ ሆቴል ወጎች ልንለዉ እንችላለን (ጎበዝ ትዝታየ የጎንዮሽ ይዞኝ ሲነጉድ ራሴን ታዘብኩት)፡፡

Author Tesfaye Gebreab

Author Tesfaye Gebreab


ተስፋየ ከሌ/ኮ አበበ ገረሱና ከሌ/ኮ አለበል ጋር ሲገናኝ አንድ ነገር አዉቁዋል፡፡ ሌ/ኮ አበበ ከብ/ጄ ከማል ጋር መቆራረጡንና በህግደፍ ይሁንታ ኒያላ ሆቴል መመሸጉን ፡ ሌ/ኮ አለበል አማረ የአማራ ድርጅት ምስረታ ላይ መሆኑን ፡፡ እንዴት አያዉቅ ጎበዝ ! ኢትዮጵያን እንደ ቅርጫ ተካፍለዉ በቅዠት በሪሞት ኮንትሮል የሚገዙዋት ኮ/ል ፍፁም(ሌኒን) ኮ/ል ጠዐመ (መቀለ) ኮ/ል ጋይም፣ ኮ/ል ዮናስ እኮ ወዳጅና መሃንዲሶቹ ናቸዉ፡፡ ዋናዉ የህግደፍ ቢሮ ቤቱ ነዉ፡፡ እነ ብ/ጄ ከማልና ብ/ጄል ሀይሉ ጎነፋ ደግሞ ከህግደፍ ጋር ስለተፋቱ አላስፈለጉትም፡፡ ለህግደፍ አይመቹም ፡፡ (የህግደፍን ፊት መንሳት ካነሳን በኤርትራዊያን ላይ የሚወርደዉን ግፍ ትተን በእንግድነት የገቡትን ኢትዮጵያዉያንን ብንነቅስ፡ አነጋፋዉ የኦነግ አመራር አቶ ገላሳ ዲልቦ ከኦነግ አመራርነት ተወግደዉ አቶ ዳዉድ ከህግደፍ ጋር ሲወዳጁ አቶ ገላሳ አስመራ ላይ እንዴት እንዴት በህግደፍ ፊት እንደተነሱና በከባድ ህመም ሲሰቃዩ ችላ ተብለዉ ህይወታቸዉ በኤርትራዊዉ የቀድሞ የአ/አ ዩኒቨርሰቲ ጉዋደኛቸዉ አቶ ምህረቱ በእምነት እርዳታ መትረፉን መዘከር ይበጃል፡፡ በአስመራዉ የስደተኞች ኮሚሽን የስደት አገር ተገኝቶላቸዉ ከኤርትራ ሚግሬሽን የመዉጫ ቪዛ ስለተከለከሉት ወገኖችስ ቢሆን ማን ይሆን ያገታቸዉ ማን ይሆን ያሳገታቸዉ ? ( የታሪክ ማጣቀሻ መፅሃፍ ይወጣዋል ) እነዚህን መሰል ህግደፍ በኢትዮጵያዊያን ላይ ስለፈፀማቸዉ ወንጀሎች ፊት መንሳት…መንቀስ ይቻላል ፡፡ ግን እንዲህ ነበር የሆነዉ እየሆነ ያለዉም ፡፡ በቃ! አሁን ግን ይሄን ገታ አርገን ወደ ጀመርነዉ እንለፍ፡፡

የነተስፍሽን የአመሻሽ ማዕድ እየተጋራሁ ከጨዋታቸዉ ስጋራ ሰነበትኩ፡፡ሌ/ኮል አበበና ሌ/ኮል አለበል የቀጣዩ መፅሃፍ ባለታሪኮች መሆናቸዉን አወቅሁ፡፡በዚያዉ ሰሞን ምሽት ሌላ አንድ እንግዳ አብሮ ተገኘ፡፡በአምሳዎቹ የሚገኝ፡፡ አምቼ ኤርትራዊ ኢኒጂነር መሆኑን በትዉዉቅ ተረዳሁ፡፡ጥርት ባለ አማርኛዉ፡፡ ከጠረጴዛዉ ጨዋታ ገለል ብለን ከኢነጂነሩ ጋር ወግ ጀመርን፡፡ ወሎ ደሴ ማደጉን ከገለጠልኝ በሁዋላ ስለዝነኛዉ የወይዘሮ ስህን ት/ቤት የቀድሞ ትዝታዉ እያነሳ ጨዋታን ጨዋታ እየመዘዘዉ ነጎድን፡፡ እኔም የወሎ ልጅ [ከወረሴህና ጃንጥራሮች የምወለድ] ነኝና ጨዋታዉን በፍስሃ ስሜት ተሞለቼ አጣጣምኩት፡፡ በጥያቄ በትዉስታዎች ያቅሜን እየተሳተፍኩ፡፡በጨዋታ መሀል አስመራ ከሚገኙት የቀድሞ የስህን ት/ቤት ተማሪ ከነበሩት ከአቶ ጠሐ ሱዋሊህ ጋር ያደረግኩትን የትዉስታ ዝግጅት እንደወደደዉ ገለጠልኝ፡፡ ኢትዮጵያ ዉስጥ ተወልደዉ ያደጉና ረዥም የህይወት ዘመናቸዉን በተለያዩ ሙያ ያሰለፉና በአማርኛ ሀሳባቸዉን መግለፅ የሚችሉ ታጋዮች ኤርትራዊያንን ወደ ፕሮግራማችን በመጋበዝ የምናካሂደዉ የጨዋታ ጊዜ በበኩሌ በጣም ነበር የምወደዉ፡፡ በዉስጤ የሁለቱን ህዝቦች በፍቅር የተሞላ ግንኙነት ያንፀባርቃል ብየ ስለማምን፡፡ ከጥላቻ ፖለቲካ የራቀ በመሆኑም፡፡ “ሠናይ ከኢነጂነር ጋር የምታደርገዉን የግል ጨዋታ አቁዋርጥ” ተስፋየ በጨዋታችን መሃል አንባርቆ ገባ፡፡ “እንዴ ለምን? እንዲያዉም የፕሮግራማችን የጨዋታ እንግዳ አደርገዋለሁ፡፡ ስለ የወሎ ጣፋጭ ጨዋታዎችና በቀደምት ተማሪዎች ትግል ታሪክ አዉራ የሆነዉ የስህን ት/ቤት ትዝታዎች ባለቤት ነዉና ባስተናግደዉ እኔንም ፕሮግራማችንንም ያኮራናል” ስል መለስኩለት፡፡ “ኢነጂነርም ፈቃደኛ ነዉ” አከልኩ፡፡ ተስፈየ ተወራጨ ፡፡ ሞቅታም አለ፡፡ ከዚያም ወደኔ ቀረብ አለና በልመና መልክ “እኔ ታሪኩን በቀጣዩ መፅሃፌ ላካትተዉ ስለሆነ እባክህ ተዉ፡፡” ሲል ተማፀነ፡፡ “ያንተ በመፅሃፍ ስለሆነ ረዘም ልታደረገዉ ትችላለህ እኛ ግን በዉስን የአየር ሰዓት ነዉ የምናስተናግደዉ፡፡

አቀራረቡ ደግሞ የተለያየ መሆኑን ከኔ በላይ ታዉቃለህ፡፡” ተስፋሽ አልተዋጠለትም፡፡ “በእናነተ መጀመሪያ ከቀረበ ለኔ ጥሩ አይመችም” ሌላ ሰበብ አከለ፡፡ “አሁን የመፅሀፍህ አካል የሚሆኑት ኮ/ል አበበና ኮ/ል አለበልም እኮ በእኛ ፕሮግራም ተስተናግደዋል፡፡ አሁን የኢነጂነር ልዩነቱ ምንድን ነዉ?” ጥያቄየ ነበር፡፡ አልመለሰልኝም፡፡ የንትርካችን ምክንያት አልታይህ አልዋጥልህ አለኝ፡፡ በመሀል አጣብቂኝ የገባዉ ኢነጀር “ሠናይ ግድ የለም፤ መጀመሪያ ከተስፋየ ጋር እንስራና ከእናንተ ጋር በቀጣይ አደርጋለሁ፡፡ እዚሁ ስለሆነ ያለሁት ችግር የለም” ሲል የሽምግልና ሀሳብ አቀረበ፡፡ እየሳቅሁ ጣጣ የለዉም አልኩ፡፡ የኢነጂነርን ሁኔታ በመረዳት፡፡ ተስፍሽ ፊቱ ፈካ አለና “በእሪኩም ዘመዳ.. አባብለህ ባለታሪኬን ልትማርክ” ቀለደ፡፡ እኔም ትዝብቴ ጦዘ፡፡ ይሄዉ ጥቂት ወራት ቆጥሮ የስደተኛዉ ማስታወሻ ወጣ፡፡ ተስፍሽና ህግደፍ መፅሃፉን አሰራጩት ቸበቸቡት፡፡ እኔም ባለታሪኮቹም አነበብነዉ፡፡ አንድ ምሽት ኒያላ ሆቴል ጎራ ስል ሌ/ኮ/ል አለበልና አበበን አገኘሁዋቸዉና “እህሳ አማን ነዉ? እንዴት እንዴት ተነበበ መፃፉ?” መፅሃፉ ዉስጥ እንዳገኘሁዋቸዉ በሚያመላከት ወንድማዊ ሰላምታ ወግ ከፈትኩ፡፡ በአንዳች ስሜት ተያዩና “ሆድ ይፍጀዉ አለ ጥላሁን” አቤ ተነፈሰ ከቀጭን ፈገግታ ጋር ፡፡ “እዚሁ በህይወት እያለን ያልተባለ ነገር መፃፍ በጣም ነዉር ነዉ” አለበል ተከተለዉ በትንታግ ስሜት፡፡ ከሁለቱም ኮሎኔሎች ጋር ደረግነዉ ቆይታ ለተሰፋየ ያጫወቱትን በተዛባ መልኩ ማቅረቡንና ከቶወኑም ያላሉትን ጨማምሮ መፃፉ እጅግ እንዳሳዘናቸዉ በሚገልፅ ምሬት የተሞላ ነበር፡፡ “ከብዙ ወዳጆቼ ትችት ደረሰበኝ፡፡ የኦሮሞን ህዝብ ክብር አዋረድክ አሉኝ ፡፡ እኔ ያላለኩትን ጨማምሮበታል ብልም ሰሚ አጣሁ። ስለዚህ ከመፅሃፉ ታሪክ በታሪክ እየጠቀስኩ በዉጭ በሚዲያ አጋልጠዋለሁ” የሚለዉን የተሰበረ የሌኮ/ል አበበን ስሜት አስታዉሳለሁ፡፡ “አሁን ባለህበት ሁኔታ በዉጭ ሚዲያ ተስፋየን መተቸቱ ላንተ ህይወት ጥሩ ስለማይሆን እስኪ ታገስ” ከማለት በቀር በበኩሌ የምለዉ አልነበረም ፡፡ ነዉርነቱን በማጠናከር ፡፡ “ያልሰማ ጆሮ ከጎረቤት ያጣላል” ብለዋል አበዉ ፡፡ ጆሮ ዳዋ ልበስ ከሆነ ግን ሆን ተብሎ ለነገር እንጂ ለሌላ ምን ይሉታል፡፡ የሆነ ሆኖ ኮ/ሌኖሎቹ ተስፋየ ላይ
ንዴታቸዉን በግል እንዳይተነፍሱ በከተማዉ ፈልገዉ አጡት ፡፡ ከኤርትራ ወደ ዉጭ በመሄዱ፡፡ እንዲሁ እየተብሰከሰኩ ወር ሁለት ወር ካሳለፉ በሁዋላ ታዲያ ከተስፋየ የተዘዋዋሪ መልዕክት ደረሳቸዉ፡፡ ለእያንዳንዳቸዉ 5 ሺህ ናቅፋ ጠቅላላ 10ሺህ ናቅፋ(200 ዶላር) ፡፡ በተግባሩ ማዘናቸዉን ሰምቶ አፍ መዝጊያ ከባህር ማዶ ብር እንደላከላቸዉ እየቀለዱ አወጉኝ ፡፡ ይበልጥም አዘኑበት ፡፡ ጉርሻዉንም አልተቀበሉትም፡፡ ገንዝብ እንደሚያስፈልጋቸዉ ባያጠያይቅም ክብረ ነክ በሆነ መልኩ መቀበልን አልመረጡም፡፡ በዉነት ከኩሩወቹ ወገኖቼ በመሆናቸዉ ኮራሁባቸዉ ፡፡

እነ ሌኮ/ል አበበና አለበል ይህን ቅያሜያቸዉን ካካፈሉኝ በሁዋላ ወሎ አደጉን ኢነጂነር አግኝቼ የሚለዉን መስማት ፈለግሁ፡፡ “ኢኒጂነር የነ ኮ/ሎኔልን ታሪክ አነበብኩት ያንተን ታሪክ ግን አጣሁት፡፡ ስለ ወሎ የአንድ ሰዉ ታሪክ ትዝታ ግን አንብቢያለሁ፡፡ አንደ ልጅ በኢንተርኔት በብዙ ድርድር ያደረሰኝ የወሎ አባት ታሪክ ነዉ በሚል ያቀረበዉን ፡፡ ያንተስ የታለ?” እንዳገኘሁት ያቀረብኩት ጥያቄ ነበር፡፡ “እሱ እኮ ነዉ እኔ ያካፈልኩት ታሪክ ፡፡ በዚህ መልኩ እንደሚቀርብ አልገመትኩም፡፡ ስሜ ይጠቀሳል እንጂ አይጠቀስም ብየ አልጠበቅኩም” ሲል ኢነጂነር ያልጠበቅኩትን ገልፆ ቅሬታዉን አዘነበዉ፡፡ “የታሪኩ ባለቤት አንተ እዚሁ እያለህ ከሌላ በደጅ ጥናት እንደደረሰዉ አስመስሎ በሌላ ስም አቀረበዉ ነዉ የምትለኝ ?” የሰማሁትን ማመን አልቻልኩም፡፡ ዕዉቁ የብዕር ሰዉ በዓሉ ግርማ ጋሼ ስብሃትና ሌሎችም ደራሲዎች ከሰዎች እዉነተኛ ታሪክና እዉኑ አለም ሰዎች ባህሪያት ተመስርተዉ ልቦለድ የመፃፍ ክህሎታቸዉን አዉቃለሁ አንብቢያለሁ፡፡ የጋሼ ስብሃት ትኩሳት ሌቱም አይነጋልኝ አጋፋሪ እንደሻዉ የበአሉ የቀይ ኮኮብ ጥሪ መፅሃፉ ላይ ያሉት እነ እምአእላፍና ደርቤ በቅርብ ከሚያዉቃቸዉ መሆኑን፡፡ ደራሲዉ ከፊል የደራሲ ስብሃት ገ/እግዚአብሄር ታሪክ ስለመሆኑ፡፡ ጋሼ ስብሃት ስለ በአሉ ሲናገርም ይህንኑ ማብራራቱን ሰምቻለሁ፡፡ በሌሎችም በልቦለድ ዉስጥ የእዉኑ አለም ሰዎች ገፀባህሪያት ተላብሰዉ መቅረባቸዉ የተለመደ አፃፃፍ ነዉ፡፡ ግለታሪክ ከሆነ ግን እንደወረደ መቅረብ የሚኖርበት ይመስለኛል፡፡ ባለታሪኩ በዘመኑና በቦታዉ ጀልባ ዉስጥ አሳፈሮ በትዝታ ባህሩ ዉስጥ እየተመላለስን እንድንሳፈፍ ከማድረጉም ባሻገር ዘመኑንና ቦታዉን እንደነበረ ለማየት እንድናጣጥም ይረዳል እላለሁ፡፡እናምነዋለንም፡፡ ለባለ ግለታሪኩም እዉቅናን ሰጥተን እናከብራልን፡፡ የደራሲ ሀዲስ አለማየሁ ግለታሪክ የደራሲና ገጣሚ መንግስቱ ለማ ታሪክ የዘነበ ወላ የስብሃት ማስታዎሻ የፍቅሩ ኪዳኔ የአራዳ ልጆች …… ; የመሳሰሉት ግለታሪክ መፃህፍት ባለታሪኮቹ በራሳቸዉ ስለሚተርኩልን መሳጭነታቸዉ አያጠያይቅም፡፡ ተስፋየ እንዳደረገዉ ግለ ታሪክ ብለን ያነበብነዉ ልብወለድ ሆኖ ስናገኘዉ እንዴት እናምነዋለን? “አይነጋ መስሉዋት ….. “ አበዉ ያሉት ነገር ፡፡ እንጃ እንግዲህ ከብሂሉ ባሻገር ሌላዉ የስነፅሁፍ ባለሙያዎችን ይመለከታል፡፡

ከህይወት ዘመኑ የወሎ ትዝታዉን ለተስፋየ ያካፈለዉ ኢነጂነር እነሆ እዉቅናና አክብሮቱ ቀርቶ ስሙን እነኩዋን ከደራሲዉ ማስታወሻ ላይ ማግኝት ሳይችል ቀረ፡፡ “በጣም ያሳዝናል፡፡ ተስፋየ በእኛ የቴሌቭዥን ፐሮግራም ላይ የጨዋታ እንግዳ ሆነህ እንዳትቀርብና ስለወሎ ደሴ ወ/ሮ ስህን ት/ቤት መልካም ትዝታህን ቀድመህ እንዳታካፍል የፈለገዉ ከሌላ የደረሰዉ አስመስሎ ለማቅረብ ስለፈለገ መሆኑ ነዉ ፡፡ ለነገሩ እሱ መች ሆነና …..” ንግሬን አልጨረስኩትም፡፡ ስሜቴን መቆጣጠር ተገቢ መሆኑን ዉስጤ ነገረኝ፡፡ “ይሄዉ ተስፋየ ታሪኬን በአደባባይ ዘረፈዉ “ ኢነጂነር መራራ ቀልድ ቀለደ ፡፡ በክህደት የተሞላዉ ህግደፍ ያመኑትን ኢትዮጵያዉያን ወታደሮችን ዘረፈ ፡፡ መዝረፉንም ቀጠለ ፡፡ ተስፋየ ገ/አብም ግለ ታሪክ ዘረፈ ፡፡ ‹የአባት ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ› መሆኑ ይሆ ? ለዛሬ በዚሁ ይብቃን፡፡ ለቀጣዩ የዚያ ሰዉ ይበለን !
ቸር እንሰንብት፡፡

ሠናይ ገብረመድህን (ጋዜጠኛ)
አዉስትራሊያ ሜልበርን
ለግል አስተያየታችሁ ከአክበሮት ጋር ፡ Wosenmarta_2010@yahoo.com

ቴዲ አፍሮን ቦሌ ላይ ለምን አገቱት? –ክንፉ አሰፋ (ጋዜጠኛ)

$
0
0

teddy afro
ክንፉ አሰፋ
ወደ አውሮፓ የሚያስገባውን ቪዛ እና ትኬት ይዞ ከወዳጆቹ ጋር ጉዞውን ለመጀመር ወደ ቦሌ አለም-ዓቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ አቀና። እዚያው እንደደረሰ የተለመደው የፓስፖርትና ትኬት ቁጥጥር ተደረገ። ሁሉም የተሟላ ነበር። ቴዲ ሸኚዎቹን ተሰናብቶ ወደ ውስጥ ገባ። እለተ ሐሙስ፣ ህዳር 28 ቀን 2007 ዓ.ም.።

የአውሮፓው ኮንሰርት በፊንላንድ፣ ሄልሲንኪ ቅዳሜ፤ ህዳር 28 ቀን ይጀምራል። ፊንላንድና አካባቢው ያሉ የቴዲ አድናቂዎች ትኬት ቆርጠው አርቲስቱን በጉጉት እየተጠባበቁት ነው። የቴዲ አፍሮ ማናጀርም አቡጊዳ ባንድን ይዞ ሄልሲንኪ ላይ ለቅዳሜው ስራ በልምምድ ላይ ይገኛል።

ቴዲን ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ተሰናብተው የተመለሱ ወዳጆቹ አውሮፓ ደውለው አርቲስቱን ሄልሲንኪ ላይ እንዲቀበሉት ተናግረው ነበር። ነገሩ እነሱ እንዳሰቡት ግን አልነበረም። ዘግየት ብሎ ሌላ ነገር መጣ። ሰዎቹ ቦሌ ላይ አገቱት። በውድቅት ሌሊት ፓስፖርቱን ነጥቀው ወደ ቤቱ አሰናበቱትም። ይህንን ያደረጉበትን ምክንያትም አልነገሩትም። አስቀድመው ገና ከበሩ ላይ መከልከል ይችሉ ነበር።… ግን ማንገላታት ነበረባቸው። ስሜቱን ለመጉዳት መሞከር ነበረባቸው። ጉልበት እንዳላቸው ማሳየት ነበረባቸው። ፈላጭ፤ ቆራጭ መሆናቸውን ማሳወቅ ነበረባቸው። ቂመኞችና ተበቃዮችም መሆናቸውን መናገር ነበረባቸው። ….

