Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » Opinion & Analysis
Viewing all 1664 articles
Browse latest View live

ኢህአዴግ ዳግም በክፍፍል ጎዳና?… (ከተመስገን ደሳለኝ)

$
0
0

ከተመስገን ደሳለኝ

ከዚህ ቀደም በተለያየ ጊዜ በተዘጋጁ ሁለት ፅሁፎች፣ የድህረ መለስን ኢህአዴግ የኃይል አሰላለፍ ለማመልከት መሞከሬ የሚታወስ ቢሆንም፤ ዛሬም ያልተጠበቁ ክስተቶችን ማስተዋላችን አልቀረም፡፡ በርግጥ «አዲሱ የኢህአዴግ አሰላለፍ ፪» በሚል ርዕስ ቀርቦ በነበረው ተጠየቅ ከሞላ ጎደል ሀገሪቷን እንደንጉስ ሚካኤል ከጀርባ ሆነው የሚያሽከረክሯት ህወሓት እና ብአዴን መሆናቸው የተጠቀሰበት አውድ ብዙም አልተቀየረም፡፡ ይሁንና በኦህዴድ እና ደኢህዴን ውስጥ እየታየ ያለው የእርስ በእርስ መተጋገል መደምደሚያ ምናልባት ወቅታዊውን መልከአ ኢህአዴግ ሊለውጠው የሚችልበት አጋጣሚ እንዳለ እገምታለሁ፤ ማን ያውቃል? …እነዚህን ኩነቶች ታሳቢ አድርገን የገዢው ፓርቲ አክራሞትን በአዲስ መስመር ጨርፎ ወደመመልከቱ እንለፍ፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ «ብላቴኖች»