ነገሩ ያልተጠበቀ ባይሆንም፤ ለቴዲ ጠበቆች ግራ ማጋባቱ አልቀረም። በነጋታው ጠበቆቹ ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ፍርድ ቤት መሄድ ነበረባቸው። ከፍርድ ቤት ያገኙት ምላሽ በቴዲ አፍሮ ላይ ምንም አይነት የማገጃ ትዕዛዝ ያለመኖሩን ነው። ከዚያም ወደ ኢሚግሬሽን ጉምሩክ እና ሌሎች ጉዳዩን የሚመለከቱ ቢሮዎች ሁሉ አመሩ። እዚያም የጉዞ ማገጃ አልተገኘም። ታዲያ ማን ይሆን ያዘዘው? የካዛንችዙ ስውር መንግስት ስራውን እንደገና ጀምሮ ይሆን?

ጉዳዩ ግራ ያጋባል። እርግጥ ነው። የዛሬይቱ ኢትዮጵያ አንድ ተራ ካድሬ እንዲህ አይነት ተራ ወንጀል የሚፈጽምባት ሃገር ሆናለች። አንዳንድ ቦታዎች ላይ “መንግስት የለም እንዴ?” የሚያስብሉ ወንጀሎች እንደሚፈጽሙ ይሰማል። የቀድሞው የኮሚኒኬሽን ሚንስትር ዴዔታ የነበረው ኤርምያስ ለገሰ፤ በቅርቡ ባሳተመው “የመለስ ትሩፋቶች” የተሰኘ መጽሃፉ አዲስ አበባን ባለቤት አልባ ከተማ ብሏታል።
በልማታዊ አርቲስቶች እለት-ተለት የሚወደሰው ጸሃዩ መንግስት፤ ለልማት የተጋው መንግስት፣ ጭቆናን ያቆመው መንግስት፤ ለዜጎች መብትና ነጻነት የቆመ መንግስት፣ ሃገሪቱን ወደ እድገት እና ትራንስፎርሜሽን ጎዳና ላይ ያስኬደ መንግስት፣ የመቻቻል ባህልን ያመጣ መንግስት…. እንዴት ሆኖ የጥላቻ፣ የቂም እና የበቀል እርምጃ ሊወስድ ቻለ?

ልማታዊ አርቲስቶቻችን ይቅርታ አድርጉልኝና የአስተሳሰብና የአመለካከት ለውጥ ሳይኖር ቁሳዊ ለውጥ ይመጣል ብሎ የነገራችሁ ማን ይሆን? አመለካከታችን ካላደገ፣ እድገት ይታሰብ ይሆን?

ወደ ጉዳዩ ስንመለስ፣ ከፊንላንድ በኋላ ሌሎች ስድስት የአውሮፓ ከተሞች ላይ ኮንሰርቶች ተዘጋጅተዋል። ፕሮሞተሮች ለመሰናዶው ብዙ ወጪ አውጥተዋል። የአርቲስቱ አድናቂዎችም አስቀድመው ትኬት ቆርጠዋል። ይህንን ካድሬዎቹ ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ሁሉንም ማጉላላቱ፤ ከተቻለም ማደናቀፉ ደስታን ይሰጣቸዋል። እንዲህ አይነት የድፍረት ስሜት የሚመነጨው አርቲስቱን ሳይሆን ይልቁንም ሕዝብን በጅምላ ከማናቅ ነው። ሕዝብን ከመጥላት። እየገዙት ያሉትን ህዝብ መናቅና መጥላት የት ድረስ ሊያደርሳቸው እንደሚችል የምናየው ይሆናል። እንደ ሰብአዊ ፍጡር ሳይሆን እንደ እንስሳ የሚያስቡ እነዚህ የዘመናችን ጉዶች ሕዝብ የሚወደውን ነገር በሙሉ በመጥላት፤ የህዝብ አካል እንዳልሆኑ እይረጋገጡልን ነው። ከጫካ ከወጡ 21 አመታትን አስቆጥረዋል። አካላቸው ከጫካ ወጣ እንጂ አመለካከታቸው ግን እዛው እንደሆነ ድርጊታቸው ይነግረናል። ከሁለት ዓስርተ-ዓመት በኋላም ጥንት ከሚያስቡበት ከጫካው ህግ አልተላቀቁም።

ይህንን ትልቅ ሃገር እና ይህንን ትልቅ ሕዝብ እየመሩ ለምን እንደመንገስት ሊያስቡ እንደማይችሉ አይገባኝም። መንግስት ሆነው እንደግለሰብ ቂም ይይዛሉ። ቂም ይዘው እንደ ክፉ ሰው ይበቀላሉ። ሀገር ደግሞ በጥበብ እና በማስተዋል እንጂ፤ ከቶውንም በቂም እና በበቀል አትመራም። ይህንን የሚያደርጉ ሁሉ መጨረሻቸው ውድቀት፤ አወዳደቃቸውም የውርደት እንደሆነ ለደቂቃ አስተውለውት የሚያውቁ አይመስለኝም።

እንግዲህ ይህ ተራ ወንጀል በዚህ ድንቅ አርቲስት ላይ ሲፈጸም የመጀመርያ አይደለም። ከወራት በፊትም ወደ አሜሪካ ሊጓዝ ሲል የአየር መንገዱ ካድሬዎች ይዘው ብዙ አጉላልተውት ነበር። እርግጥ ነው ቴዲ አፍሮ ላይ ጥርሳቸውን ነክሰውበታል። ኤርምያስ ለገሰ፤ በ”መለስ ትሩፋቶች” መጽሃፉ ላይ የቴዲን ጉዳይ አንስቶ የገዢው ፓርቲ ሰዎች ይህንን አርቲስት እንዴት በክፉ አይን እንደሚመለከቱት ዳስሷል። ይህ አርቲስት ምናልባት በአንዲት ዜማ ተችቷቸው ይሆናል። እነሱም አላለፉትም። በፍትህ ስም የበቀል ዱላቸውን አሳርፈውበታል። ወህኒ ወርዷል። እስኪበቃቸውም ቀጥተውታል።

ቴዲ አፍሮ ግን ቂም አልቋጠረባቸውም። አሁንም የሚያቀነቅነው ስለ ፍቅር ነው። አሁንም የሚለው እንዲህ ነው። “ፍቅር ያሸንፋል!”

እነዚህ ሰዎች ሃያ ሁለት አመታት ሙሉ ከጥፋት አለመማራቸው ብቻ አይደለም የሚደንቀው። በአንድ ግለሰብ ምክንያት ከሚሊዮኖች ጋር እንደሚላተሙ አለማሰተዋላቸውም የሚገርም ነው። ለሟቹ ፓትሪያርክ ሲሉ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኦርቶዶክስ ምዕመናን ጋር ተቃርነው ነበር። አንድ የሙስሊም መጅሊስ መሪን ለመያዝ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሙስሊም ምዕመናን ጋር ጠፋጥተዋል።

ዛሬ አንድ ቴዲን ቢያንገላትቱት፣ ቢያግቱትም ሆነ ፓስፖርቱን ቢነጥቁት ለግዜውም ቢሆን የአድናቂዎቹን ስሜት ሊጎዱት ይችሉ ይሆናል። ይህ ድርጊታቸው ቴዲ አፍሮን ቅንጣት ያህል አይጎዳውም። ይልቁንም የበለጠ ተወዳጅ እና የበለጠ ጀግና ያደርገዋል። ከዚህ የፖለቲካ ንግድ እነሱ የሚያተርፉት ነገር ቢኖር የህዝብ ጥላቻን ነው። የቴዲን መታገት የሰሙ የገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ሳይቀሩ እንዲህ ሲሉ ተደመጡ፤ “አሁንስ አበዙት… ሃገራችንን እንድንጠላ አደረጉን….” ካድሬዎቹ ማህበራዊ ድረ-ገጾችን ቢጎበኙ የህዝቡን ስሜት ያነብቡ ነበር።

በሕዝብ አመኔታ ሳይሆን ይልቁንም በጆሮ ጠቢዎችና በመሳርያ በመተማመን እስካሁን ስልጣን ላይ ላላችሁት ገዢዎች ግን አንድ የምለው አለኝ። የፈረንሳዩ አንባገነን ናፖሊዮን ቦናፓርት የነበረውን ሰራዊት እስተውሉ። ይህ ግዙፍ እና የሰለጠነ ሰራዊት በህዝብ እንደ አሸዋ ተበተነ። የግብጹ ሆስኒ ሙባረክ ያልታሰበ እና ያልታለመ ውድቀት የመጣው እንዲሁ በመሳርያ ከመተማመን እና ህዝብን ከመናቅ ነበር። ይህ አስደንጋጭ ትዕይንት ለእናንተ ትምህርት ካልሰጣቸሁ የሱ እጣ ፈንታ ይጠብቃችኋል። መቶ አመት የቆየ አንባገነን ገዢ በታሪክ አላየንም።

ኢትዮጵያ ፋናዬን ትመስላለች –ሀገርና ልጆቿ እንዲህ በመከራ ሰጠሙ። (ሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 06.12.2014 /ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ/

እሜቴ ነፃነት እንደምን ከርመሻል?!

ከአምናው ሸክማሸክምሽ ዘንድሮ ብሶሻል ።

ዕንባነን አቅንተሽ ዘመን ሸኝተሻል ….

እትብትን ገብረሽ መከራ ወሮሻል። …

ያልፋልም ሳይመጣ እንዲህ ጠቋቁረሻል፤

የፋሽስቱ ኑሮ እንዲህ አሳሮሻል

ያገተው ተፈጥሮሽ – ራሄልን ሆኗል።

Teme & momየሀገሬ ልጆች እንዴት ናችሁልኝ? የዛሬን „የወያኔን የዱላ ቀን“ ሰበር ዜና ከዘሃበሻ እዬተከታተልኩ – እያነበብኩ የጻፍኩት ነው። ይህ ፎቶ ሀገራችን ከነውስጧ ይናገራልስለማያልቀው አሳሯ ይመስክራል። እያደር ስለሚጎላው የበቀል ዱላ ያብራራል። ኢትዮጵያ ለእኔ ፋናዬን ትመስላለች። አዛውንቷ እናት ሀገራችን ኢትዮጵያ እንዲህ በግራጫ ዘመኗ ክልትምትም ትላለች። ልጇ እንደ ናፈቃት፣ እንደሳሳት፣ ወጥቶ ሳይመለስ ይቀርባታል። በሰው እጅ ወድቆ በመከራ ስንቅነት ይቀጠቀጣል። ለንዳድ ወይ ለባሩድ ገጸ በረከት ይሰጣል። አዎን እናት ኢትዮጵያ ፋናዬን ትመስላለች ….

ዕድሜ ጠገቧ እመቤት ሀገራችን ኢትዮጵያ ዛሬ አልጋ አያስፈልጋትም – መሬት እንጂ። …. መቀነት አላስፈለጋትም ገመድ እንጂ፣ እህል አለስፈለጋትም – ፆም እንጂ፤ ደስታን አታቅድም ልጇቿ አሳራቸው ጠንቷልና፤ ሠርግ አያምራትም ልጃቿ ተስፋቸውን ተቀምተው ወጣትነታቸው ካቴና እንዲሆን  በአረመኔዎችና በጨካኞች ተገምድሎባቸዋልና *። ግን አቅሟ ያለው ከብሌኗ ስለሆነ ታነባለች – ሌትና ቀን። አዎን ልዕልተ ኢትዮጵያ እንዲህ ፋናዬን ትመስላለች ..

ልጇ ስጋቱ መንፈሱን ሲወጥረው ተንፍሶ ሃሳቡን ቢገልጽ  – ዱላ ነው፤ ወስፋቱ ሲንጫጫ፤ መጋኛው ሲተራመስ እራበኝ ብሎ ቢናገር – እርግጫ ነው፤ ጉሮሮው ድርቆ ሊያረጥብ ጠብታ ለምኖ ጠማኝ ለማለትም – ቅጥቀጣ ነው፤ ሌማቱ ድሆኖ* በባዶነቱ ሲያቅትቱ ኑሮን አልቻልኩም ቢል – መከትከት ነው፤ የተጣፈችው፣ ዘመን በልቷት አፍረተ ሥጋውን ለመከወን አቅም ያነሳትን ጥብቆ እያያት ከበላዩ ስታልቅ ታርዝኩኝ ቢልም –  ወንጀል ነው፤ የዘመን አራጣ ከፋይ ሆኗልና።

ሀገሬ፣ እናቴ ኢትዮጵያ ብሎ ደፍሮ ለመናገርም አሸባሪ“ ተብሎ ከርቸሌ ወይንም የባሩድ እራት ይሆናል፤ የማንነቴ መግለጫ ባርነትን ያለሳህኝ ባለውለታዬ ዓርማዬ ሰንደቄ እራቡንም ጥማቱንም በአንተው ልቻለው ብሎ ፈተናውን ለመተጋስ ሰንደቁን ቢለብስም የከፋ ጦር ይታዘዝበታል – ማረጃ ይሰናዳለታል።  ብሄርተኛ አክራሪ“ ነህ ተብሎ የፊጥኝ ታስሮ መፈጠሩን እስኪረግም ድረስ በዱላ ይቀጠቀጣል፤  ስለሆነም ዬልጇቻ ፍዳ እዬጠና መሄድ ያሳሰባት እናት ታወርደዋለች ዕንባዋን። …. እዬረጨችም በመማጸን … አዎ ኢትዮጵያ እንዲህ ናት ውስጧ ፋናዬን ትመስላለች።

መጣህልኝ ልጄ? ምን ይሻልህ? ደከመህ ወይ? አመመህን? የት አመሸህ? ቀረ … እንደ ራበ … ጠጋ ብሎ ጠረንን – ለጠረን እዬጣጣሙ በፍቅር እናታዊ ዓይን ልጅን መዳበስ – መዳሰስ – ማሻሸት- የፆም ውሃ ሆነ፤ ልጅና እናት የሆድ የሆድን ጧት ማታ ማውጋጋት ቀረ፤ የወጣነውም ብንሆን ቢታመሙ አንደርስ፤ ቢሞቱ አንቀብር እንደ ወጣን ቀረን፤  ሀገር ቤት ያለውም እንደ ወጣ ቀረ ጅቦቹ ኑሮውን ነጠቁት አራዊቶች ባዕቱን ቀሙት። ለፍዳው ዞን ተበጀለት። አዎ ኢትዮጵያ ዛሬ ያረረባት ፋናዬን ትመስላለች ….

እሷ የሚያስፈልጋት የፋካ የልጇ ጠረን ብቻ ነበር። ወጥታ ገብታ፣ አግኝታው፣ ቅርብ ብላ ጠረኑን መጠጣት። ድራ ኩላ ከጎረቤቱ፣ ከቤተዘመዱ ጋር ሐሤታን ተጋራታ ዓይኗን በዓይኗ ማዬት፤ የልጅ ልጅ መሳም፤ አዲስ የጋብቻ ዝምድና ፈጥራ ዝክሩን ማህበሩን ሞቅ ደመቅ አድርጋ በፈግጋታ ፍሬዋን መዬት ነበር፤ ለፍታ – ደክማ – ጠቁራ – ከስላ ያሳደገችው ለዚህ እንጂ ለበቀል ቁርስ ምሳና እራት አልነበረም። ግን ሆነ … እንዲህ ተስፋዋን አተነነው ዞገኛው ወያኔ።

ፍላጎቷን እንደ ህልሟ ማዬት እናት ሀገር ኢትዮጵያ አልቻለችም። ልጇ ለተለያዩ የቋሳ መፈተኛ እዬዋለ ነው። …. እያለ ሰውነቱ ዝሎ የራሴ የሚለው አካሉ ሸሽቶት ሞትን ናፈቀ። ይህን ታያለች አናት። የፈዘዘውን የልጇን አካል ታስተውላላች – እናት። ዬልጇ ክብሩ አካል ለአራዊት ፈንጠዝያ፤ ለባህር ሲሳይ፤ ይሄው ነው ኑሮዋ ኑሮ ከተባለ። …. ስለሆነም እንቅልፍ እልባዋ ቀንም ሌትም  በአሳር – ትፈተላለች። በጥቃት – ትባዘታለች። በሰቀቀን – ትወጋላች። ነገር ግን ሩቅ ታሰባለች። ቢሆንም እያች ግን የለችም። ሁለመናዋን መንፈሷን ሳይቀር ተነጥቃለች።  … አዎን እናት ሀገር ኢትዮጵያ ፋናዬን ትመስላለች ..

የፋናዬ ዕንባ ጅረት ነው፤ የአባይ ፏፏቴ ነው። …  ይነጉዳል ዘመንን እዬወቀሰ። ይሄዳል … ዘመንን እዬነቀሰ፤ ፈጣሪን ግን ተማጽኖ – መጪውን ዘመኑን በርኮ ከበለኃሰቦች እንዲታደግ እያሳሰበ … ጠብታዋ ጉዞውን አሁንም ቀጥሏል – እዬተከዘ። አያልቅበት ይፈሳል … መከራው የሚያልቅበትን ቀን ያልማል፤ ፍዳው የሚቋጭበትን ሁኔታ ያሰላል …. ዋናው በዕንባ ወንዝነት …. ይሠግራል ….

ተፋሰሱ አልፎ ደረቷን እራስ ሲያደርገው፤ ተፋሰሱ ቀጥሎ ዕንብረቷን ሲጎበኘው። ያን ጊዜ እትብቱና መከራው ተገናኝተው ያወጋሉ፤ ማለፊያውን ቀን ያልማሉ። እንደ ገና በህቅታ ቃና እና ሲቃ የፈላ አዲስ ፋፋቴ ይተካል። እኔ እቀድም እኔ እቀድም በአዲስ ጉልበት ይሯሯጣሉ። ገደቡን ጥሶ ይለቀቃል …. አዎን ኢትዮጵያ ፋናዬን ትመስላላች ….

ዱላው ቀጥላሏ፤ ዛሬም የዱላ ቀን ነው። ነገም እንዲሁ … ግን ሲከር ይበጣሳል ሲሞላም ይፈሳል። እግዚአብሄር ይስጥልኝ – ኑሩልኝ  የእኔዎቹ። የራሄልን ዕንባ የታደገ ዕንባ የፋናዬንም ይታደግ! አሜን! አዛውንቷ ፋናዬ ልዕልት ኢትዮጵያ ናትና ….

መፍቻ * መገምደል …  ኢ – ፍታህዊነት፤ ኢ – ህጋዊነት የወረረው ጋድም ዳኝነት።

* ድሆኖ ከጭቃ የተሠራ የእንጀራ መያዣ፤ ነገር ግን ጉዝጓዝ ጥሬ ሽንብራ ወይንም የቁንዶ በርበሬ ዛላ ቅጠል ወይንም  ባህርዛፍ ቅጠል ወይንም እንሰት /ኮባ/ ቅጠል ከሥር ያስፈልገዋል። በዘመነ ደረቁ ለምለም ስለመኖሩ ግን አላውቅም።                

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

በአገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ ትግላችን አይቆምም! –ከትብብሩ የተሰጠ መግለጫ

$
0
0

addis ababa semayawi partyየ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ባለፈው አንድ ወር ‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል መርሃ ግብር ቀርጸን ስንቀሳቀስ ዋናው አላማችን የስርዓቱን አረመኔያዊነት ለህዝብ በማጋለጥ የኢትዮጵያ ህዝብ በትግሉ እንዲሳተፍ ማድረግ ነው፡፡ እንደጠበቅነው ገና ከጅምሩ የህወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ትግላችንን በጭካኔ ለማስቆም ጥሯል፡፡ ህዳር 7/2007 ዓ.ም የመጀመሪውን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በጠራንበት ወቅት ስብሰባውን በኃይል በትኗል፡፡

ትብብራችን ከመቸውም ጊዜ በላይ ያሰጋው ህወሓት/ኢህአዴግ በተለይ የህዳር 27/28 2007 ዓ.ም የአደባባይ አዳር ሰልፍን እንዳይካሄድ የትብብሩን አመራሮችና አባላቶቻችን በማዋከብ፣ በመደብደብና በማሰር ተጠምዶ ሰንብቷል፡፡ በተለይ በትናንትናው ዕለት ሰልፍ በወጣንበት ወቅት ስርዓቱ አመራሮችንን፣ አባላቶቻችንን፣ ተሳታፊዎችንን እንዲሁም አልፎ ተርፎ መንገደኛውን ህዝብ በጭካኔ ደብድቧል፡፡ አፍሶ አስሯል፡፡ ሙስሊም እህትና ወንድሞቻችን በየጎዳናው ታፍሰው የአገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ ሰለባዎች ሆነዋል፡፡ በርካቶችም በእ
በየ እስር ቤቶቹ ታጉረዋል፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ ከ300 በላይ የትብብሩ አመራሮችና አባላት የታሰሩ ሲሆን የትብብሩና የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበርን ጨምሮ በርካታ አመራሮች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ድርሶባቸዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆነው አቤል ኤፍሬም ራሱን እስኪስት ተደብድቧል፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ የተገኙ ሴት አመራርና አባላት አንድ አገርን እየመራሁ ነው ከሚል አካል በማይጠበቅ መንገድ በጭካኔ ተደብድዋል፡፡ እነዚህ በጭካኔ የተደበደቡ አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ህክምና እንዳያገኙ ተከልክለዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በጥበቃ ሰራተኝነት የሚሰሩ የ72 አመቱ አቶ ቀኖ አባጆቢር ከስራ ሲወጡ በደህንነት ኃይሎች ታፍነው የተወሰዱና እስካሁን የት እንደደረሱ ያልታወቀ ሲሆን ይህም አገዛዙ የመጨረሻው የአረመኔነት ደረጃ ላይ እንደደረሰና ይህን የስርዓቱ ውንብድና ለማስቆም ጊዜ የማይሰጠው ተግባር መሆኑን በግልጽ የተገነዘብንበት ነው፡፡

አገዛዙ በትናንትናው ዕለት በፍጹም ሰላማዊ ሰዎች ላይ የወሰደው የውንብድና እና አረመኔያዊ እርምጃ በትግሉ ውስጥ የምንጠብቀውና ስርዓቱ ለኢትዮጵያ የማይበጅ መሆኑን ዳግመኛ ያያ

ረጋገጠበት ነው፡፡ የትናንትናው ትላችን አገዛዙ ለይስሙላ እከተለዋለሁ ከሚለው ‹‹ህጋዊ ሰርዓት›› ይልቅ ስልጣኑን በኃይል ለማስጠበቅ ቆርጦ መነሳቱን እና በህገ መንግስት ስም ህዝብን የሚበድልበትን የአረመኔያዊነት ጭንብል ገልጠን ለዓለም ያሳየንበት የትግላችን ውጤት ነው፡፡

አገዛዙ ላላፉት 24 አመታት ስልጣኑን በኃይል ለማስጠበቅ ሲጥር ቆይቷል፡፡ በትናንትናው ዕለት የፈጸመው ፍጹም አረመኔያዊ እርምጃም እንደተለመደው ሰላማዊ ታጋዮችን ያሸማቅቃል ብሎ አስቦ እንደሆነ እሙን ነው፡፡ ነገር ግን ይህ የአገዛዙ አረመኔያዊነት ከሰላማዊነታችን ፍጹም ወደኋላ ሊያንሸራትተን አይችልም፡፡ ወደ ትግል ስንገባ የስርዓቱን ጭካኔና ለኢትዮጵያ የ

ማይመጥን መሆኑን አውቀንና የሚያስከፍለውን መስዋዕትነት ለመክፈል ተዘጋጅተንም ነው፡፡ አሁንም አገዛዙ የህዝብን ድምጽ በማፈን ስልጣኑን ለማስጠበቅ ተመሳሳይ እርምጃ እንደሚወስድ እንጠብቃለን፡፡ ነገር ግን መጀመሪያውንም ትግሉን ስንቀላቀል አስበን የገባነው እየቆሰልን፣ እየታሰርንም፣ እየሞትንም ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ ለመሆን ነውና ከትግላችን ቅንጣት ሊያደናቅፈን አይችልም፡፡ ስለሆነም ወደፊትም ይህን የአገዛዙን አረመኔያዊነት በማጋለጥና ህዝቡን በትግሉ በማሳተፍ ለኢትዮጵያ የሚገባት ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመመስረት በቀጣይነትም ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነን፡፡

በዚህ አጋጣሚ ሰላማዊ ሰልፉን ለማሳካት እንዲሁም የህወሓት/ኢህአዴግ ቡድን የፈጸመውን ጭካኔ በማውገዝ ከጎናችን ለቆማችሁ ሁሉ ምስጋናችን የላቀ ነው፡፡ ከህወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ጋር የሚደረገው ትግል እልህ አስጨራሽ፣ ከፍተኛ መስዋዕትነት የሚያስከፍልና የእያንንዳንዳችን ትብብር የሚጠይቅ መሆኑን ተገንዝበን ሁላችንም በጋራ እንድንቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን

ያለ መስዋዕትነት ድል የለም፡፡

ብርሀነ መስቀል ረዳን በጨረፍታ

$
0
0

ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—-
በዩኒቨርሲቲ ቆይታዬ (ከ1989-እስከ 1992 በነበረው ጊዜ) “ሐቄ” የምትባል ልጅ አውቃለሁ፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት የሴቶች ጉዳይ ሃላፊ የነበረችው (በኋላ በኮትዲቯር የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆነችው) ወ/ሮ ታደለች ሀይለሚካኤል የዚያች ልጅ እናት እንደነበረች ይወሳ ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ የባለስልጣን ልጅ መሆኗን በመፍራት ብቻ ብዙዎች አይጠጓትም ነበር፡፡ ከልጅቷ ጋር የሚቀራረበው ተወልደ መዝገቡ የሚባል የአዲግራት ልጅ ብቻ እንደነበረ አስታውሳለሁ፡፡

BerhaneMeskael Reda የዩኒቨርሲቲው ትምህርት ከተጠናቀቀ ከጥቂት ወራት በኋላ መጽሔቶችን ሳገላብጥ ያቺ ልጅ ለምልክት ከሞት የተረፈች የፈጣሪ ተአምር እንደሆነች ተረዳሁ፡፡ አባቷ ነፍሲያውን ሊጠነቅ በተቃረበበት ወቅት ታሪኩን ትመሰክር ዘንድ የዘራት ብቸኛ ፍሬው ነበረች፡፡ ብዙዎች በእናቷ ሆድ የነበረችበትን ጊዜ በብዕራቸው ነካክተውታል፡፡ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያም በበኩላቸው ያቺ ነፍስ በእናቷ ሆድ ውስጥ በመገኘቷ እናቷን ከሞት ያተረፈች መሆኗን መስክረውላታል፡፡ ለዚህም ይመስላል እናቷ “ሐቄ” የሚለውን ስም የሰጠቻት፡፡

ህይወት ተፈራ Tower in the sky የተባለውን መጽሐፍ ስትጽፍ ለዚያች ልጅ መጠነኛ ሽፋን ሰጥታለች፡፡ ከእናቷ ጋር የተነሳችውንም ፎቶግራፍ በመጽሐፉ ውስጥ አካተዋለች፡፡
*****
በፎቶግራፉ ላይ የምትመለከቱት የዚያች ልጅ አባት የነበረውን ሰው ነው፡፡ ይህ ሰው ከታሪካዊው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ መሪዎች መካከል አንዱ የነበረውና የመጀመሪያው የኢህአፓ ዋና ጸሓፊ ሆኖ የተመረጠው ብርሀነ መስቀል ረዳ ነው፡፡ ለብዙሃን ህይወት መለወጥ በብርቱ የታገለ፣ ሁለቱን ጠንካራ ስርዓቶች ፊት ለፊት የተጋፈጠ፣ ላመነበት ዓላማ ትምህርቱን ሰውቶ መታገልን የመረጠ፣ ከሀገር ወጥቶ በሰው ሀገርና በበረሃ የተንከራተተ፣ በመጨረሻ ላይ ግን ከገዛ ጓዶቹ ጋር ተጣልቶ የራሱን መንገድ የመረጠ፣ በዚህም ከፍተኛ የውዝግብ ርዕስ ለመሆን የበቃ የዚያ ዘመን ፋኖ!…

ብርሀነ መስቀል ማን ነው?… በኢትዮጵያ ህዝቦች የፖለቲካ ትግል ውስጥ ምን ሚና ነበረው?… የርሱ ህይወትና የትግል መንገድ እንዴት ይገመገማል?… እነኝህ በኔ አቅም የሚመለሱ ጥያቄዎች አይደሉም፡፡ ታሪኩ እስከ አሁን ድረስ እያወዛገበ ስለሆነ ሐቁን ከግርድፉ ማጣራቱ ከባድ ጥረት ይጠይቃል፡፡ ብርሀነ መስቀል በወዳጆቹም ሆነ በጠላቶቹ የሚከበርና የሚፈራ መሆኑን ግን ማንም አያስተባብልም፡፡ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም በእስር ቤት አናዝዘውት ከገደሉት በኋላ “የመርሐቤቴ ገበሬዎች ገደሉት” እያሉ ለመዋሸት ቢሞክሩም በኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ውስጥ የነበረውን ሚና በአዎንታዊ መልኩ ነው የገለጹት፡፡ በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የቅርብ ጓደኛው የነበሩት አንጋፋው ገጣሚና ባለቅኔ ኃይሉ ገብረ-ዮሐንስ (ገሞራው) “ችኩል እና ቁጡ ከመሆኑ በስተቀር ለሀገር መሪነት የሚበቃ ስብዕና ነበረው” በማለት መስክረውለታል፡፡

ከሁሉም በላይ የብርሀነ መስቀልን ቆራጥነትና ልዩ ተሰጥኦ ሰፋ ባለ ሁኔታ የገለጹት የኢህአፓው ክፍሉ ታደሰ ነበሩ፡፡ አቶ ክፍሉ “ያ ትውልድ” በተሰኘውና በከፍተኛ ደረጃ ተነባቢ ለመሆን በበቃው መጽሐፋቸው “ብርሀነ መስቀል በኢህአፓ ውስጥ የራሱን አንጃ ፈጥሯል” የሚል ክስ እያቀረቡበት እንኳ ለትግሉ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በተዋቡ ቃላት ገልጸዋል፡፡ ለምሳሌ ያህል የሚከተለውን መጥቀስ ይቻላል፡፡
“በተማሪው እንቅስቃሴ ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተውና አንደበተ ርቱእ የሆነው ብርሃነ መስቀል፣ በእንቅስቃሴው ውስጥ ሲታሰርና ሲፈታ የኖረ ነው” (ክፍሉ ታደሰ፣ ያ ትውልድ፣ ገጽ- 144)
*****
ብርሀነ መስቀል ለደርግ መርማሪዎች የሰጠው ቃል ሰሞኑን በኢንተርኔት ተበትኖ የብዙዎች መነጋገሪያ ሆኗል፡፡ እኔም ይህ 98 ገጾች ያሉት የምርመራ ቃል ከአንድ የፌስቡክ ጓደኛዬ ደርሶኝ እያነበብኩት ነው (ሙሉውን ዶክመንት www.zehabesha.com ከተሰኘ ዌብሳይት ማግኘት ትችላላችሁ)፡፡ እስከ አሁን ድረስ 1/3ኛ ያህሉን አገባድጄዋለሁ፡፡ ይሁንና ፊት ከማውቀው የብርሀነ መስቀል ታሪክ የተለየ ነገር አላገኘሁበትም፡፡ በሚቀጥሉት ቀናት አትኩሮት የሚስቡ መረጃዎችን ካገኘሁበት ልመለስ እችላለሁ፡፡ እስከዚያው ግን ስለብርሀነ መስቀል በትንሹ ላውጋችሁ፡፡

ብርሃነ መስቀል ረዳ ወልደ-ሩፋኤል በ1930ዎቹ አጋማሽ በትግራይ ገጠር ነው የተወለደው፡፡ ያደገው ግን በደሴ ከተማ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ በነበሩት አጎቱ ቤት ነው፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደሴ በሚገኘው የወይዘሮ ስሒን ት/ቤት ካጠናቀቀ በኋላ በ1955 ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገብቷል፡፡ በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ትምህርቱን ከመከታተል ይልቅ ተማሪዎችን ለተቃውሞ በማንቀሳቀሱ ላይ ነበር ያተኮረው፡፡ በዚህም መሰረት ወደ ዩኒቨርሲቲው እንደገባ ከርሱ ቀደም ብለው “አዞዎቹ” በሚል ቡድን ዙሪያ የተሰባሰቡትን የስር-ነቀል ለውጥ ደጋፊ ተማሪዎችን ለመቀላቀል በቅቷል፡፡ ከዓመት በኋላ በ1956 በዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተማሪዎች ህብረት ውስጥ የመረጃ ኦፊሰር ሆኖ ተመርጧል፡፡ በአመቱ ደግሞ የብሔራዊ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ዋና ጸሓፊ ሆኖ ነበር፡፡

ብርሃነ መስቀል በ1957 የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች “መሬት ላራሹ” የሚል መፈክር አንግበው ድምጻቸውን ለፓርላማ ያሰሙበትን ታሪካዊ ሰልፍ ካደራጁት መካከልም ነበር፡፡ በዚያ ሰልፍ ሳቢያ ከትምህርታቸው ከተባረሩት ዘጠኝ ተማሪዎች መካከልም አንዱ ነው (በወቅቱ ከርሱ ጋር የተባረሩት ገብሩ ገብረወልድ፣ ሀይሉ ገብረዮሐንስ፣ ዮሐንስ ስብሐቱ፣ ታዬ ጉርሙ፣ ዘርዑ ክህሸን፣ ስዩም ወልደ ዮሐንስ፣ ሀብቴ ወልደ ጊዮርጊስና ሚካኤል አበበ ናቸው)፡፡ እነዚያ ተማሪዎች ከአንድ ዓመት በኋላ ወደ ዩኒቨርሲቲው ቢመለሱም በተረጋጋ ሁኔታ ትምህርታቸውን መከታተል አልቻሉም፡፡ በየጊዜው በሚካሄዱት ሰልፎችና የተቃውሞ ስብሰባዎች ግንባር ቀደም ተጠያቂ እየሆኑ ይታሰሩ ነበር፡፡ በስተመጨረሻ ግን የ“አዞዎቹ” ቡድን አባላት ከነአካቴው ከዩኒቨርሲቲው ተባረሩ፡፡ በመሆኑም በተደራጀ ሁኔታ ለመታገል ወሰኑ፡፡

በዚህም መሰረት ብርሃነ መስቀልና አምስት ጓደኞቹ ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ የሚበር አንድ አውሮፕላን በመጥለፍ ወደ ካርቱም ኮበለሉ፡፡ ከጥቂት ወራት በኋላም ወደ አልጄሪያ ተሻገሩ፡፡ በአልጀርስ ቆይታቸው እጅግ ቀስቃሸ የሆኑ ጽሑፎችን እያዘጋጁ ወደ ሀገር ቤት ይልኩ ጀመር (በዚያ ዘመን “ጥላሁን ታከለ” በሚል የብዕር ስም በመጠቀም አስደናቂ ጽሑፎችን ይጽፍ የነበረው ብርሃነ መስቀል ረዳ እንደሆነ ነው የሚታመነው)፡፡ በአልጄሪያ የነበሩት ስደተኛ አብዮተኞች በውጪው ዓለም ትምህርታቸውን ከሚከታተሉ ኢትዮጵያዊያን ጋር በሚያደርጓቸው ግንኙነቶች በተደራጀ መንገድ የሚታገሉበትን መንገድ ቀየሱ፡፡ እነዚያ ውይይቶች እያደጉ ሄደው በ1964 ኢህአድ (የኢትዮጵያ ህዝብ አርነት ድርጅት) የተሰኘ ህቡዕ ፓርቲ ተወለደ፡፡ ብርሀነ መስቀል ረዳም የድርጅቱ ዋና ጸሐፊ ሆኖ ተመረጠ (የድርጅቱ ስም በ1967 “የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ” በሚል ተለውጧል፤ ይህም በአህጽሮት “ኢህአፓ” የሚባለው ነው)፡፡

ብርሀነ መስቀል የኢህአድ ዋና ጸሓፊ በነበረበት የመጀመሪያ ዓመት በአብዛኛው ፓርቲውን የማስተዋወቅና ድጋፍ የመፈለግ ስራዎችን ነበር የሰራው፡፡ በዚህም ከአውሮፓ እስከ መካከለኛው ምስራቅ ድረስ ተጉዟል፡፡ ከባለቤቱ ታደለች ሀይለሚካኤል ጋር የተዋወቀው በዚያን ጊዜ ነው፡፡ በ1966 ብርሃነ መስቀልና ጥቂት ሰዎች የድርጅቱን የትጥቅ ትግል እንዲጀምሩ ወደ ኤርትራ ተላኩ፡፡ ወታደራዊ ስልጠና ለመውሰድ ለአንድ ዓመት በኤርትራ ከቆዩ በኋላ በ1967 መጀመሪያ ላይ ትግራይ ውስጥ ወደሚገኘው አሲምባ ተራራ ተሻገሩ፡፡ ሆኖም የትጥቅ ትግሉን ሳይጀምሩ በአሲምባ ቤዛቸው ለስድስት ወራት ቆዩ፡፡ በዚህ መሀል ስምንት ያህል የቡድኑ አባላት ከብርሀነ መስቀል ጋር የነበራቸውን ቀየሜታ በማሳበብ ድርጅቱን ጥለው ለደርግ መንግሥት እጃቸውን ሰጡ፡፡ ብርሀነ መስቀል በፋኖዎቹ አድራጎት በመቆጣቱ በሌሉበት የሞት ፍርድ ፈረደባቸው፡፡ ሆኖም ይህ ውሳኔው ከሌሎች የኢህአፓ አባላት ተቃውሞ ገጠመው፡፡ የኢህአፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጉዳዩን ካጣራ በኋላ በሰዎቹ ላይ የተላለፈው የሞት ፍርድ እንዲነሳ ወሰነ፡፡ ብርሀነ መስቀልም ከሰራዊቱ ተነጥሎ ወደ አዲስ አበባ እንዲሄድ ተወሰነ፡፡ ይህም በብርሀነ መስቀልና በሌሎቹ የኢህአፓ መሪዎች መካከል ንትርክ ፈጠረ፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ በነሐሴ ወር 1967 አህአፓ ራሱን በአዲስ መልክና በአዲስ ስም ሲያደራጅ “ዋና ጸሐፊ” የሚባል የስልጣን እርከን ተሰረዘ፡፡ ድርጅቱ ሊቀመንበርም ሆነ ዋና ጸሐፊ የለውም ተብሎ ታወጀ፡፡ ብርሀነ መስቀል ይህንን እርምጃ እርሱን ከቦታው ለማንሳት የተሸረበ ሴራ አድርጎ ስለወሰደው ከፍተኛ ቅሬታ አደረበት፡፡ ከማዕከላዊ ኮሚቴው ጋር የሚያደርገውንም ግንኙነት ማቀዝቀዝ ጀመረ፡፡ የደርግ መንግሥት በሚያዚያ ወር 1968 በህቡዕ ለተደራጁ ድርጅቶች ሁሉ የግንባር ጥሪ ሲያደርግ ብዙሃኑ የኢህአፓ አመራር ጥሪውን በመሰረቱ እንደሚቀበል ከገለጸ በኋላ መሟላት ያለባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች አስቀመጠ፡፡ እነዚያ ሁኔታዎች ካልተሟሉ በስተቀር ከደርግ መንግሥት ጋር እንደማይሰራ ገለጸ፡፡ ብርሀነ መስቀል ግን “ቅድመ- ሁኔታ ማስቀመጡ ልክ አይደለም” በማለት ተከራከረ፡፡ በነሐሴ ወር 1968 የኢህአፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ “ራሳችንን ለመከላከል የከተማ ትጥቅ ትግል ማድረግ አለብን” በማለት ሲወስን ብርሀነ መስቀል “ውሳኔው አደገኛ ነው፤ ኢህአፓን ያስመታል፤ ደግሞም ደርግ ማርክሳዊ ነኝ ብሎ ያወጀ መንግሥት ስለሆነ ማርክሳዊ መንግሥትን በትጥቅ አመጽ መቃወም የአብዮታዊያን ጸባይ አይደለም” በማለት በብርቱ ተቃወመው፡፡ ይህም ታቃውሞ ከኢህአፓ አመራር ጋር እስከ ወዲያኛው አቆራረጠው፡፡