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ክልሉን የሚያስተዳድረው የደኢህዴን የአመራር አባላት በስርዓቱ ልሂቃን የፖለቲካ ግምገማ ገና «ብላቴና» ተደርገው የሚወሰዱበት የትምክህት ዘመን አላከተመም፡፡ በርግጥ ድርጅቱ ደርግን ለመጣል በተደረገው የትጥቅ ትግል ላይ የተሳተፈ ባለመሆኑ፣ ዛሬም ፖለቲካን (ሀገር ማስተዳደርን) በበረሃው ትግል ተፈትኖ ከማለፍ ጋር ከሚያጋምዱት የግንባሩ ጉምቱ መሪዎች ዘንድ፣ ይህን መሰል ማጣጣያ የሚጠበቅ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ለደኢህዴን ደካማነት በምክንያትነት የሚነሳው ጉዳይ ከአወቃቀሩ ጋር የሚያያዝ ነው፤ ይኸውም በክልሉ የሚገኙ 56 የተለያዩ ዘውጎችን ማቀፉ ለመከፋፈል አደጋ በቀላሉ የሚጋለጥበትን ዕድል የማስፋቱ እውነታ ነው፡፡ ይህም ሆኖ ከክልሉ ነዋሪዎች በቁጥር የሚልቁት የወላይታና የሲዳማ ተወላጆች፣ በደኢህዴን ውስጥ ያላቸው ተሰሚነት (ተፅዕኖ) የገዘፈ መሆኑን ለመረዳት፣ ሕገ-መንግስቱ ከፀደቀበት ጊዜ ጀምሮ የፓርቲውን ሊቀ-መንበርነትም ሆነ የክልሉ ፕሬዚዳንትነት ከሁለቱ ብሔሮች በቀር፣ ለሌሎቹ የሰማይ ያህል የራቀ ያደረገውን «ዲሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት» መጥቀሱ በቂ ነው፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የፓርቲው ሊቀ-መንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ የያዘውን መንግስታዊ ስልጣን የሚመጥን ተሰሚነት ለማግኘት ድርጅታዊ ድጋፍ ማሰባሰብ ላይ ያተኮሩ የሚመስሉ ክስተቶችን ሲከውን ታዘብናል፡፡ ኩነቱን በስነ-አመክንዮ ለማጠናከር ጥቂት ማሳያዎችን ላቅርብ፡- በጠቅላይ ሚኒስትርነት መንበር ላይ ከተቀመጠ በኋላ፣ በደኢህዴን ውስጥ ያሉ የተወሰኑ ተገዳዳሪዎቹን ከኃላፊነታቸው ከማንሳትም አልፎ፣ ደጋፊዎቹ (ታማኞቹ) እንደሆኑ የሚነገርላቸውን በከፍተኛ ሥልጣን ላይ አስቀምጧል የሚያስብለው፣ ከወራት በፊት በፓርቲውም ሆነ በደቡብ ክልል ከእርሱም የበለጠ ተሰሚነት የነበረውን ሽፈራው ሽጉጤን አንስቶ፤ ትጉህ አገልጋዩ እንደሆነ የሚነገርለትን ደሴ ዳልጌን ተክቶታል፤ በቅርቡ ደግሞ ሌላኛው ‹የደኢህዴን ቁልፍ ሰው› የሚባለው የፖለቲካ (የድርጅት) ጉዳይ ኃላፊ እና የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አለማየሁ አሰፋን ያለአንዳች ኮሽታ «በትምህርት ስም» ከቦታው አንስቶታል (ይህ ጉዳይ እስከአሁን ድረስ መንግስታዊው ሚዲያ የዜና ሽፋን አላገኘም)፡፡ በግልባጩ ታማኝነታቸውን ያስመሰከሩ፣ ከሲዳማ ብሔር ውጪ ያሉ ጓዶቹን በፌደራል መንግስቱ ወሳኝ የስልጣን እርከኖች ላይ አስቀምጧል፡፡ ለማሳያ ያህልም አሰፋ አብዩ /ሀድያ/፣ ወርቅነህ ገበየውን ተክቶ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር፤ ደበበ አበራ /ከፋ/፣ የኢህአዴግ ዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ፤ ውዱ ሀቶ /ሸካ/፣ የፀረ ሙስና ምክትል ኮሚሽነር፤ አማኒኤል አብርሃም /ወላይታ/፣ በሚኒስቴር ዴኤታ ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሕዝብ አደረጃጀት አማካሪ፤ ሰለሞን ተስፋዬ /ጉራጌ/፣ በተመሳሳይ ማዕረግ የፕሬስ አማካሪ፤ ካይዛ ኬ (ጂንካ) በገቢዎች ባለስልጣን የገብረሀዋድን ቦታ ተክቶ የገባ እና የፌደራል ዋና ኦዲት መስሪያ ቤት ምክትል ኃላፊ ተደርጋ የተሾመችውን የወላይታዋ ተወላጅን መጥቀስ ይቻላል (ከደኢህዴን የሥራ-አስፈፃሚ አባላት መካከል የኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትሩ ሬድዋን ሁሴን እና መከላከያ ሚኒስትሩ ሲራጅ ፈጌሳም የሲዳማ ተወላጅ አለመሆናቸውን ልብ ይሏል) ይህንን ጉዳይ እንዲህ በብሔር ደረጃ ቁልቁል አውርደን እንድንመለከተው የሚያስገድደን ስርዓቱ ከሚያራምደው የፖለቲካ ፍልስፍና እና በክልሉ እየተነሱ ካሉ የማንነት ጥያቄዎች ጋር የመቆራኘቱ አንድምታ ነው፡፡ በተለይ

ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሲዳማዎች ራሳቸውን ችለው

በክልል ደረጃ ለመዋቀር ተደጋጋሚ ጥያቄ አቅርበው አያሌ መስዋዕትነትን መክፈላቸው ይታወሳል (በኢህአዴጋዊ የክልል አሰያየም ቀመር ሕገ-መንግስታዊ ድጋፍ ያላቸው መሆኑ ሳይዘነጋ)፡፡ ይሁንና ጥያቄው ተቀባይነት ቢያገኝ የክልሉ አስተዳደር መቀመጫ የሆነችውን አዋሳን ከመውሰዳቸውም በላይ፣ ሊያስከትል የሚችለው አለመረጋጋት ሲታከልበት፣ ህዳጣን ልሂቃኑን የኢኮኖሚ ጥቅመኝነት ያሳጣቸዋል፡፡ ይህ ስጋትም በደኢህዴን ውስጥ ከሲዳማ ተወላጆች ውጪ ካሉ የአመራር አባላት ድርጅታዊ ድጋፍ ለማግኘት ብርቱ ትግል ከሚያደርገው ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር በወሳኝ ሰዓት፣ መሀል መንገድ ላይ ቢያስተቃቅፋቸው የማይታመን አይሆንም፡፡