የኢህአፓ አመራር ብርሀነ መስቀል ያሳያቸውን የአቋም ልዩነቶች ከገመገመ በኋላ ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነቱ ሰረዘው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላም “ብርሀነ መስቀል በፓርቲው ውስጥ የራሱን አንጃ ለመመስረት ጥረት እያደረገ ነው” የሚል ክስ አቀረበበት፡፡ በድርጅቱ ጋዜጦች ላይ ግለ-ሂስ እንዲያደርግም አዘዘው፡፡ ብርሀነ መስቀልም ሂሱን ካወረደ በኋላ በድርጅቱ ታጣቂዎች እንዲጠበቅ ተደረገ፡፡ በሚያዚያ 1969 ግን ለማንም ግልጽ ባልሆነ መንገድ ከአዲስ አበባ ከተማ ተሰውሮ ወደ መርሐቤቴ አውራጃ ገባ፡፡ እዚያም ከተወሰኑ ሰዎች ጋር የትጥቅ ትግል ለማድረግ ሞከረ፡፡ ይሁን እንጂ በእርምጃው ከጥቂት ወራት በላይ አልዘለቀም፡፡ የደርግ አዳኝ ሀይሎች በ1970 መጀመሪያ ላይ ይዘውት ወደ አዲስ አበባ አመጡት፡፡ ለአንድ ዓመት ከሰድስት ወራት ያህል በታላቁ ቤተ መንግሥት ከታሰረ በኋላ በሚስጢር ተገደለ፡፡
*****
የብርሀነ መስቀል አንጃ የመፍጠር ሙከራ በራሱም አንደበት የተረጋገጠ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ብርሀነ መስቀል “እኔ ያካሄድኩት የእርማት ንቅናቄ እንጂ ፓርቲውን ለማጥፋት ያለመ አንጃ አልፈጠርኩም” ባይ ነው፡፡ በተጨማሪም ባለቤቱ ወይዘሮ ታደለች ሀይለ ሚካኤል በአንድ ወቅት በሰጡት ቃለ ምልልስ ብርሀነ መስቀል የእርማት ንቅናቄ ለማካሄድ መሞከሩን ተናግረዋል፡፡ በዚያ ዘመን በርሱ ስም የተሰራጩትን ልዩ ልዩ ዶክመንቶች በሙሉ የርሱ ናቸው ለማለት ይከብዳል፡፡ አንደኛው ጽሑፍ ግን በርሱ እጅ ጽሑፍ የተጻፈ መሆኑ ስለሚታወቅ የርሱን እምነት ይገልጻል ተብሎ ይታመናል፡፡ ብርሀነ መስቀል በዚያ ጽሑፉ የኢህፓን አመራር ቢኮንንም ደርግንም በሚገባ ይቃወማል፡፡ እንዲሁም በርሱ ስም ድርጅቱን የበጠበጡ በርካታ ቅጥረኞች እንደነበሩም ያወሳል፡፡ ሆኖም የኢህአፓ አመራር እርሱ ያለውን አምኖ የተቀበለው አይመስልም፡፡ ኢህአፓዎች “ለድርጅቱ ብተና ፈር የቀደደ ከሀዲ ነው” ነው የሚሉት፡፡

ማንም የማይክደው አንድ ሐቅ ግን አለ፡፡ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ሲነሳ ብርሀነ መስቀልን መርሳት በጭራሽ አይሞከርም፡፡ በርካታ የለውጥ ፈላጊው ትውልድ አባላት የርሱን አርአያ በመከተል ወደ ትግሉ ጎራ መቀላቀላቸውንም ማስተባበል አይቻልም፡፡ ስለዚህ ምሁራን በቅጡ ያልተመረመውን የዚህን ፋኖ ታሪክ ጎልጎለው በትግሉ ውስጥ የነበረውን አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ሚና ሳይሸፋፍኑ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
*****
አፈንዲ ሙተቂ
ህዳር 28/2006


ከብሔረሰብ በዓል ወደ ለታላቁ ሩጫ! –በእውቀቱ ስዩም

$
0
0

beweketu
ከአምስት ዓመት በፊት ይመስለኛል፣ በደቡብ የሚገኝ የግብርና ዩንቨርሲቲ የብሔር ብሔረሰቦቸን ቀን ምክንያት በማደረግ የክብር አንግዳ አድርጎ ጠራኝ። ትንሽ ካቅማማሁ በኋላ ማየት አይከፋም ብየ ሚኒባስ ተሣፈርሁ። ካምፓስ እንደ ደረስሁ የምግብ ትርኢት ወደ ሚካሄድበት ትልቅ አዳራሽ መሩኝ። ባዳራሹ ትልቅ የግብር ማብያ ጠረጴዛላይ ብሔሮችን የሚወክሉ መብሎችና መጠጦች ተደርድረዋል። ሁሉንም ብሔር ላለማስከፋት ሰማንያ ጉርሻ መጉረስ ይጠበቅብኝ ይሆን በማለት በልቤ እያጉረመረምሁ ለቅምሻ ተሰናዳሁ። ሥጋና ወተት የሁሉም የኢትዮጵያ ብሔሮች ተወዳጅ ምግቦች መሆናቸውን ለመጀመሪያ ጊዜ አስተዋልሁ። ያም ሆኖ፣ ተማሪ ሁላ የራሱን ብሔር ምግብ ልዩ ግኝት አድርጎ ሊያሳይ ይጥራል። አንዱ በተለጎመ ቅል ያቀረበውን ወተት፣ሌላው በሸክላ ጥዋ ያቀርበዋል። አልተሸወድሁም። ወተቱም የላሚቱ ፣ ቅሉም የተፈጥሮ ግኝት እንደሆነ አውቃለሁ።

ቀጣዩ ፕሮግራም፤የብሔር ብሔረሰቦችን ባህላዊ ትርኢት ማየት ነበር። በዩንቨርሲቲው አነስተኛ ስቴድየም ውስጥ በተዘጋጀልኝ ቦታ ላይ ጉብ አልሁ። ስቴድየሙ የተለያዩ የብሔረሰብ ዩኒፎርሞች በለበሱ ተማሪዎች ተሞልቷል። ተሜ ፣እዚም እዚያም ትንንሽ የሰው ደሴት ሰርታ ፣ ወልመጥ ወልመጥ እያለች ጭፈራውን ታስነካዋለች። ብሔረሰብ ይወክላል ተብሎ የሚታሰብ ጥንታዊ እቃ የቀረ አይመስልም። መንሽ፣ጎፈር፣አጎዛ፣አንቀልባ፣አገልግል፣ ሞፈርና ቀንበር፣ጦርና ጋሻ፣ቆልማማ ጩቤ፣ መውዚር ጠመንጃ በየተማሪው እጅ አለ። እንድያውም፣ትንሽ ብጠብቅ የድሮ መድፍ ከነመንኮራኩሩ ሲገባ ማየቴ አይቀርም ነበር።

ዝግጅቱ ተጀመረ። አራት ጎረምሳ ተማሪዎች ርቃን ሰውነታቸውን እንደ ጥምቀት ሽመል አዝጎርጉረው እንጣጥ እንጣጥ እያሉ ባጠገቤ አለፉ። የያዙት አርማ የኦሞ ሸለቆ ብሄሮች ይላል። አንዱን አተኩሬ ሳየው ሸገር የማውቀው መሰለኝ። መጠራጠሬን የታዘበ አጠገቤ የተቀመጠ ተማሪ ምስጢሩን ተነፈሰልኝ፤‹‹የሰውነታቸውን ቅርጽ ለሴቶች ለማሳየት ብለው፣እንደ ኦሞ ለብሰው ነው እንጂ አራቱም የቦሌ ልጆች ናቸው›› አለኝ ።
በነገሩ የሌሉበት ሌሎች ተማሪዎች በስቴድየሙ ዙርያ ተበትነው፣የባለንጀሮቻቸውን ጫንቃ ተደግፈው ከፊታቸው የሚካሄደውን በጥርጣሬ ይመለከታሉ። እኔም መመልከቴን ቀጠልሁ። ከጥቂት ሰላም በሁዋላ አንድ ችግር ተፈጠረ።የትኛው ብሔር ቀድሞ ይለፍ የሚለው ጥያቄ በሁለት ብሔሮች መሀል ውጥረት ለኮሰ። አንዱ ተማሪ የሌላውን ተማሪ ባህላዊ ኮሌታ ጨምድዶ ይዞ ሲተናነቅ አየሁት። ሌሎች ተማሪዎች ለማገላገል ሙከራ ያደርጉ ጀመር። አቧራው መጠብደል ሲጀምር ስጋት ሰቅዞ ያዘኝ። የግቢውን ውበት የማደንቅ መስየ ድብድቡ ሲጀመር ወጥቼ ማመልጥበትን ቀዳዳ መፈለግ ጀመርሁ። በዚህ ዓይነት፣ ለብሔረሰብ በአል መጥቼ፣ለታላቁ ሩጫ ራሴን ሳሟሙቅ፣ ሽማግሌ ገባና ነገሩን አበረደው።

ሰሞኑን ባንድ ዩንቨርሲቲ ግቢ ብሔር መራሽ አምባጓሮ ተቀሰቀሰ ሲሉኝ ትዝ ያለኝ ይሄ ነው። እንደምታውቁት የብሔርና የእግዚአብሔር ነገር ኢትዮጵያ ውስጥ፣ለወሬ አይመቹም። Taboo ናቸው ለማለት ነው። ለደንበኛ ውይይት ሲቀርቡ ሰዎች ይቆጣሉ። ግን ዝምታ፣ የችግሮቻችንን ጥፍርና ክራንቻ ከማሳደግ በቀር ጥቅም የለውም። ወደድንም ጠላንም አገርን ከሥር የሚነቅል ጠብ የሚያስነሡ ሁለቱ ነገሮች ናቸው።

ታላቁ እስክንድር

$
0
0

ከኢዮኤል ፍሰሐ

ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰው ድሃ አይደለችም። በየጊዜው ሰው ይወጣላታል። በእሷ ፍቅር የከነፉ ልጆችን ሁሌም ቢሆን አታጣም። እማማ እንደዚህ አይነት ልጆቿን አምጣ ትወልዳቸዋለች። በእርግጥ ሁላችንም ተምጠን ብንወለድም ፣ ለእሷ ራሳቸውን አሳልፈው ሊሰጧት የተዘጋጁትን ግን ከሁላችንም በከፋ ምጥ ውስጥ ትወልዳችዋለች። ለዛሬ ከእነዚህ እማማ ኢትዮጲያ በከፋ ምጥ ውስጥ ከወለደቻቸው ጀግኖች መሃል የሚመደበውን እስክንድር እንቃኛለን።
Eskinder-Nega
እስክንድር ነጋ ከራሱ ይልቅ የሀገሩን ጥቅም የሚያስቀድም ፣ በሀገሩ ጉዳይ ባይተዋርነት የማያጠቃው ፣ ለግለሰብ ልዕልና የሚታገል ፣ ነጻነትን አጥብቆ የሚፈልግና ለዛም ዋጋ እየከፈለ የሚገኝ ታጋይ ነው። እስክንድር ፣ ላመነበት ነገር ዋጋ እንደሚከፍል በተግባር ያሳየ ሰው ነው። ‹‹ለውጥ ያለመስዋዕትነት አይገኝም። ነጻነታችንን የምንፈልገው ከሆነ ደግሞ እያንዳንዳችን ዋጋ ልንከፍል ይገባል›› ይላል። ይህ ሰው ለነጻነቱ ሲሟገት ሚስቱና ልጆቹን በስደት ተነጥቆ ስጋውን ደግሞ ቃሊቲ አድርጎ ነው። ቃሊቲ ውስጥ ሆኖም ስጋው እንጂ መንፈሱ እንዳልታሰረ በሚገባ ያስታውቃል። አርቆ አሳቢነቱ ፣ አስተዋይነቱና ከአሉታዊ ነገሮች ውስጥ እንኳ አዎንታዊ ነገሮችን የማውጣት ብቃቱ ልዩ ነው። ሰውንም በሰውነቱ ያስተናግዳል። ሁሉንም ሰው በእኩል አይን ማየት ይችላል። እስክንድር ዘንድ ዶክተር ፣ ኢንጅነር ፣ አርቲስት ፣ ጋዜጠኛ ፣ አትሌት ወዘተ…… ሁሉም እኩል ናቸው። ለራሱ መቼም ቢሆን ከፍተኛ ግምት አይሰጥም። እኔ ምን ሰራሁ? ይህ ሁላ ሙገሳ አይገባኝም የሚል ሰው ነው። የፔን አዋርድ ተሸላሚ የሆነ ጊዜ ከወዳጆቼ ጋር በመሆን «እንኳን ደስ አለህ» ለማለት ቃሊቲ በተገኘንበት ጊዜ እንኳን እንዲህ ማለቱን አስታውሳለሁ፤
‹‹እኔ ምን ሰራሁ? ይህ ሽልማት እኮ የእኔ አይደለም። በኢትዮጵያ ውስጥ ዴሞክራሲያዊ ስርአት እንዲሰፍን እየታገሉ የሚገኙት ውጤት ነው። እኔ ብቻዬን ምንም አላደረኩም። ስለዚህ እንደራሴ ሽልማት አድርጌ አልቆጥረውም።›› ይህን ሲለን እጅግ ተገረምኩ።

እሱ እየከፈለ የሚገኘውን ዋጋ እያየሁ እኔ ምን አደረኩ? ሲልም ተደመምኩ። ይህን ሲለን የታሰረ ሰው እንኳ አይመስልም። የመንፈስ ጥንካሬው አስገራሚ ነው። መንፈሱ ከቃሊቲ ውጪ እንደሚገኝ እስክንድርን ቃሊቲ ተገኝቶ የጠየቀው ሁሉ ይመሰክራል። ስጋውም ቢሆን አልተጎዳም። እስኬው ፤ ከጥሩ ተነጋሪነቱ ባሻገር ጥሩ አድማጭም ጭምር ነው። የሰውን ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትንም ያከብራል።
ትህትናው ደግሞ ልዩ ነው።

‹‹እስክንድር ማለት ቤተ-መጻሕፍት ነው።›› ስትል ባለቤቱ ሠርካለም ፋሲል የተናገረችው እውነት እንደሆነም መመስከር እችላለሁ። አዎ! እስክንድር ቤተ-መጻሕፍት ነው። ምን ያህል እውቀት እንዳለው ጠጋ ብላችሁ ስታናግሩት ታውቃላችሁ። እውቀቱን ለማካፈል ባለመሳሳቱ ደግሞ እውነተኛ ምሁር ብዬ እንድጠራው እገደዳለሁ። በአጭር ደቂቃዎች እንኳ ከእስክንድር አንደበት ብዙ ቁም ነገሮችን ቀስሞ መመለስ ይቻላል። ይህ ደግሞ የእስኬውን የእውቀት መጠን በሚገባ ያሳያል። እስኬው ቃሊቲ መሆኑ ክፉኛ ያበሳጫል። ከቃሊቲ ውጪ ቢሆን ኖሮ ብዙ ነገሮችን መስራት ይችላል። ገዢዎቻችንም ይህን ስለተረዱ ክስ መስርተውበት 18 አመት ፅኑ እስራት በይነውበታል። ይህን በሚመለከት ከአንድ ወዳጄ ጋር ስናወጋ ‹‹የእስክንድርን እስር የአንድ ግለሰብ እስር አድርጌ ለመቀበል ይከብደኛል። እስክንድር እኮ የኢትዮጲያ ሪሶርስ ነው። ኢትዮጲያ አንድ ትልቅ ሪሶርስ አታለች። ይህ ሪሶርስ ቃሊቲ መቀመጥ የለበትም። ከቃሊቲ መውጣት አለበት።›› ነበር ያለኝ፡፡ ስለ እስክንድር ይህን ሁላ ብዬ ስለ ጽናቱ ሳላነሳ ባልፍ የእስክንድርን ትልቁንና ዋናውን ጠንካራ ጎን መሳት ይሆናል። እስክንድር ጽናቱ እጅግ ያስደምማል። ጽናቱ የት ድረስ እንደሆነ የሚገልጹ አንድ ሁለት ነገሮችን ላንሳላችሁ።

እስክንድር ፣ ናፍቆት የሚባል ብቸኛ ልጅ አለው። ናፍቆት የተወለደው ምርጫ 97ትን ተከትሎ እሱና ባለቤቱ ለእስር በተዳረጉበት 1998 ዓ.ም ላይ ነው። የናፍቆት የትውልድ ቦታ ደግሞ ቃሊቲ እስር ቤት ነው። ባለቤቱ ሠርካለም ናፍቆትን የተገላገለችው በቃሊቲ እስር ቤት ውስጥ በሚገኝ ክሊኒክ ነው። እስክንድር ከእስር አስኪፈታ ማለትም እስከ 1999 ዓ.ም ድረስ ልጁን አላየውም። ከዚህ በመነሳትም ልጁን ናፍቆት ሲል ሰየመው። እስክንድር እንዲህ የሚወደውን ልጁን ለስምንተኛ ጊዜ ለእስር በበቃበት ማለትም በ መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ.ም ላይ በድጋሚ ተለየው። በወቅቱ ናፍቆትን ከትምህርት ቤት በማውጣት ላይ የነበረው እስክንድር ፣ በፖሊሶች ቁጥጥር ስር ሲውል ልጁ ናፍቆት አብሮት ነበረ። ፖሊሶቹ ናፍቆትን ከአባቱ በመለየት አባቱን ይዘውት ሄዱ። ይህን ሲያስተውል የነበረው ናፍቆት ክፉኛ ተረብሾ ነበር።

እስክንድር በእንዲህ መልኩ ከልጁ ከተነጠለ በኋላ ልጁን የሚያገኘው በቃሊቲ ወህኒ ቤት ውስጥ ነው። ናፍቆት ከጊዜ ወደ ጊዜ ስነልቦናው በጣም እየተጎዳ ሲመጣ እስክንድርና ባለቤቱ ሠርካለም በአንድ ነገር ላይ መከሩ። ይህም ልጃቸው አዲስ ከባቢ እንደሚያስፈልገው ነው። በዚህ መሠረትም ሠርካለምና ናፍቆት እስክንድርን በመሰናበት ወደ አሜሪካ አቀኑ። ይህ ውሳኔያቸው ምንኛ ከባድ እንደነበር ሠርካለም ለስደት በተዳረጉበት ጊዜ ፤ በአንድ መጽሄት ላይ እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ያለፈችባቸውን ውጣ ውረዶች ጽፋ ለንባብ ማብቃቷን አስታውሳለሁ። ይህን ጽሁፍ ካነበብኩ በኋላ ቃሊቲ በማምራት

እስክንድርን አገኘሁት። እሱና ሠርካለም ስላሳለፉት ውሳኔ ስጠይቀውም እንዲህ አለኝ፡-
‹‹ለናፍቆት በማሰብ ያደረግነው ነው። እዚህ ሲመጣ የመረበሽ ስሜት አስተውልበት ነበር። ከዛም በተጨማሪ በትምህርት ቤት ውስጥ ከሌሎች ልጆች የመነጠልና የብቸኝነት ስሜት ይታይበት ስለነበር ከባቢ መቀየር የተሻለ ሆኖ ስላገኘነው በጋራ መክረን የደረስንበት ውሳኔ ነው።››
‹‹ባለቤትህንና ልጅህን አንተ እዚህ ሆነህ በስደት መነጠቅህ አይከብድም ወይ?›› አልኩት

እሱም፡-‹‹ባለቤቴንና ልጆቼን በእጅጉ እናፍቃቸዋለሁ። ከእነሱ መነጠሌ ክፉኛ ጎድቶኛል። ግን ይህ መስዋትነት መከፈል ያለበት መስዋዕትነት ነው። እነ ናፍቆት ዴሞክራሲያዊ ስርአት በተገነባባት ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር አለባቸው። ለእዚህ ደግሞ መስዋትነቱን መክፈል ያለብኝ እኔ ነኝ።›› ሲል መለሰልኝ፡፡

የተናገረው ንግግሩ የእስክንድር ጽናት ምን ደረጃ እንደሆነ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። እንዲህ አይነቱ ጽናት ያላቸው ሰዎች ፣ እጅግ በጣም ጥቂቶች ናቸው። ከእነዛ ጥቂቶች መሀል ደግሞ አንዱ ታላቁ እስክንድር ነው።

የእስክንድርና ጽናት የሚያሳይ አንድ ሌላ ነገር ጨምሬ ጽሁፌን ልቋጭ። በአንድ ወቅት እስክንድርን እየፈራሁና እየተባሁ እንዲህ የሚል ጥያቄ አነሳሁለት። ‹‹እስክንድር ፣ይቅርታ ጠይቀህ የመውጣት ሀሳብ የለህም ወይ?›› (ይህን ጥያቄ ያነሳሁለት የእስክንድር ምላሽ ጠፍቶኝ ሳይሆን የእስክንድር እዛ መሆን ስለሚያበሳጨኝ ነው።)

እንዲህ በማለት ለጥያቄዬ ምላሹን አስከተለ፡- ‹‹የኢህአዴግን መንግስት አይደለም ይቅርታ ይቅርና አመክሮ አልጠይቀውም። 18 አመት አይደል የፈረደብኝ እሷኑ 18 አመት ጠጥቼያት እወጣለሁ እንጂ እንዲህ አይነት ነገርን በጭራሽ አላስብም።››

ይህ ምላሹ የእስክንድር የአእምሮ ጥንካሬና ጽናት ምን ድረስ እንደሆነ እንድገነዘብ አድርጎኛል። እንዲህ አይነት ጽናት ከየት እንደሚገኝ ግን አላውቅም። እንደ ታላቁ እስክንድር ለመሆን እንዲህ አይነት ጽናትና የአእምሮ ጥንካሬ ግድ ይላል። ኢትዮጵያ ብዙ ታላቁ እስክንድሮችን ትሻለች። እስከዛው ግን በአንዱና ቃሊቲ በሚገኘው ታላቁ እስክንድሯ አንገቷን አትደፋም!

40ኛው የህጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ እና “ልማታዊው ሲኖዶስ”

$
0
0

“የብጹዕ አቡነ ዜና ማርቆስ ቦታ አሁንም ክፍት ስለሆነ በቦታው ተጠባባቂ/ምክትል ፓትርያርክ ቢመረጥ መልካም ነው”

 

ታዬ ብርሀኑ

በስደት ላይ የሚገኘው ህጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ 40ኛውን መደበኛ ጉባኤ ከጥቅምት 26-28/2007 ዓ/ም በኮሎምበስ ኦሀዮ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል የተካሄደው ጉባኤ ስኬታማ ነበር። እንደዚህ ዓይነቱ የተሳካ ስብሰባ በኦሀዮ መደረጉ የራሱ የሆነ ታሪካዊ እሴት አለው። ይህም የቅዱስ ሲኖዶስ ድጋፍ ኮሚቴ ብለው የተሰባሰቡ ግለሰቦች በአባቶቻችን መሃል ከሶስት ዓመታት በፊት የጫሩት የመለያየት እሳት ግብዓተ መሬቱ እዛው ቦታ ላይ መፈጸሙ ነው። በእርግጥ አባቶች የነዚህን ስብስቦች አካሄድ ተረድተው ወደ አንድ ገጽ ከመጡ አንድ ዓመት አስቆጥረዋል ሆኖም ከማወጅ በፊት አንድነቱ ይርጋ በሚል ስንጠባበቅ ቆይተን 40ኛው የሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ያንጸባረቀውን መልካም ገጽታ እኛ ምኦመናንን ስላስደሰተ እግዚአብሄርን ለማክበርና ለማመሰገን እንዲሁም ደስታችንን እንገልጽ ዘንድ ለመጻፍ ወደድኩ።
holy sinod excile
የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በቅዱስ ፓትርያርኩ መልካም ፈቃድ በብጹእ አቡነ መልከጼዴቅ ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊነት ዘመናትን በተሻገረ በጠለቀና በበሳል የአመራር ችሎታ ስብሰባው ተመርቶ ወቅታዊና አበይት በሆኑ ርዕሶች ላይ ተነጋግሮ ጉባኤው በስኬት ተፈጽሟል። ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ስለ ህገ ቤተክርስቲያን መከበርና ሰለ ስብከተ ወንጌል መስፋፋት በስፋት የተነጋገረበት ሲሆን ይህን አሰመልክቶ ከተለያየ አቅጣጫ የቀረቡት አስተያየቶች በተገቢው መንገድ ሁሉም ተስተናግደው ወደ ውሳኔ ሃሳብ ተደርሷል። ቅዱስ ሲኖዶሱ ከተወያየበት ወቅታዊ ርዕሶች በደማቁ ሊሰመርበት የሚገባው ሀገራችንን ኢትዮጵያ ውስጥ በገዢው ፓርቲ እየተካሄደ ያለውን ከርዕስትና ከጉልት ማፈናቀል፣ የዘር ማጥፋትና ማጽዳት ወንጀል፤ የፍትህ እጦት፤ የሰብዓዊ መብት ጥሰት፤ በሃይማኖት ተቋም ውስጥ የሚያደርግውን ጣልቃ ገብነት አውግዞ በመጨረሻም ቅዱስ ሲኖዶስ ይህን የኢትዮጵያን ህዝብን ሰቆቃ የሚያስቆመው ከህዝብ ትግል ጋር እግዚአብሔር በመሆኑ በያዝነው ጾመ ነቢያት ወቅት መላው ኦርቶዶክሳውያን በአጥቢያው በሚገኘው አብያተ ክርስቲያን እየተገኘ የምህላ ጸሎት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርቧል። በመሆኑም ካለፈው እሁድ ጀምሮ በሕጋዊ ቅዱስ ጥላ ጥር በታቀፉ በመላው አለም በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ዓብያተ ክርስቲያናት ተጀምሯል።

ቅዱስ ሲኖዶስ «እኔስ የመረጥኩት ጾም ይህን አይደለምን የበደልን ሰንሰለት ትፈቱ ዘንድ የቀንበሩን ማነቆ ታላቅቁ ዘንድ የተጨቆኑትን ነጻ ታወጡ ዘንድ ቀንበሩን ሁሉ ትሰብሩ ዘንድ አይደለምን?» ኢሳ 58፥6 በሚለው አምላካዊ ቃል መሰረት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሰንሰለት ህዝቡ ይ,ፈታ ዘንድ፣የኢፍትሐዊነት ቀንበር በኢትዮጵያ ምድር እንዲሰበርና ዘረኝነት በኢትዮጵያ ምድር እንዲገደብና በጠቅላላው ኢትዮጵያውያን ከጭቆና ነጻ ይወጡ ዘንድ ጌታ የመረጠውን ጾም አውጇል። መንፈስ ቅዱስ የሚመራው ሲኖዶስ ፣ በሐዋርያት ወንበር ላይ የተቀመጡ እውነተኛ አባቶች ስለ ምእመናን ሕይወት ግድ ይላቸዋል በክርስቶስ ደም ዋጋ ተክፍሎባቸዋልና። በስደት ያሉት ብጹዓን አባቶችና ካሕናት ሊቀ ካህናቸው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚከተለው ያስተማራቸውን በቅጡ አስተውለው የጌታ አመትን እየሰበኩ እየገኛሉ። “የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና፤ ለታሰሩትም መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ፥ የተጠቁትንም ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ ዘንድ ልኮኛል” ሉቃስ 4፥18
Holy sinod addis ababa
በአንፃሩ ሀገር ቤት የሚገኙው ህገወጡ ሲኖዶስ ስብሰባቸው ጨርሰው ያወጡትን መገለጫ በዘሀበሻ ድረ ገጽና በሐራ ተዋህዶ ላይ ተለጥፎ እንዳየሁት የመጀመሪያ ጥሪ ለሕብረተሰቡ የቀረበው ልማታዊ ጥሪ ነው በተለይም የአባይን ግድብ አሰመልክቶ። የአባይ ግድብ ጉዳይ መንፈሳዊ አባቶችን ጨምሮ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ቢሆንም መንፈሳዊ አባቶች ማስቀደም ያለባችው የተጠሩበት ሰማያዊ ጉዳይ ነው። አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአገልግሎት የጠራችው የሰው ሕይወት እንዲያድኑ እንጁ ለሕንፃ ልማት አይደለም። ለነገሩ መንበሩን የተቆጣጠሩት በጦር መሳሪያ ሃይል እንጂ በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ስላልሆነ ሲጀመርም ቅድስና የሌለው ሲኖዶስ ነው። በመሆኑም ቅዱስ ሲኖዶስ የሚለው ስያሜ አይገባውም ይልቁንም “ልማታዊ” ሲኖዶስ የሚለውን ስያሜ ይገባችዋል። በጣም የሚያሳዝነው ጉዳይ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረው ወገናቸውን መረገጥ በዓይናችው እያዩ የስላሲዎች ህንጻ የሆነው ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን ኢ-ፍትሐዊነት ዓይናቸውን ጨፍነው እያለፉ ክርስቶስ በደሙ የዋጃቸውን የአማራውና አኝዋኩ ሕዝብ ላይ የተፈጸመውን የዘር ማጽዳት ዘመቻ እየሰሙ እንዳልሰሙ አልፈው ያልተጠሩበትን ስለ ግዑዙ አባይ መገደብ ያወጡት መገለጫ ምንም መንፈሳዊ መዓዛ የሌለውና በሞራላዊ መስፈርት ሲመዘን እጅግ የወረደ መግለጫ ነው።

ተመዝንክ ግን ቀለህ ተገኘህ የሚለው የመጽሃፍ ቅዱስ ቃል ለነዚህ የአባቶች ስብስብ ተገቢ ቃል ነው (ዳንኤል 5፡26) ። ፍትህ እንደዚሁም ሰብዓዊ መብት እኮ በእግዚአብሔር አምሳል ለተፈጠረ ሰው ስማያዊ ስጦታ ነው። ሰለሆነም የዜጎች ሰብዓዊ መብት ሲጣስ እንዲከበር መጮህ፣ ጸልዩ ብላ ማዘዝ እንዲሁም ጸሎት ብቻ ማዘዝ ሳይሆን መብቱንና ነጻነቱን ለማስከበር የበኩሉን እንዲያረግ ማዘዝ የቤተክርስቲያን ተልዕኮ ነው። ሩቅ ሳንሄድ ኢትዮጲያዊውያኑ ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስና አቡነ ሚካኤል ለዚህ ምግባር ዓይነተኛ ምሳሌዎች ናቸው። ሀገር እየደማ፣ ሀገር እየቆሰለ ህዝቡ ርስቱን እየቀማ በሀገሩ እየተሰደደ፣ በሀስት ክስ እያታሰረና እየሞተ ልክ በኢያሪኮ በወንጀለኞች ተደብድቦ ወድቆ በሕይወትና በሞት መካከል የነበረውን ሰው የአይሁድ ካህናት (ፈሪሳውያን) እንዳላዩ ገለል ብለው እንዳለፉት (ሉቃ 10፥30-35) እንደዚሁ የሀገር ቤቶች አባቶችም የሕዝቡን ሕማማትና ሞት ችላ ብለው አልፈው አባይ ይገደብ ይሉናል ምናለ በነካ አፋችው የሰብዓዊ መብትም ጥሰት ይገደብ፣ ዘረኝነትና ስደት ይገደብ ቢሉ። የሚገርመው ሉቃ 10፥30-35 እንደሚነገረን ካህን ያልሆነው ሳምራዊው ግለሰብ በነገድ ከማይገናኘው ለወደቀው ሰው አዝኖ መደረግ ያለበት እርዳታ ሁሉ አደረገለት። በዘርና በነገድ ከኛ ምንም ግንኙነት ሳይኖራችው ግን ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚደረገው የሰብዓዊ መብት ጥሰት “Amnesty International” ፣ “Human Rights Watch” እና የዓለም ዓቀፉ የጋዜጠኞች ማህበር የሚጮሁት የሳምራዊውን በጎ ምግባር ሲወጡ የአዲስ አበባው ልማታዊ ሲኖዶስ ደግሞ የፈሪሳውያኑን ስራ አንጸባርቀዋል። የአዲስ አባባው ሲኖዶስ የሃይማኖትን ስም ተላብሶ በምግባር ግን በአቶ (ምዕመን) ደረጃ ካሉት ከአርቲስት ታማኝ ና ከአቶ ኦባንግ ያነሰ የሞራል ስብዕና እያሳዩ ናቸው። ዲ/ን ዳንኤል “የማያለቅስ ልጅ” በሚለው ጽሁፉ ይህንን የአዲስ አበባውን ሲኖዶስ ስብሰባ አሰረ ሐዋርያትን (የሐዋርያት ፈለግ) የተከተለ ብሎ አድንቆታል ለማንኛውም የአንባቢ ህሊና የሐዋርያትን ፈለግ የተከተለው የትኛው ጉባኤ እንደሆነ ይፍረድ።

ጭራሽ የአዲስ አበባው ሲኖዶስን ጨምሮ ሌሎችም የሃይማኖት ተቋሟት በትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት የሰለላ ድርጅት እዝ ስር ተዋቅረው መንጋውን የሚሰልሉና የሚያስጨንቁ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኝና ምንደኛ እረኞች እንደሆኑ ለኢሳት የደረሰውን የገዢው ፓርቲ የስለላው ድርጅትን ሪፖርት የድምጽ መረጃ የሰማ ይገነዘባል። የእግዜሃብሔር ቃል ለእነዚህ የሃይማኖት አባቶች እንዲህ ይላል፥

“እግዚአብሔር ከሕዝቡ ሽማግሌዎችና ከአለቆቻቸው ጋር ይፋረዳል፤የወይኑን ቦታ የጨረሳችሁ እናንተ ናችሁ፤ ከድሆች የበዘበዛችሁት በቤታችሁ አለ፤ሕዝቤንም ለምን ታደቅቁአቸዋላችሁ? የድሆችንስ ፊት ለምን ትፈጫላችሁ? ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። ኢሳ3፥13

“ስለዚህ፥ እረኞች ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። እነሆ፥ በእረኞች ላይ ነኝ፥ በጎቼንም ከእጃቸው እፈልጋለሁ፥ በጎቼንም ከማሰማራት አስተዋቸዋለሁ። ከዚያም ወዲያ እረኞች ራሳቸውን አያሰማሩም፤ በጎቼንም ከአፋቸው አድናለሁ፥ መብልም አይሆኑላቸውም። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና። እነሆ፥ እኔ ራሴ በጎቼን እሻለሁ እፈልግማለሁ።እረኛ በተበተኑት በጎች መካከል ባለ ጊዜ መንጋውን እንደሚፈልግ፥ እንዲሁ በጎቼን እፈልጋለሁ፤ በደመናና በጨለማ ቀን ከተበተኑት ስፍራ ሁሉ አድናቸዋለሁ።” ሕዝቅኤል 34፦9-12

በመጨረሻም ህጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ የሚገኝበት ሁኔታ ደስ የሚያሰኝ ነው። በስደት ከሚገኙት የመምህራንና የጋዜጠኞች ማህበር እንደዚሁም ከተለያዩ በስደት ከሚገኙ የኢትዮጲያውያን ተቋሟት የግንኙነት መሰመር ፈጥረው የህዝባችንን ሰቆቃ የሚያጥርበት ጊዜ አብረው ቢመከሩ መልካም ይመስለኛል። የጠቅላይ ቤተክህነቱ አስተዳደሪ ከሰዎች ጋር በበለጠ እየተግባባ እንዲሰሩ ቢመከሩ እንደዚሁም የህዝብ ግንኙነት ክፍል አንደበተ ርቱዕና ነቃ ያሉ አባቶች ቢካተቱበትና የብጹዕ አቡነ ዜና ማርቆስ ቦታ አሁንም ክፍት ስለሆነ በቦታው ተጠባባቂ/ምክትል ፓትርያርክ ቢመረጥ መልካም ነው።

የአባቶቻችን አምላክ የተመሰገነ ይሁን!
Taye_berhanu@ymail.com

ዋለልኝ መኮንን-አፈና ያልገታው የአመጽ ድምጽ

$
0
0

ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
ተነገወዲያ ህዳር ህዳር 29/2007 ዘጠነኛው የብሄርና ብሄረሰቦች ቀን ሊከበር ነው፡፡ ይህ ቀን ለበዓሉ አከባበር የተመረጠው የኢፌዴሪ ህገ-መንግሥት የጸደቀበት ቀን ስለሆነ ነው ተብሏል፡፡ ታዲያ በዚሁ ቀን አንድ ታላቅ አብዮታዊ ተገድሎ ነበር፡፡ የሚገርመው ደግሞ በዚያች ቀን የሞተው ሰውዬ በኢትዮጵያ ውስጥ የብሄርና ብሄረሰቦች መብት መከበር አለበት በማለት ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ የጻፈ ሰው መሆኑ ነው፡፡
*****
walelignህዳር 29/1964፡፡ ረፋዱ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ 708 ጄት አውሮፕላን ከአዲስ አበባ በአስመራ በኩል ወደ አቴንስ ሊበር ነው፡፡ በአውሮፕላኑ የሚጓዙ መንገደኞች ቦታ ቦታቸውን ይዘዋል፡፡ ሰባት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ከአውሮፕላኑ ውስጥ ተሳፍረዋል፡፡ የበረራው ሰዓት ሲደርስ አውሮፕላኑ ከመሬት ተነሳ፡፡ ከሰማዩ ገብቶ መብረር ሲጀምር ግን ያልታሰበ ሁኔታ ተከሰተ፡፡ እነዚያ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አውሮፕላኑን በቁጥጥራቸው ስር ማዋላቸውን አስታወቁ፡፡ እነርሱ ወደሚፈልጉት ሀገር እንዲበሩም አብራሪዎቹን አዘዟቸው፡፡ ተማሪዎቹ የጠለፋ እወጃውን ካሰሙ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ ሌላ ያልታሰበ ነገር ተከሰተ፡፡ አውሮፕላኑን ከጠለፋ እንዲታደጉ የታዘዙ ኮማንዶዎች በቀጥታ በጠላፊዎቹ ላይ በማነጣጠር ተኮሱባቸው፡፡ ስድስት ጠላፊዎች ተገደሉ፡፡ አንዲት ጓደኛቸው ደግሞ በከባድ ሁኔታ ቆሰለች፡፡ የአውሮፕላኑ ወለል በሙታኑ ደም ታጠበ፡፡
*****
በዚያች ዕለት የሞተው ታዋቂው የተማሪዎች ንቅናቄ መሪ ዋለልኝ መኮንን ነበር፡፡ ከርሱ ጋር የተገደሉትም ማርታ መብራህቱ፣ ጌታቸው ሀብቴ፣ ተስፋዬ ቢረጋ፣ ዮሐንስ በፈቃዱ እና አማኑኤል ዮሐንስ ናቸው፡፡ እነዚያ ወጣቶች አውሮፕላኑን ለመጥለፍ የሞከሩት የስርዓቱ ክትትል መፈናፈኛ ስላሳጣቸው ነው፡፡ ዓላማቸው ወደ ውጪ ከኮበለሉት ጓደኞቻቸው ጋር በመቀላቀል ለስር-ነቀል ለውጥ የሚታገል ድርጅት መመስረት ነበር፡፡ ከድርጅቱ ምስረታ በኋላም ወደ ሀገር ቤት ተመልሰው ትግሉን በየአቅጣጫው ለማፋፋም አስበዋል፡፡ ሆኖም እንደተመኙት አልሆነላቸውም፡፡ አውሮፕላን ለመጥለፍ ማቀዳቸው ቀደም ብሎ ተጠቁሞ ስለነበር የጸጥታው ክፍል በአየር ላይ አፍኖ አስቀራቸው፡፡
*****
ከላይ በተገለጸው አሳዛኝ ገቢር (ትራጄዲ) ህይወቱ የተቋጨው ዋለልኝ መኮንን በወሎ ክፍለ ሀገር የሳይንት (ቦረና) አውራጃ ተወላጅ ነው፡፡ የአንደኛና ደረጃ ትምህርቱን በደሴው ንጉሥ ሚካኤል ትምህርት ቤት አጠናቀቀ፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱንም እስከ አስረኛ ክፍል ድረስ ደሴ ከተማ በሚገኘው ታሪካዊው ወይዘሮ ስሒን ት/ቤት ተከታለለ፡፡ አስራ አንደኛና አስራ ሁለተኛ ክፍልን ደግሞ የዘመኑ ምርጥ ተማሪዎች መማሪያ በነበረው በአዲስ አበባው በዕደማሪያም ትምህርት ቤት አገባደደ፡፡ በ1958 ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከገባ በኋላም እጅግ የተለየ አብዮታዊ ሆነ፡፡

ዋለልኝ በ1959 በዩኒቨርሲቲው በተደረገው የግጥም ውድድር “ሙት ወቃሽህ መጣው” በሚለው ግጥም አንደኛ ወጥቷል፡፡ በዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ህብረት ይዘጋጅ በነበረው የታገል መጽሔት ከማንም በላይ የነቃ ተሳትፎ ያደርግ ነበር፡፡ በህቡዕ የሚዘጋጁ ጽሑፎችንም እያዘጋጀ ያሰራጭም ነበር፡፡ በተለይ “አዞዎቹ” የሚባለው የስር-ነቀል ለውጥ ደጋፊ የተማሪዎች ስብስብ በአቋም ደረጃ የተስማማባቸውን ሀሳቦች በጽሑፍ እያቀናበረ የሚያዘጋጀው እርሱ እንደነበር በያኔው እንቅስቃሴ የተሳተፉትም ሆነ የዘመኑን ታሪክ ያጠኑ ምሁራን ይመሰክራሉ፡፡

ከዋለልኝ ጽሑፎች መካከል ዝነኛ የሆኑት ሁለት ናቸው፡፡ አንደኛው ከላይ የጠቀስኩትና ህዳር 10/1961 በታተመው “ታገል መጽሔት” ላይ የወጣው “የብሄረሰቦች ጥያቄ በኢትዮጵያ” የሚል ርዕስ ያለው ጽሑፍ ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ በ1962 የተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት የነበረው ጥላሁን ግዛው ሲገደል የአጼው ስርዓት በተማሪዎቹ ላይ ያደረገውን ዛቻ በመቃወም “ለአዋጁ አዋጅ” በሚል ርዕስ በህቡዕ ጽፎ የበተነው ጽሑፍ ነው፡፡ ዋለልኝ በጽሑፎቹ ሳቢያ በተደጋጋሚ ጊዜያት ታስሯል፡፡ በተለይ “ለአዋጁ አዋጅ”ን የጻፈው እርሱ መሆኑ ሲታወቅ በችሎት ፊት ቀርቦ አምስት ዓመት እስራት ተፈርዶበታል (ሆኖም ተማሪዎች ባደረጉት ከፍተኛ የተቃውሞ ጫና ከዓመት በኋላ ተፈትቷል)፡፡

ከ1962 በኋላ ሁለት ክስተቶች የተማሪውን ንቅናቄ አቅጣጫ ቀይረውታል፡፡ እነዚህም በስርዓቱ የሚደረገው አፈና መጠናከር እና የድርጅት ምስረታ ጥያቄ መቀስቀስ ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንደ ቀድሞው ጊዜ የተቃውሞ ሰልፍ ከማድረግ ይልቅ የጥናት ክበቦችን እየመሰረቱ መወያየቱን መረጡ (የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በተቃውሞ ቀጠሉ)፡፡ ዋለልኝም በውይይት ክበቡ በሚያደርገው ጥናት ላይ አተኮረ፡፡ ከሀገር ተሰደው በአልጄሪያ ከሚገኙት እነ ብርሀነ መስቀል ረዳ ጋር በሚያደርገው የደብዳቤ ልውውጥ አማካኝነትም ሰፊ መሰረት ያለው ድርጅት ለመመስረት በሚደረገው ውይይትም ውስጥ ይሳተፍ ነበር፡፡ ህዳር 29/1964 በውጪ ካሉት ጓደኞቹ ጋር ለመቀላቀል ሲል አውሮፕላን ጠለፈ፡፡ ሆኖም ካሰበው ስፍራ ሳይደርስ በአውሮፕላኑ ውስጥ ተገደለ፡፡
*****
ከያኔው የተማሪዎች ንቅናቄ መሪዎች መካከል ዋለልኝ መኮንን ልዩ የሚያደርገው አንድ ነገር አለ፡፡ ይኸውም የተለያየ አመለካከት ባላቸው የፖለቲካ ድርጅቶች እንደ ታላቅ ሰማዕት የሚታይ መሆኑ ነው፡፡ ደርግ፣ ኢህአፓ፣ ህወሐት፣ ኦነግ፣ ሻዕቢያ፣ መኢሶን፣ ወዘተ… ሁሉም ለርሱ በጎ አመለካከት ነው ያላቸው፡፡ ታዲያ በዋለልኝ ታሪክ ላይ የሚደረገው ሽሚያም በጣም የጠነከረ ነው፡፡ አንዳንዶቹ ታሪኩን ከራሳቸው ድርጅት ጋር ለማቆራኘት ይሞክራሉ፡፡ በወቅቱ የነበረው የርሱና የጓደኞቹ አሰላለፍ ሲገመገም ግን ዋለልኝ ኢህአፓን ከመሰረቱ ወጣቶች ጋር ተመሳሳይ የፖለቲካ መስመር የነበረው ሆኖ ነው የሚታየው፡፡ ኢህአፓን የመሰረቱትም የርሱ የቅርብ ጓደኞች ናቸው፡፡ በመሆኑም ዋለልኝ በህይወት ቢሰነብት ኖሮ የዚሁ ድርጅት አባል ይሆን ነበር ተብሎ ነው የሚገመተው፡፡
*****
ዋለልኝ መኮንን ከብዙ በጥቂቱ ይህ ነበር፡፡ ወደፊት ሰፋ ባለ ሁኔታ ስለርሱ እጽፋለሁ ብዬ አስባለሁ፡፡ እናንተም በበኩላችሁ የምታውቁትን እንድታጋሩን በአክብሮት እንጠይቃችኋለን፡፡
——
ሰላም
አፈንዲ ሙተቂ
ህዳር 29/2006

ዜሮን በሞራ፤ በሁሉም የወደቀ ዱለኛ። (ሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 10.12.2014 /ሲወዘርላንድ – ዙሪክ/

ዛሬ እንደ አውሮፓውያኑ አቋጣጠር ታህሳስ 10 ቀን 2014 ነው። ይህ ቀን በዓለምአቀፍ ደረጃ በአንባገነኖች ጫና ሥር የተሰዉ ሰምዕት በጸሎት የሚታሰቡበት፤ በህይወት እያሉ ሰብዕናቸው ለሚጠቀጠቅ ምልዕት አትኩሮት በአፅህኖት የሚሰጥበት ብሩክ ቀን ነው። እንዲሁም ዓመታዊ ክንውኖችና ምላሻቸው በተደሞ የሚቃኝበት – የ1948 ቅዱስ መንፈስን የተካኑ 30 ሁለንትናዊ የኑሮ ቃለ ወንጌላት የተወለዱበት ማዕልት።

Yenese Gebreእኛም ኢትዮጵውያን በሰብዕዊ መብት ጭፍለቃ የሚታወቀው አንባገነኑ የወያኔ ማንፌስቶና ማስፈጸሚያ መሳሪያዎቹ ሁሉ በወገን፣ በሀገር፣ በዳር ደንበር፣ በሰንደቅ፣ በታሪክ፣ በዕምነት፣ በባህል፣ በፍቅር፣ በአብሮነት፣ በማንነት፣ በዜግነት፣ ዙሪያ ያደረሰውን፤ በማድረስ ላይ ያለውን ጭቆና ለማስወገድ ለትጋት እራሳችን የምናሰናዳበት ልዩ ቀን ነው። ገና በዋዜማው የታዳጊ ሃና ዘግናኝ ግፍና በደል፤ የሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ በወያኔ ሠራዊት መወረር፤ የዘጠኙ ፓርቲ የትብብር መርሃ ግብር ግብር ሁሉም በዱላና እስር የገጣማቸው ግፍ በአርምሞ ይታሰባሉ። ስለዚህ ይህን ቀን እኛ የምናስታውሰው ቀደምት ሰማዕቶቻችን የእነአሰፋ ማሩ፤ ሺብሬ ደሳለኝ፤ ዶር. እምሩ ሥዩም፤  ዬእኔ ሰው ገብሬ፣ የህጻን ነብዩ፤ ከዚህ ባለፈ በዬስደት ሀገሩ ክልትምትም ሲሉ ላለፉ፤ እኛ ሳናወቃቸው በመርዝ ለተጨረሱት፤ እስር ቤት በድርብ በቀል መዶሻ ለሚቀጠቀጡት ወገኖቻችን ሁሉ ልባችነን ክፍት አድርገን የመንፈሳችነን ዓይን አብርተን ጥላቻን – ጥላቻ እንዳይወልደው፤ በቀል – በቀልን እንዳይወልደው እራሳችነን አን በንፁህ ልቦና እና መንፈስ ወደ አምላካችን ዕንባችን በመላክ ይሆናል – በቃችሁ እንዲለን። ድጋሚ ስደት፣ ድጋሚ መከራ፣ ድጋሚ ሰቀቀን፣ ድጋሚ ሰጋትና መጠቃቃት ከምንጩ የሚደርቅበትን አዲስ ንጹህ መንፈስ በመውለድ፤ ሰብዕዊ ህግትን በሥራ ለመተርጎም ህሊናችን ስንዱ በማደረግ ሊሆንም ይገባል – የመስዋዕት ሰማዕታት ውለታ።

የወመኔው ወያኔ ህግጋት እናት ህጉ፤ ህገ መንግሥቱ በሞራ የተጠቀለለ ዜሮ ነው። ለአፈጻጸም የሚያሰናዳቸው መመሪያዎች ቢሆኑ በሞራ የተጠቀለሉ ዜሮዎች በመሆናቸው ሰብዕዊ ህጋዊ መብቶችን ገዳይ ናቸው። በእናት ሀገር ኢትዮጵያ ዓለም ዓቀፉ ህግ የተባባሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሀገሮች እንዲፈጽሙት የደነገጉት ድንጋጌዎች ቢሆን ሥራ ላይ ሊውሉ የማይችሉ በሞራ የተሸፈኑ የዜሮ ድምሮች ናቸው። ክብሪት ብቻውን ብርሃንን፤ ሻማ ብቻውን ብርሃን አይሰጡም። ስለሆነም ሁለንትናዊው ዓለም ዐቀፍ የህግ አንቀፃትና ወያኔ ፈተና ውስጥ ናቸው። ወያኔ ፈተናውን የማለፍ አቅም የለውም። ስለዚህ ውጤቱም ዜሮ ነው።

ፈተናውና ውጤቱ በጥቂቱ።

„አንቀጽ 1የሰው ልጅ ሁሉ ሲወለድ ነጻና በክብርና በመብትም እኩልነት ያለው ነው። የተፈጥሮ ማስተዋልና ሕሊና ስላለው አንዱ ሌላውን በወንድማማችነት መንፈስ መመልከት ይገባዋል።“ የወያኔ ማንፌስቶ ህሊና ካለው አልተወለደም። አስተዳደሩም እንዲሁ። ወንድማማችነትን ፍቆ ጠብን፣ ጥላቻን የዘራና ያዘመረ፤ በቤተሰብ የቆዩ ትውፊቶች ሁሉ ቀራኒዎ ያወጀ ስለሆነ ኢትዮጵያ ላይ ውጤቱ —- ዜሮ ነው።

„አንቀጽ 2፤ እያንዳንዱ ሰው የዘር የቀለም የጾታ የቋንቋ የሃይማኖት የፖለቲካ ወይም የሌላ ዓይነት አስተሳሰብ የብሔራዊ ወይም የኀብረተሰብ ታሪክ የሀብት የትውልድ ወይም የሌላ ደረጃ ልዩነት ሳይኖሩ በዚሁ ውሳኔ የተዘረዘሩት መብቶችንና ነጻነቶች ሁሉ እንዲከበሩለት ይገባል። ከዚህም በተቀረ አንድ ሰው ከሚኖርበት አገር ወይም ግዛት የፖለቲካ የአገዛዝ ወይም የኢንተርናሽናል አቋም የተነሳ አገሩ ነጻም ሆነ በሞግዚትነት አስተዳደር ወይም እራሱን ችሎ የማይተዳደር አገር ተወላጅ ቢሆንም በማንኛውም ዓይነት ገደብ ያለው አገዛዝ ሥር ቢሆንም ልዩነት አይፈጸምበትም።“ ይህ ደግ ድንጋጌ በጎሳ ምጥ ውስጥ ባለች ሀገር የማይታሰብ ነው፤ ብሄራዊነት ህም! ውጤቱ –  ዜሮ ነው።

„አንቀጽ 3፤ „እያንዳንዱ ሰው የመኖር፣ በነጻነትና በሰላም የመኖሩ መጠበቅ መብት አለው።“ መላ አካላቷ በጠበንጃ በታገተ ሀገር የሚኖሩ ህዝቦች ሰላምና ነፃነት አልባ ናቸው። እንዲያውም ፈጣሪ አምላክ ትቶልን የሄደው የውስጡን ሰላም ሆኖ ሳለ፤ በወያኔ ግን ስቅላት የተበዬነበት የፈጣሪ ሥጦታም ጭምር ነው። ስለሆነም …. ውጤቱ —- ዜሮ

„አንቀጽ 4፤ „ማንም ሰው ቢሆን በባርነት አይገዛም። ባርነትና የባሪያ ንግድም በማንኛውም ዓይነት ክልክል ነው።“ የወያኔ ማንፌስቶ ያቀፈው ምርጥ ዘር ገዢ ሌላው ደግሞ ተገዢ ባሪያ ነው። ከዚህ በተጨማሪ  ሰሞኑን እንደ ጀርመኑ ዬZDF ቴሌቪዢን ዶክመንተሪ ዘገባ  የዘመናዊ የሠራተኛ ባርነት በሲዊዲኑ አሰሪ ካንፓኒ H&M ኢትዮጵውያን የመጨረሻ ክፍያ የሚያገኙና ለዘመናዊ ባርነት የተጋለጡ ስለመሆናቸው ምስክርነቱን ሰጥቷል። እንዲያውም ለባርነት የተዳረጉት ዬንፁህን የጉልበት ብዝበዛ ወሸኔና ማለፊያ ብሎ ወያኔ የሸለማቸውን ሺክ አላሙዲን ጨምሮ  እስኪበቃው ድረስ ዘገበው ወርፏቸዋል። ሀገረ ሲዊድን የባሪያ ጭቆናን በአዋጅ ካስረች በኋላ በእስያና በአፍሪካ የምታደርገው የእጅ አዙር ዬባርነት አገዛዝንም ዘገባው እስኪበቃው ነበር የከተከተው። ድርብርብ ባርነት በዘረኝነት ፖሊሲ ኢትዮጵያ ላይ ዘውድ ጭኗልና። ስለዚህ ውጤቱ …. ዜሮ ነው

„አንቀጽ 5፤ ማንም ሰው ቢሆን የጭካኔ ስቃይ እንዳይደርስበት ወይም ከሰብዓዊ አፈጻጸም ውጭ የሆነ የተዋረድ ተግባር ወይም ቅጣት አይፈጸምበትም።“ ሩቅ ሳይኬድ በተከበሩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የተፈጸመው ኢ – ሰባዕዊ ድርጊት በስተጀርባው ካለው የጣር ድምጽ፤ የወንድማችን ዬአቡበከር የእግር ብረት ቃለ ምልልስ ከበቂ በላይ ነው … ስለሆነም የዚህ ድንጋጌ ተፈፃሚነት – ዜሮ ነው ኢትዮጵያ ላይ።

„አንቀጽ 6፤ እያንዳንዱ ሰው በሕግ ፊት በሰው ዘርነቱ የመታወቅ መብት አለው።“ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ሰው ለመታዬት ለጎሳ ማደግደግ ያስፈልጋል። ይለፍ ያለው ጎጥ፤ ስለዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ የሰው ሰውነቱ የሚለካው በጎጡ ነው። ስለዚህ – ዜሮ ይሆናል ውጤቱ።

„አንቀጽ 7፤ ሰው ሁሉ በሕግ ፊት እኩል ነው። ያለአንዳች ልዩነትም ሕጉ ደህንነቱን እንዲጠበቅለት እኩል የሆነ መብት አለው። ይህንን ውሳኔ በመጣስ ከሚደረግ ልዩነት ለማድረግ ከሚነሳሳ እንዲጠበቅ ሁሉም የእኩል መብት አለው።“ ይህ አንቀፅ በአራዊት ጫካዊ ተመክሮ ፈጽሞ ሊታሰብ የማይችል፤ በክትና በዘወትር ዜግነት አሳሩን የሚያይ ድንጋጌ ነው። ስለሆነ – ዜሮ ነው።

„አንቀጽ 8፤ እያንዳንዱ ሰው በሕገ መንግስቱ ወይም በሕግ የተሰጡትን መሠረታዊ መብቶች ከሚጥሱ ድርጊቶች ከፍተኛ በሆኑ ብሔራዊ የፍርድ ባለስልጣኖች ፍጹም በሆነ መንገድ እንዲወገድለት መብት አለው።“ የትኛው ህገ መንግሥት? ያ ማባጨዬዋው። ህም። እያንዳንዱ የወያኔ ጀሌ ንጉሥ ነው። እሱ ያሰረውን ቢቀዬር – ቢሞት ሌላው አይፈታውም እንኳንስ ያደገውን አንቀጽ ተግባር ላይ ለመዋል ስለዚህ ያው – ዜሮ።

„አንቀጽ 9፤ ማንም ሰው ያለፍርድ ተይዞ እንዲታሰር ወይም በግዛት እንዲኖር አይደረግም።“ ይህ ዕለታዊ የኢትዮጵያ ህዝብ የፍዳ ክምር ምን ሆነና? – በውንብድና ሀገር እያስተዳደር ባለው በጭፍኑ ወያኔ እርግጫ የተደረመሰ አንቀፅ ነው ስለዚህ ውጤቱ  –  ዜሮ

„አንቀጽ 10፤ እያንዳንዱ ሰው በመብቶቹና በግዴታዎቹ አፈጻጸም እንዲሁም በሚከሰስበት ማንኛውም ዓይነት የወንጀል ክስ ነጻ በሆነና በማያዳላ የፍርድ ሸንጎ በትክክለኛና በይፋ ጉዳዩ እንዲሰማለት የሙሉ እኩልነት መብት አለው።“ ይህ ድንጋጌ ህግና መንግሥት ፍርድ ቤትና ዳኛ ላላቸው ሀገሮች እንጂ እንደ እኛ እረኛ አልባ፤ ባለቤት አልባ፤ ለሆነ ስላልሆነ … በህጉ ውስጥ መኖር አይደለም በአጠገቡም የወያኔ መንፈስ የለም ስለዚህ ያው —- ዜሮ።

„አንቀጽ 11፤  „1/፡ በወንጀል ክስ የተከሰሰ ማንኛውም ሰው ለመከላከያው አስፈላጊዎች የሆኑትን ሁሉ አቅርቦ በሚከራከርበት የይፋ ፍርድ ቤት በሕግ መሠረት ወንጀለኛ መሆኑ እስቲረጋገጥበት ድረስ ከወንጀል ነጻ እንደሆነ የመቆጠር መብት አለው።“ ይህ ሊሆን ይችላልን? እእ –  ኢትዮጵያ ላይ የህልም ሠርግ ነው ስለዚህ ውጤቱ — ዜሮ

„2/፡ ማንም ሰው በብሔራዊ ወይም በኢንተርናሽናል ሕግ አንድ ነገር ወንጀል ሆኖ ባልተደነገገበት ጊዜ በፈጸመው ወይም ባልፈጸመው ማንኛውም ሥራ ወንጀለኛ ሆኖ አይከሰስም። ወይም ወንጀሉ በተፈጸመበት ጊዜ ከተደነገገው ቅጣት ይበልጥ አይፈረድበትም።“ ወያኔ እኮ ወንጀል ነው የሚለውን ፈብርኮ እራሱ ቀርፆ፤ አስገድዶ አስፈርሞ እኮ ነው የነፃነት አርበኞቻችን ግዞት ውስጥ መንፈሳቸውን እያነደደ የሚገኘው — አፈጻጸሙ እራሱ ሰቅጣጭ፤ መቀጣጫ የሚያደርግ፤ ሰው መሆንን የሚፈትን ስለሆነ – ውጤቱ – ዜሮ

„አንቀጽ 12፤ ማንም ሰው በግል ኑሮው በቤተሰቡ ውስጥ በቤቱ ወይም በሚጻጻፈው ደብዳቤ በፍርድ ያልተለየ ጣልቃ ገብነት ወይም ክብሩን የሚነካና ስሙን የሚያጎድፍ ተቃውሞ አይፈጸምበትም። እያንዳንዱ ሰው ከእንደዚህ ያለ ጣልቃ ገብነት ወይም የሚጎዳ ተግባር ሕግ እንዲከላከልለት መብት አለው።“ በዜጎች ታሪክ ላይ ስንት ድርድር ተውኔት ነው ወያኔ የሚሠራው? … ክብርን እንዴት ነው የሚጥሰው? አይደለም ዜጋን ሀገርን እንደ ሀገር ማዬት የማይችል፤ በክብሯና በማንነቷ፤ በታሪኳና በሉዕላዊቷ ላይ በሚያላግጥ ብህዝቦቿ ሞራል ላይ ሞት የፈረደ ስለሆነ ከዚህ ድንጋጌ ጋር እንዴት ብሎ ወያኔ ሊወዳጅ ይችላል?! ስለሆነም – ዜሮ

„አንቀጽ 13፤  1/፡ እያንዳንዱ ሰው በየብሔራዊ ወሰን ክልሉ የመዘዋወርና የመኖር ነጻነት መብት አለው።“ ይቻላልን? አይቻልም። እንኳንስ ይሄ ከባዕቱ እትብቱ ከተቀበረበት እንኳን መቀመጥ አይፈቀድለትም። ስንቱ ነው መንፈሱ በጭቃኔ የታረሰው – በደሉ ረመጥ ነው። ግፉ ቋያ ነው። ስለዚህ የድንጋጌው ውጤት – ዜሮ

„2/፡ እያንዳንዱ ሰው ከማንኛውም አገር ሆነ ከራሱ አገር ወጥቶ እንደገና ወደ አገሩ የመመለስ መብት አለው።“ በ24 ሰ ዓት ዜጎች ሀገራቸውን ለቀው እንዲወጣ የሚያደርግ ግዑዝ ይቻላልን? ይሆናልን? ደንበር እዬዘለለ፤ ደንበር እዬጠሳ ስንት ወገኖቻችን ነው ወያኔ የበላው? በተሰደድንበት ሀገር እንኳን ሊያስቀምጡን አልቻሉም በሆድ የገዛቸው ደጋፊዎቹ …. እንኳንስ ሌላ። የተከበሩ ዬአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ታላቅ እህት ምን ነበር የተፈጸመባቸው?! …. ስለዚህ መንፈሱ በዘመነ ወያኔ እንዳአለ የታጠሰ አንቀጽ ነው። እናም — ዜሮ

„አንቀጽ፡ 14፤ „1/፡ እያንዳንዱ ሰው ከጭቆና ሸሽቶ በሌሎች አገሮች ጥገኝነትን የመጠየቅና በደህና የመኖር መብት አለው።“ ወያኔ እያለ እንዴት ተብሎ? …. በበቀል በተነከረ የደም ጥማቱ፤ በመርዝ በተገኘው ነገር ሁሉ እያደነ ሰላም ይነሳል እንጂ … ኢትዮጵያ ያሉት ብቻ ሳይሆን ተሰደንም አልተኛልንም ወያኔ ስለዚህ ውጤቱ – ዜሮ

„2/፡ ፖለቲካዊ ካልሆኑ ወንጀሎች ወይም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ዓላማዎችን ከሚቃረኑ ሥራዎች የተነሳ በሚደርሱ ክሶች ምክንያት ከሆነ ይህ መብት ሊያገለግል አይችልም።“ ወይ ጉድ ኢትጵውያን እኮ ፈርሃ እግዚአብሄር ያለን ለህገ እግዚአብሄር ሆነ ለሰው ሰራሽ ህግጋት ትሁትና ቅን መንፈስ ያለን ሰላማዊ ዜጎች ነን። አብዛኞቻችን ኢትዮጵውያን በተሰደድነብት ሀገር ጸጥ ለጥ ብለን ነው የምንኖረው። ለጎረቤት፣ ለሥራ ባልደራባዎች ሁሉ የምንመች። ህግ የማይገዛው ሥራዓት የማያስተደድረው ወያኔና ማንፌስቶው ብቻ ናቸው።

„አንቀጽ፡15፤  „1/፡ እያንዳንዱ ሰው የዜግነት መብት አለው።“ ዜግነት በኢትዮጵያ ከተሰረዘ 24 ዓመት ሆነው። ዜግነት ትግሬነት ሆኗል። ስለዚህ ኢትዮጵያዊ ዜግነት እራሱ „ጽንፈኛ ብሄርተኛ“ እዬተባለ በጎሰኛው ወያኔ የሞት ፍርድ የታወጀበት ነው። የዜግነት ክብር ግርማና ሞገስ ፈተና ላይ ናቸው። ዜግነት ታስሯል። ወያኔ እንደ ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሚፈራውም አንዳችም ነገር የለም። ስለዚህ ያለው ጡንቻ ሁሉ የሚያርፈው ከዜግነት ላይ ነው። ስለዚህ የአፈጻጻሙ ክብርና ሂደቱ  – ዜሮ ነው።

„2/፡ ማንም ሰው ያለፍርድ ዜግነቱ አይወሰድበትም ወይም ዜግነቱን የመለወጥ መብት አይነፈገውም።“ ህም ነው …. ድንጋጌውንና በደሉን ማጠጋጋት ወይንም ማቀራረብ እንኳን አይቻልም ስለሆነም ይህም ዜሮ፤

„አንቀጽ፡16፤  1/፡ አካለ መጠን የደረሱ ወንዶችና ሴቶች በዘር በዜግነት ወይም በሃይማኖት ልዩነት ሳይወሰኑ ጋብቻን የመፈጸምና ቤተሰብን የመመሥረት መብት አላቸው፤ ጋብቻ በመፈጸም በጋብቻ ጊዜና ጋብቻ በሚፈርስበትም ጊዜ እኩል መብት አላቸው።

2/፡ ጋብቻ የሚፈጸመው ጋብቻ ለመፈጸም በሚፈልጉ ሁለቱም ወገኖች በሚያደርጉት ነጻና ሙሉ ስምምነት መሠረት ብቻ ነው።

3/፡ ቤተሰብ በኀብረ ሰብ የተፈጥሮና መሰረታዊ ክፍል ስለሆነ በኀብረሰቡና በመንግሥቱም ደህንነቱ እንዲጠበቅለት ይገባል።“

አነኝህን ድንጋጌዎች በነጠለ ትርጉማቸው ስንወስዳቸው በሞራ የተሸፈነ ብልጭልጭ የሚል አስመሳይ ደወሎች አሉበት። ወደ ውስጥ ስንዘልቅ ግን በሀገራችን በሚፈጸሙት ሶስት የጋብቻ ሥርዓቶች በሃይማኖታዊ፤ በባህላዊ እና በብሄራዊ ጋብቻ የጋብቻ ቀደምት ባህል፤ ትውፊትና ታሪክ ጠቀራ ለብሰዋል። የወልቃይትና የጠገዴ ሴቶች ልጆቻቸው በእናታቸው ሥም ነው የሚጠሩት፤ በአማራው ብሄረሰብ ልጅ እንዳይወልዱ የተሰጠው ክትባት የትድርን ዶግማ በቀጥታ የሚጻረር ነው። ወያኔ የጋብቻ መንፈስ ሸቀጥ እንዲሆን የሚደረገው ግፊት ብቻ ሳይሆን ጋብቻን ፍቅር ሳይሆን ዞግ – መራሽ እንዲሆን ስውር ተጽዕኖ ያደርጋል። ተጽዕኖውም ሆነ ተጠቂነቱም ከፍ ያለ ነው። ከዚህ በላይ በግፍ ስደቱ — እስራቱ – ሞቶ የጋብቻን ተፍጥሮ ድራሹን ነው ያጠፋው። ስለዚህ ከዋናው አምክንዮ ህግና ከአፈጻጻሙ ስውር ደባ አንፃር የውጤቱ ዝንባሌ ወደ ዜሮ ይሸኛል ….

„አንቀጽ፡17፤  „1/፡ እያንዳንዱ ሰው ብቻውን ወይም ከሌሎች ጋር በኀብረት ሆኖ የኀብረት ባለቤትነት መብት አለው።“ በጎሳ መንፈስ፤ በባለ ጊዜነት ዕይታ ከሆነ አዎን። እንደ ዜጋ ሲሰላ ግን ኢትዮጵያ ላይ አንቀጹ ከቦታው ተስርዟል። ስለሆነም ውጤቱ — ዜሮ።

„2/፡ ማንም ሰው ያለፍርድ ንብረቱ አይወሰድበትም።“ ፍርድ ቤት ሲኖረን ነው። እኛ ፍርድ ቤት፤ ለህዝብ ጥቅም የቆመ ሚዛን፤ ለሙያው ኪዳን ራሱን የሰጠ ርትሃዊ ሥርዓት የለንም። ስለዚህ ይህም ዜሮ

„አንቀጽ፡18፤ እያንዳንዱ ሰው የሃሳብ የሕሊናና የሃይማኖት ነጻነት መብት አለው። ይህም መብት ሃይማኖቱን ወይም እምነቱን የመለወጥ ነጻነትንና ብቻውን ወይም ከሌሎች ጋር በኀብረት በይፋ ወይም በግል ሆኖ ሃይማኖቱን ወይም እምነቱን የማስተማር፣ በተግባር የመግለጽ የማምለክና የማክበር ነጻነትን ይጨምራል።“ ኢትዮጵያ ላይ የአንቀጹ ጭብጥ ተግባራዊነት መሃን ነው። ስለዚህ ቁልጭ ያለ — ዜሮ

„አንቀጽ፡19፤ እያንዳንዱ ሰው የሐሳብና ሐሳቡን የመግለጽ መብት አለው። ይህም መብት ያለጣልቃ ገብነት በሐሳብ የመጽናትንና ዜናን ወይም ሐሳቦችን ያላንዳች የድንበር ገደብ የማግኘትን የመቀበልን ወይም የማካፈልን ነጻነትም ይጨምራል።“ ታላቁ የወያኔ የጥቃት ኢላማ ምን ሆነና – ያውም ወደልዜሮ

„አንቀጽ፡20፤ „1/፡ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ በሰላም፡ የመሰብሰብና፡ ግንኙነት፡ የማድረግ፡ ነጻነት፡ መብት፡ አለው።“ ኢትዮጵያ ላይ የለውም። የሰሞኑ  ዬሰማያዊ ቢሮ ፎቶ ብቻ በቂ ነው። ስንቱስ ተዘርዝሮ ያልቅና። ስለዚህ ውጤቱ – ዜሮ

„2/፡ ማንም፡ ሰው፡ የአንድ፡ ማኀበር፡ አባል፡ እንዲሆን፡ አይገደድም።“ ወያኔ አስገድዶ – በገንዘብ ገዝቶ ነው አባል የሚያደርገው፤ አባልነት በፈቃደኝነት መርሁ ተዘቅዝቆ የተሰቀለ ነው። ስለዚህ – ዜሮ

„አንቀጽ፡21፤ 1/፡ እያንዳንዱ፡ ሰው፡በቀጥታ፡ ወይም፡ ነጻ፡ በሆነ፡ መንገድ፡ በተመረጡ፡ እንደራሴዎች፡ አማካኝነት፡ በአገሩ፡ መንግስት፡ የመካፈል፡ መብት፡ አለው:“ ወይ መዳህኒተ ዓለም አባቴ በጎጥ ሶሻሊዝም ይህ ቅዱስ መንፈስ በቢላዋ ነው ዓይኑን ወያኔ ያወጣው። ስለዚህ – ዜሮ

„2/፡ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ በአገሩ፡ የህዝብ፡ አገልግሎት፡ እኩል፡ የማግኘት፡ መብት፡ አለው።“ ለባለወርቅ ሊሆን ይችላል። ለግዕፋኑ ግን አይሠራም። ስልሆነም – ዜሮ።

„3/፡ የመንግስት፡ ሥልጣን፡ መሠረቱ፡ የሕዝቡ፡ ፈቃድ፡ መሆን፡ አለበት። ይህም፡ ፈቃድ፡ ለሁሉም፡ እኩል፡ በሆነ፡ በምሥጢር፡ በሚደረግ፡ የድምፅ፡ መስጠት፡ ምርጫ፡ ወይም፡ በተመሳሳይ፡ ሁኔታ፡ በየጊዜውና፡ በትክክል፡ በሚፈጸሙ፡ ምርጫዎች፡ እንዲገለጽ፡ መሆን፡ አለበት።“ አውሬን የሚፈቅድ፤ አራጅን የሚፈቅድ፤ አግላይን የሚፈቅድ፤ ገዳይን የሚፈቅድ ህዝብ የለም። ስለሆነም ድንጋጌው መልካም ሆኖ ሳለ በጎሳ ገዢወች የታፈነው ዬኢትዮጵያ ህዝብ ፍርፋሪውን ወይንም የድንጋጌውን ጸበለ ጻዲቅ ሊያገኝ አልቻለም። በቃህኝ! ካለ እኮ ቆዬ። 97 እኮ ንቅንቅ ብሎ ወጥቶ ነበር ባዶውን ያስቀረው። ረሃብን የሚፈቅድ ማን አለና? ክብር መጣስን የሚሻ ማን አለና? ስለዚህ ዜሮን በሞራ ጠቅሎ የዓለምን ህዝብ የሚያባጭልበት የእዬአራት አመቱ ምርጫ ከህዝብ ፈቃድ ውጪ በተጎማጀ አውሬያዊ መንገዱ ያስፈጽመዋል። በመሆኑ የድንጋጌው ድርጊተኝነት ኢትዮጵያ ላይ … ጠፍጣፋ ዜሮ።

„አንቀጽ፡22፤ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ የኀብረ፡ ሰብ፡ አባል፡ እንደመሆኑ፡ በኀብረ፡ ሰብ፡ ደህንነቱ፡ እንዲጠበቅ፡ መብት፡ አለው። እንዲሁም፡ በብሔራዊ፡ ጥረትና፡ በኢንተርናሽናል፡ መተባበር፡ አማካይነትና፡ በእያንዳንዱ፡ መንግስት፡ ድርጅትም፡ የሀብት፡ ምንጮች፡ መሰረት፡ ለክብሩና፡ ለሰብዓዊ፡ አቅሙ፡ ነጻ፡ እድገት፡ የግድ፡ አስፈላጊ፡ የሆኑት፡ የኤኮኖሚ፡ የማኀበራዊ፡ ኑሮና፡ የባህል፡ መብቶች፡ በተግባር፡ እንዲገለጹለት፡ መብት፡ አለው።“ ህዝባዊ መንግሥት ሲኖር፤ በህዝብ ፈቃድ ሥልጣን የተሰጠው ሃላፊነት የሚሰማው ሥልጡን ሥርዓት ሲኖር ብቻ፤ በአስተሳሰብ ድህነት ለተወረረው ዬወያኔ ሥርዓት ግንዛቤ  ግን – ሳይፈጽመው ዜሮ ላይ አስክኖታል።

„አንቀጽ፡23  „1/፡ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ የመሥራት፡ የሥራ፡ ነጻ፡ ምርጫና፡ ለሥራም፡ ትክክለኛና፡ ተስማሚ፡ የአሠራር፡ ሁኔታዎችና፡ ሥራም፡ እንዳያጣ፡ መብት፡ አለው።“ አለን ይሄ ኢትዮጵያ ላይ ….?! የድንጋጌው መሪ የጎጥ ድርጅት አባልነት ብቻ ነው። ስለዚህ ለምልዕቱ የድናጋጌው ትርፋማነት ኢትዮጵያ ላይ — ዝክንትል ዜሮ።

„2/፡ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ያላንዳች፡ ልዩነት፡ ማድረግ፡ ለአንድ፡ ዓይነት፡ ሥራ፡ እኩል፡ የሆነ፡ ደመወዝ፡ የማግኘት፡ መብት፡ አለው።“ ኢትዮጵያዊነቱን ለሚያስቀድም ብቁ ዜጋ፤ ነፃነት ከ እኔ መጀመር አለበት ለሚል ብልህ፤ አቅም ላለው ዜጋ ይህ አንቀጽ አይሰራም። — ለድውያኔ፣ ለደካሞች፣ ለአቅመ ቢሶች  ዬአስተሳስብ ድህነት ለረበባቸው ግን ይሠራል። ስለዚህ ህገ – ትርጓሜው የእኩል ተጠቃሚነትን ስለማይተረጉም — አድሎዊ ስለሆነ ኢትዮጵያ ላይ ውጤቱ – ደጎስ ያለ ዜሮ።

„3/፡ በሥራ፡ ላይ፡ ያለ፡ ሰው፡ ለእራሱና፡ ለቤተሰቡ፡ ለሰብዓዊ፡ ክብር፡ ተገቢ፡ የሆነ፡ ኑሮን፡ የሚያስገኝለትና፡ ካስፈለገም፡ በሌሎች፡ የኀብረሰብ፡ ደህንነት፡ መጠበቂያ፡ ዘዴዎች፡ የተደገፈ፡ ትክክለኛና፡ ተስማሚ፡ ዋጋውን፡ የማግኘት፡ መብት፡ አለው።“ ያው ለጎሳው ሊሠራ ይችል ይሆናል። ለኢትዮጵያዊነት ግን ኢትዮጵያ ላይ ጣር ነው። ስለዚህ - ከዜሮም ጎባጣው።

„4/፡ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ ጥቅሞቹን፡ ለማስከበር፡ የሙያ፡ ማኀበሮችን፡ ለማቋቋምና፡ ማኀበርተኛ፡ ለመሆን፡ መብት፡ አለው።“ በጎሳ መንፈስ ብቻ ለተደራጀ። በብሄራዊነትን ለመግደል ለሚተባባር ሃይል ብቻ አልጋ ባልጋ ነው መንገዱ ነው። ለነፃነት ዘንካቲት ግን የሀገራዊነትን መንፈስ ለፈቀደ አይሠራም ድንጋጌው ሽባ ነው ስለዚህ ማርኩ – ዜሮ።

„አንቀጽ፡24፤ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ የዕረፍትና፡ የመዝናናት፡ እንዲሁም፡ በአግባብ፡ የተወሰኑ፡ የሥራ፡ ሰዓቶች፡ እንዲኖሩትና፡ በየጊዜው፡ የዕረፍት፡ ጊዜያትን፡ ከደመወዝ፡ ጋር፡ የማግኘት፡ መብት፡ አለው።“ ይሄን ድንጋጌ አንባቢ ብቻ ሳይሆን በህይወቱ ያሉ ይለኩት።

„አንቀጽ፡25፤ 1/፡ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ ለእራሱና፡ ለቤተሰቡ፡ ጤንነትና፡ ደህንነት፡ ምግብ፣ ልብስ፣ ቤትና፡ ሕክምና፡ አስፈላጊ፡ የማኀበራዊ፡ ኑሮ፡ አገልግሎቶችም፡ ጭምር፡ የሚበቃ፡ የኑሮ፡ ደረጃ፡ ለማግኘት፡ መብት፡ አለው። ሥራ፡ ሳይቀጠር፡ ቢቀር፡ ቢታመም፡ ለመሥራት፡ ባይችል፡ ባል፡ ወይም፡ ሚስት፡ ቢሞት፡ ቢያረጅ፡ ወይም፡ ከቁጥጥሩ፡ ውጭ፡ በሆኑ፡ ምክንያቶች፡ መሰናከል፡ ቢገጥመው፡ ደህንነቱ፡ እንዲጠበቅለት፡ መብት፡ አለው።“

„2/፡ ወላድነትና፡ ሕጻንነት፡ ልዩ፡ ጥንቃቄና፡ እርዳታ፡ የማግኘት፡ መብት፡ አላቸው፤ በጋብቻ፡ ወይም፡ ያለጋብቻ፡ የሚወለዱ፡ ሕጻናትም፡ የተመሳሳይ፡ የደህንነታቸው፡ መጠበቅ፡ መብት፡ አላቸው።“ ሁለቱም ንዑሳን ድንጋጌዎች ድምጽ የሚመራት ሀገር ስትኖረን ነው። ከዓለም ሶስት የመጨረሻ ደሃ ሀገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ናት። ሟርቱ ተሳክቶለታል። ኢትዮጵያ ስንት ትውልድ ሊከፍለው እንደሚችል አይተወቅም በዕዳ የተዘፈቀች፤ በብዙ ውስብስብ ፈተናዎች ለመፍታት የሚፈልገው መዋዕለ መንፈስ እራሱ … ህም። ለማንኛውም በሁለመናዋ በወያኔ እስር ለተፈረደባት ሀገር የህልም ገነት የሆነ አንቀጽ ነው። ስለዚህ የወደቀ ለቅሞ ለመብላት ተራ፤ ለዛም የሚጥል በሌለበት ሀገር  ስለሆነ የድንጋጌው ተፈጻሚነት ለጥቂት ወንበዴዎችና ቤተሰቦቻቸው ብቻ ይሆናል – ዜሮ።

„አንቀጽ፡26፤ 1/፡ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ የመማር፡ መብት፡ አለው። ትምህርት፡ ቢያንስ፡ ቢያንስ፡ በአንደኛ፡ ደረጃና፡ መሰረታዊ፡ ደረጃዎች፡ በነጻ፡ ሊሆን፡ ይገባል። የአንደኛ፡ ደረጃ፡ ትምህርት፡ መማር፡ ግዴታ፡ ነው። የቴክኒክና፡ የልዩ፡ ልዩ፡ ሙያ፡ ትምህርት፡ በጠቅላላው፡ የከፍተኛ፡ ደረጃ፡ ደግሞ፡ በችሎታ፡ መሠረት፡ ለሁሉም፡ እኩል፡ መሰጠት፡ አለበት።

2/፡ ትምህርት፡ ለእያንዳንዱ፡ ሰው፡ ሁኔታ፡ ማሻሻያና፡ ለሰብዓዊ፡ መብቶችም፡ መሠረታዊ፡ ነጻነቶች፡ ክብር፡ ማዳበርያ፡ የሚውል፡ መሆን፡ አለበት። እንዲሁም፡ የተለያየ፡ ዘር፡ ወይም፡ ሃይማኖት፡ ባሏቸው፡ ሕዝቦች፡ መካከል፡ ሁሉ፡ መግባባትን፡ ተቻችሎ፡ የመኖርንና፡ የመተባበርን፡ መንፈስ፡ የሚያጠነክርና፡ የተባበሩት፡ መንግሥታት፡ ድርጅት፡ ሰላምን፡ ለመጠበቅ፡ የሚፈጽማቸው፡ ተግባሮች፡ እንዲስፋፋ፡ የሚያበረታቱ፡ መሆን፡ አለበት።

3/፡ ወላጆች፡ ለልጆቻቸው፡ ለመስጠት፡ የሚፈልጉትን፡ ትምህርት፡ ለመምረጥ፡ የቅድሚያ፡ መብት፡ አላችው።“ እንኝህን የሥልጣኔ መሠረት የሆኑት የዕውቀት ግንባታና መሠረት በጥቅሉ ሲታይ፤ የትምህርቱ ደረጃም የሚለካውና የሚመዘነው ከሥርዓቱ ጥንካሬና ከጠንካራ ፖሊሲዎቹ ከሚፈልቁ ጉልበታም ተግባራት ነው። በዘመነ ወያኔ ታላቅ ውድቀት ከደረሰባቸው አንዱ ትምህርትና የትምህርት ተዋዖው ነው። የትምህርት ሥርጭቱ ያልተመጣጠነ አድሎ የዘፈነበትና ነገን ያሳረር፤ ዬትናንትን ታሪካዊ ሃብታትን ያለርህራሄ ያቃጠለ ነው። ዝርክርክ „የእነ ተሎ ተሎ ቤት ግድግዳው ሰንበሌጥ“  ለዜሮም መቅኑ የፈሰሰ – ዜሮ

„አንቀጽ፡27፤ 1/፡ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ በኀብረተ ሰቡ፡ የባህል፡ ኑሮ፡ በነጻ፡ መካፈልና፡ በኪነ፡ ጥበብ፡ ለመጠቀም፡ በሳይንስ፡ እርምጃና፡ በጥቅሞቹም፡ ለመሳተፍ፡ መብት፡ አለው።

2/፡ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ ከደረሰው፡ ማንኛውም፡ የሳይንስ፡ የድርሰትና፡ የኪነ፡ ጥበብ፡ ሥራ፡ የሚያገኘው፡ የሞራሉንና፡ የሃብት፡ ጥቅሞች፡ እንዲከበሩለት፡ መብት፡ አለው።“ ዬትውልድ መጸሐፍ የሆነው አርቲስት ወጋዬሁ ንጋቱን ያልተካ የትውልድ ማገር የሆነውን አርቲስት ደበበ እሸቱን የህዝብ ሃብትነቱን ያሰረ፤ ጸጋውን የለጎመ። አዬ! በአንድ ባለቅኔ ቴዲ አፍሮ የሚደረሰው ፍዳና መከራ በቂ ነው። ከብሄራዊነት የሚነሱ ማናቸውም አምክንዮዎች የሚመጠብቃቸው ዱላ ነው። ስለዚህ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከጎሳ ማኒፌስቶ ወራጅ ውሃ የተጠለለ ከሆነ – ምን አልባት። በተረፈ ለዛውም ለሥነ ጥበብ ነፃነት የጋዜጠኞች የጸሐፍት ፍልሰት ምንጩ ምን ሆነና። የዚህ ዬፍትህ ሥርዓት የተስተካካለ ይሆናል ብሎ ማሰብ ጮርቃነት ነው። ለዚህም ነው ዬነፃነት ትግሉ ብጥቅጣቂ ነገሮችን ዘግቶ አጠቃላይና ሥር ነቀል በሆኑ ሁኔታዎች ላይ አቅሙንም ጉልበቱንም የመንፈስ ሃብታትም መፍስስ አለበት የሚባለው። ከአጠቃላዩ የጎጥ አስተዳደር መንፈስ የጥልቅ ግልጽ ጥቃቱና ከሥውር ደባው ስንነሳ የዚህ አንቀጽ ተፈጻሚነት ኢትዮጵያ ላይ – የተድበለበለ ዜሮ ነው።

„አንቀጽ፡28፤ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ በዚህ፡ ውሳኔ፡ ውስጥ፡ የተዘረዘሩት፡ መብቶችና፡ ነጻነቶች፡ በሙሉ፡ በተግባር፡ እንዲውሉ፡ ለሚደረግባቸው፡ የኀብረሰብና፡ የኢንተርናሽናል፡ ሥርዓት፡ የመጠቀም፡ መብት፡ አለው።“ ለመብቱ ባይታወር የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ግዴታውን ለመፈጸም ይችላል። ይህ ማለት ብዙሃኑ ነፃነቱን ተነጥቆ ለተነጠቀው ነፃነት ዘብ ቁሞ ያድራል። ከጣና የተሳባው የመብራት ሃይል ትግራይ እስኪደርስ ድረስ ያለፈባቸው መንገዶችን እንደጨለመባቸው ሲሆን፤ ነገር ግን የመብራቱን ወጋግራ ባለፈባቸው ቦታዎች ያሉ ንጹኃን ቁመው ሲጠብቁ ውለው ያደራሉ። ማለት ብዙሃኑ ለማይጠቀምበት ቁሞ መብራት ይዞ ቁርስ ራት ምሳ ያበላል – ለባለጊዜው። እሱ ግን እንደ ተራበ። ለዛውም አንጡራ ሃብቱ ሆኖ። የበደሉ ልክ እኮ የለውም። ለነጌቶቹ መብራት ይዞ –  ለብዙሃኑ ግን ምንም – ያው ዜሮ።

„አንቀጽ፡29፤  1/፡ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ የራሱ፡ ነጻነትና፡ ሙሉ፡ መሻሻል፡ በሚያገኝበት፡ ኀብረሰብ፡ ውስጥ፡ የሚፈጽማቸው፡ ግዴታዎች፡ ይኖሩበታል።

2/፡ እያንዳንዱ፡ ሰው፡ በመብቶቹ፡ በነጻነቶቹ፡ በሚጠቀምበት፡ ጊዜ፡ የሚታገደው፡ የሌሎችን፡ መብቶችና፡ ነጻነቶች፡ በሚገባ፡ ለማሰከበር፡ ብቻ፡ በተደነገጉ፡ ሕጎችና፡ የግብረ፡ ገብነትን፡ የጠቅላላውን፡ ሕዝብ፡ ፀጥታና፡ ደህንነት፡ በዴሞክራቲክ፡ ማኀበራዊ፡ ኑሮ፡ ትክክለኛ፡ የሆነው፡ ተፈላጊ፡ ጉዳይ፡ ለማርካት፡ በተወሰነው፡ ብቻ፡ ነው።

3/፡ እነዚህ፡ መብቶችና፡ ነፃነቶች፡ በማንኛውም፡ ሁኔታ፡ የተባበሩት፡ መንግሥታት፡ ድርጅት፡ መሰረት፡ ዓላማዎች፡ ተቃራኒ፡ በሆነ፡ መንገድ፡ ሊፈጸሙ፡ አይገባቸውም።“ ህግ መተላለፍ ከወያኔ በስተቀር ኢትዮጵያዊ ተፈጥሮ አይፈቅደውም። ስለዚህ ህግ ጣሹ ወያኔ ለህግጋቱ ሳይገዛ እዬዳጠና እዬደፈጠጠ የሚሄደውን ነገር ማስቆም የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ግዴታ ነው።

„አንቀጽ፡30፤ በዚህ ውሳኔ ከላይ የተዘረዘረው ሁሉ በዚሁ ውስጥ የተጠቀሱትን ማናቸውም መብቶች ወይም ነጻነቶች ለማበላሸት በታሰበ ማንኛውም ዓይነት ተግባር ለማዋል ወይም ድርጊትን ለመፈጸም ለማንኛውም መንግሥት ወይም ድርጅት ወይም ሰው የተባሉ አይተረጎሙም“ ወገኖቼ  እነዚህ ድንጋጌዎች ለዬሀገሮች ማስተማሪያ ብቻ ሳይሆኑ እንዲፈጸሙ፤ የህግ ጥበቃና ድጋፍ፤ እንዲሁም ክትትልና ቁጥጥር ሊደረግባቸው የሚገቡ የነባቢተ – ነፍስ ንጹህ የአዬር መስጫ ቧንቧዎች ናቸው። የተባበሩት መንግሥታት አባል ሀገሮች አኃታዊ ህገ መንግሥት፤ እናት ህግ ብለው ይሻል ይመስለኛል።

ከ1948 በኋላም ቢሆን በተለያዩ ጊዜያቶች ብዙ የማጠናከሪያ፤ የማጉያ አትኩሮት ተስጥቷቸዋል። በተለይ በ2007 እና በ2008 ጥልቅ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሰፊ አምክንዮዊ መንፈሶች በተጨማሪነት አድገዋል፤ ግን በወያኔ ባዶ ናቸው። ወያኔ የመስሚያ ታንቡሩ የተነፈስ ነውና። በ2007 እና በ2008 ሰፊ አትኩሮት የተሰጣቸው ጥልቅ የሰብዕና ህላዊ ጉዳዮች Durban Declaration constitutes  – racism, racial discrimnation, xenophobia and related intolerance በመፈጸም የድርጊት ጀግኖች ተብለው ለናሙና ከተመረጡት ሀገሮች ጥቂቶችን እስኪ ላንሳ።

አንዷ አርመንያ ነበረች። አረመንያ በፆታ እኩልነት ፍጹም የሆነ ጥበቃና ክትትል የምታደርገው ህግ በማውጣት ብቻ ሳይሆን፤ ለወጣው ህግ ጠንከራ ጠበቂ ተጨማሪ ህግ አውጥታ ሥራ ላይ በማዋል ነው፤ ድንቋ አርመንያ የሥራ ባርነት በፍጹም ሁኔታ የተወገደባት ሀገር ናት። ስለ ሰብዕዊ መብት በህጋዊ ትምህርት ቤቶች፣ በክበቦች፣ በካንፓሶች በነፃ ውይይት ይደረግበታል። አብሶ ለወጣቶች በትጋት እንደ ሃይማኖታዊ ዶግማ ይሰበከል። በአርመንያ 8ኛ ክፍል ላይ እንደ አንድ የትምህርት ሳብጀክት የሰብዕዊ መብት (Human Rights) ትምህርት ለተማሪዎች ይሰጣል።

ለንጽጽር እንዲረዳም – ከእማማ አፍሪካ ውስጥም ቢሆን አልጀሪያ ለተምሳሌ የተመረጠች ሀገር ናት። በብዙ ፈተና ውስጥ ያለፈችው አልጀርያ ለዚህ ክብር የበቃች ሀገር ናት። ዬ60 ብሄረሰቦች እናት የሆነቸው ቡርኪናፋሶ ዘረኝነትን፤ ግለላን፣ የሰው ልጅ ጥላቻን፤ ንቀትን በአዋጅ ያስቀረች ለሰብዕዊ መብት መከበር ጥልቅ ፍላጎቶች የተስማማች ሀገር ናት። ቀደምቷ የሰው ልጅ መፈጠሪያ እናት ሀገር ፍርጃ ደግሞ በጎሳ መከታከት። ባለፈም ሰብዕዊ መብት ቃሉን መጥራት የማይፈቀድባት፤ የሰብዕዊ መብት አፈጻጸም የሲኦልና ዬሃሞት ሀገር አድርጓታል – ወያኔ። አንዲት ስንጥር ደግ ነገር ፈጽሞ ማግኘት አይቻልም። ሀገር ማለት እኮ የእኔ ውዶች ዓለም አቅፍ ዕውቅና ባለው ድንበር ውስጥ የሰዎች ማህበር ማለት ነው። ማህበሩ ከተጠቀጠቀ፣ ከፈረሰ፣ ከተዘለለ ሀገር የለም። የሀገር መነሻው ሰው ነው። ዬማናቸውም ፍላጎት መነሻው ከሰው ምቹ ተፈጥሮ መሆን አለበት። ወያኔ ግን ተነሳፎ ነው ያለው። መነሻ ቢስ – ከንቱ ስለሆነ። ቀድሞ ነገር ለሰው ልጅ ማህበራዊ እድገት ንቀት ብቻ ሳይሆን እድገቱን የሚጸዬፍ ወያኔ ብቻ።

ክብሮቼ ልክውነው ….  ቁምነገሩ እኛስ ህልማችን ምንድን ይሆን? እነዚህን ህግጋት በውስጣችን አድርገን፣ ነገ የምናልማት ኢትዮጵያን በመንፈሳችን ይዘን፣ የአርነት ትግሉን ስናጠነክር ብቻ ለውጤት እንበቃለን። ግን አራሳችን ማዘዝ ስንችል ብቻ ነው። እንደገናም እኛስ በሌሎቹ ላይ ህግን ተላልፈን ምን በደል ፈጸምን ይሆን? ይሄ ሌላው የነገ የኢትዮጵያ ጥልቅ ፈተና ነው። ዛሬ አረሙ ካልጸዳ ነገም ይህ በደል ይፈጸማል። ከዚህ ላይ አንድ ምሳሌትን ላንሳ አንቀጽ 13ን ንዑስ አንቀጽ  „2/፡ እያንዳንዱ ሰው ከማንኛውም አገር ሆነ ከራሱ አገር ወጥቶ እንደገና ወደ አገሩ የመመለስ መብት አለው።“  ወገኖቻችን ኢትዮጵያ ሀገራቸውን አይተው የሚመጡትን ወንጀለኛ እናደርጋቸዋለን። ሲያስፈልግም መረብ ዘርግተን ማህበራዊ ግንኙነታቸውን ሁሉ ጢስ እናለብሰዋለን። አቅማችን ከበላው መሰረታዊ ጉዳይ አውራው ስለሆነ ነው ይህን ያነሳሁት። ይህ የተገባ አይደለም። የሚችሉ መሄዳቸው ዓለምዓቀፍ መብታቸው ነው። ኢትዮጵያ እጅግ እንደ ሰው የምትናፈቅ ሀገር ናት። መቀመጫውን ፓሪስ ያደረገ አንድ ዓለማቀፋዊ ዬኢኮኖሚ እድገት አያያዝና አገልግሎትን ጥራት አበረታች ድርጅት Business Initiative Directions (BID) ጉባኤ የሽልማት ሥርዓት ላይ በሥርዓቱ የተገኙ አንድ አዛውንት ስለ ሀገር ናፍቆት ጠይቄያቸው እንዲህ ነበር ያሉኝ „መኪና ውስጥ ሆኖ ምግብ ታዞ፤ አስተናጋጅ መጥቶ የሚያሰተናግድባት ብቸኛ ሀገር እኮ ናት – ኢትዮጵያ ለምን አትናፍቅ?!“ ስለዚህ እውነት እኛ እራሳችን መለወጥ አለብን።

እምዬ ሀዘን ላይ ብትሆንም፤ ጉስቁልናዋን ሄዶ ማዬት የነፃነት ትግሉን ያጎለበተዋል እንጂ አያሰልለውም። ብዙ ዓይነት መረጃዎች፤ የዓይን ምስክሮች ይገኛሉ። በዚህ ዙሪያ እራሱን የቻለ ተከታታይ አቅም ያለው ተግባር ቢከውን ስንት ምርት ይታፈስበታል።  እርግጥ የወያኔን ባይረስ ተሸክመው የሚመጡ ሊኖሩ ይችላሉ። እኛ አቅም አለን። እውነት አለን። ቁጭ ብለን ሞግተን የእኛ ሃብት ማድረግ እንችላለን። ዝም ብሎ በጅምላ ማዋከቡ፤ ማግለሉ ግን እንደ ለእኔ ህግን መተላለፍ ይመስለኛል። „ህግ ተላላፊዎችን ጠላሁ“ አለ ነብዬ እግዚአብሄር ዳዊት። ህግ ወያኔ ጣሰ ለማለት እኛ እራሳችነን በህግ ሥር ማሳደርን ይጠይቅ ይመስለኛል። አንዳንድ ጊዜ ከሰብዕዊ መብት የተነሱ ሃይማኖታዊ ሆኑ ዓለምዓቀፍ ህግጋት ጋር የመራራቅ ችግርም ያለብን ይመስለኛል።

ይህም ብቻ አይደለም በኪነጥበብ ዘርፍም አንቀጽ 27 ሃብትነቱ የህዝብ ሆኖ ለጥበበኛው የሚጣለው ማዕቀብ የብዙሃኑ ታዳሚ መብትን ይገጣል። አንቀጽ 18፣ ቢሆን ሃስብን – ፍላጎትን – ዕይታን  – ተቃውሞን – ድጋፍን የመግልጽ ነፃነት በትክክል መፈጸም ካልቻልን ነገን ያቀጭጫል። አሁን እኔ ዘሃበሻ ነፃነቴን ባያውጅልኝ በምን እንገናኝ ነበር። ነፃነት የሰው ልጅ ባገኘ ቁጥር ውስጡን ገልጦ ያሳያል። ውስጡን ግልጦ ባሳዬ ቁጥር ደግሞ የመፍትሄው አቅጣጫ ይታወቃል። አይደለም ከሚያግዝ፣ ዬማያግዝ ሃሳብም ልግሞ በውስጥ ከሚያዝ ቢወጣ፤ ያበጠው መተንፈሻ ቧንቧ ይሠራለትን እና መግሉ እንዲወጣ፤ ቁስሉ እንደ አባት አደሩ እንዲድን መፈወሻ ያገኛል። የማይድን ሲሆን ደግም አገላብጦ አይቶ በማሰናበት ጊዜን በአግባቡ ማስተዳደር ይቻላል።። ግን ለማድመጥ ስንፈቅድ ብቻ ነው። እኛ እራሳችን ነፃነትን ለሌለው ነፃነት በመስጠት መደባችን የት ላይ ይሆን?!

አያድርግብኛ እንጂ አንድ ምሳሌ ባነሳ „እኔ ወያኔ ብሆን¡“ ሎቱ ስብሃት ስለቃሉ ይቅር ይበለኝ አምላኬ ጋዜጠኛ ተመስገንን አላስርም ነበር። ስለምን? „የቅርብ ሟዕት የቹቻ መንከሪያ ይሆናል“ ይላል ጎንደሬ ሲተርት። ትእግስቱ ተመስገን ትልቅ ዋርካ ነበር። ከትንሿ ሰቀቅን ተነስቶ የህዝብን የውስጥ ስሜት እንደ ሃኪም መርምሮ፤ ትችቱን – መፍትሄውን – ቁልፉን በድፍረት ይናገራል። ፈውሱ ነበር ለወያኔ ግን በምን አቅል? ሽንፍላ። የተሜ ትንተናው የተቋም ያህል ከልብ ነበር። ደፋር ትችቱ ነገን አቃንቶ የማምጣት ልዩ አቅም ነበረው። ከህዝብ ውስጣዊ የሞቀ ወይንም ለብ ያለ ወይንም የበረደው ስሜት ተነስቶ የሚሰጠው ትንተና ለወያኔ መዳኛው መፈወሻው ልዩ ማሰልጠኛው ነበር። ሌላው አዛውንቱ ብዕረኛ ጋዜጠኛ እስክንድር የመንፈስ ዓይን ነበር። ሌሎች የብዕር አርበኞቻችንም ዕድሉን ቢያገኙ መዳህኒትም – መዳኛ ነበሩ። ለአንድ ሥልጡን ማህበረሰብ ህዋሱ የደፋር ጋዜጠኞች መኖር ነበር። ግን አልተቻለም። የነፃነት እራህብን በራህብ ቆላው፤ የነፃነት እርሃብን በራህብ አንገረገበው ጆፌው አሞራ።

አብርሽም ቢሆን ወያኔ  ከሚመካበት ማህበረሰብ የወጣ ወጣት ስለነበር፤ ጭራቁ የጎጥ ዶክተሬን በአዲሱ ትውልድ ዕይታ ምን እንደሚመስል ሳዕሊው ነበር። አቅም ስሌለው ወያኔ ብዕርን ፈርቶ ሃሳብን ሸሽቶ አሰረ። ኢትዮጵያን ሻማ አልባ አድርጎ ጭጋጋማ ጨለማ አለበሳት። ስለዚህ የእኛ ትግል ነገም የሃሳብ ብልጫ የሚመራት፤ የጠራ የሃስብ ጭማቂ የሚያስተዳድራት ሀገር ለመፍጠር ከሆነ፤ በዚህ ዙሪያ መጠራቅቁን ይፍታህ ማለት ያለብን ይመስለኛል። አራሳችን ለራሳችን ካሜራ መሆን አለብን።

አንቀጽ 20. ንዑስ አንቀጽ 2 አባልነት በፈቃደኝነትን ያከበረ ስለመሆኑ አበክሮ ያስገነዝባል። ስለሆነም ፈቅዶ የአንድ ፓርቲ አባል ለሚሆን፤ ወይንም ፈቅዶም ለማይሆኑ እኩል አክብሮትና የቤተሰባዊ ፍቅር የመስጠት እቅምን አምጠን መውለድ አለብን። ይህ ለዛሬ ብቻ አይደለም – ለነገም። ዛሬ ተሞርዶ ጎባጣውን ካላቃናነው ነገንም ያበልዘዋል።

ይህን ታላቅ „የወንጌል ቃል ያነገሠ“  ቀን ስናከብር ድንጋጌዎችን የዕለት ህይወታችን እንዲመሩት መፈቀዳችን እያረጋገጥን መሆን አለብን። በስተቀር አስክንድር – እስክንድር፤ የእኔ ሰው የእኔ ሰው፤ እርዮት እርዮት፤ በላይነሽ ባላይነሽ፤ አቡቦከር አቡበከር፤ በቀለ በቀለ፤ ውብሸት – ውብሸት ማለቱ ብቻውን ነገን አብርቶ አያመጣም። ስለዚህ ህጎችን ከወዲሁ ከእራስ ጋር አዋህዶ አክብሮቱን ድርጊት ላይ ለማዋል መትጋት ግድ ይለናል – እኛ እራሳችነን፤ እኛ ከዛ ቦታ ብንሆን በማለት ፈታኝ ነገሮችን ሁሉ ዛሬ መልክ ካላስያዝናቸው ነገ እዬመረቀዙ ለዛ መከረኛ ህዝብ ዕንባ ቀጣይነት ማዳበሬያ ይሆናሉ። ማሸነፍ የሚነሳው ከራስ ነው። ለሚወዱት ፍላጎት አራስ ነብር ሳይሆኑ እራስን ማሸነፍ ጀግነንት ነው - ደስታ ነው – ብሩህ ተስፋም ነው። የኔዎቹ ረጅም ጊዜ አቆዬኋችሁ – የግድ ስለነበር። አመሰግንኳችሁ። ትእግስታችሁን አደንቅኩኝ። መሸቢያ የሥራ ቀናት ከመጪው ሰንበት ጋር እንዲሆን ተመኘሁ – በአክብሮት። ደህና ሰንብቱልኝ።

ህግ የሚመራው ተናፋቂና ተወዳጅ ሥርዓት አምላካችን መርቆ ይስጠን!

ለህገ – ልቦና ነፍሳችን ይገዛ ዘንድ ልቦናችነን አምላካችን ይክፈት – ይርዳንም። አሜን!

ለእኔስ ሰው መሆኔ ብቻ ይበቃኛል።

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

Viewing all 1664 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>