eprdfየእነዚህ አዳዲስ ኩነቶች (ሹም ሽሮች) መግፍኤ፣ በሁለት የቢሆን ሃሳቦች ተነጣጥለው ሊታዩ ይችላሉ፡፡ የመጀመሪያው ኃይለማሪያም ደሳለኝ የጠቅላይ ሚንስትርነት ሹመቱን ተከትሎ ‹በዚህ ላይ ፈርም›፣ ‹ይህንን ተናገር›፣ ‹እንዲህ አይነት አስተያየት ስጥ!!› ወዘተ የሚሉ ከጀርባ ሆነው የሚሾፍሩት የአለቆቹ ቀጭን ትዕዛዛትን የሚገዳደርበት ፖለቲካዊ ጉልበት ለማሰባሰብ እና በቁርጥራጭ ጨርቅ በተጣጣፈው እናት ድርጅቱ ውስጥ ያሉ ችግሮችን ስልታዊ በሆነ መልኩ አስወግዶ ቅቡልነቱን ለማጠናከር እንቅስቃሴ ጀምሯል የሚል ሊሆን ይችላል፡፡
ሌላኛው ደግሞ ከኢትዮጵያውያንም አልፎ በውጪ ዜጎች ሳይቀር ‹ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሻንጉሊት ነው› የሚለውን እምነት ለማስቀየር በህወሓትና ብአዴን እየተደረገ ያለ ፖለቲካዊ ጨዋታ ሊሆን የመቻሉ ጉዳይ ነው፡፡

ኦህዴድ

ባለፉት የህወሓትም ሆነ የአቶ መለስ ዜናዊ የበላይነት በገነኑባቸው ዘመናት፣ ኦህዴድ ምንም እንኳን ስርዓቱን ካነበሩ የግንባሩ አባል ድርጅቶች አንዱ መሆኑ ባይካድም፣ በስጋት መታየቱ የአደባባይ እውነታ ነው፡፡ እንዲያውም በአንድ ወቅት አቶ መለስ ራሱ «ኦህዴድ ሲፋቅ ኦነግ ነው» ማለቱ አይዘነጋም፡፡ ከሶስት ያላነሱ የስራ አስፈጻሚ አባላቱ፣ ድርጅቱን ከድተው ኦነግን መቀላቀላቸውም የውንጀላው ማሳያ ተደርጎ እስከመወሰድ ደርሶ ነበር፡፡ ይህ ሁኔታም ኦህዴድን የተረጋጋ አመራር እንዳይኖረው ከማደናቀፉም ባሻገር፣ በተቀነባበረ ማኪያቬሊያዊ ሴራ እርስ በርስ በማይተማመኑና በተከፋፈሉ ሰዎች ስር እንዲቆይ አስገድዶታል፡፡ ግና፣ ኩነቱን ምፀት የሚያደርገው ህወሓት በረሃ እያለ ያሳትመው በነበረው ልሳኑ «የኦሮሞ ጥያቄና የኢትዮጵያ አብዮት» በሚል ርዕስ ባሰራጨው ፅሁፍ ኢህአፓን «የኦሮሞ ሕዝብ በነፍጠኛው ላይ የነበረውን ተገቢ ጥላቻ በማራገብ ፋንታ ለማብረድ በተጨባጭ ተንቀሳቅሷል» («የትግል ጥሪ» 3ኛ ዓመት ቁጥር 10፣ 1979 ዓ.ም) ሲል ይከስሰው እንደነበረ ማስተዋላችን ነው፡፡

በአናቱም አቶ መለስ እስከ ህልፈቱ ድረስ በኦህዴድ ደስተኛ እንዳልነበረ ይነገራል፡፡ ይህ ግን ‹የኦሮሞን ሕዝብ በአግባቡ አላገለገለም› ከሚል ቁርቆራ የተነሳ አይደለም፤ እንዲህ አይነቱ ስሜት ሌላውን ክልል ቀርቶ ትግራይንም የሚመለከት ቢሆን አሳስቦት አያውቅምና፡፡ የእርሱ ቅሬታ ‹ህዝቡን አሳምነውም ሆነ ጠርንፈው ከድርጅቱ ጎን አላሰለፉትም›፣ ‹ሁላችንንም በሚያሳጣ መልኩ ዘረፋ ውስጥ ገብተዋል›፣ ‹ዲሲፕሊን የላቸውም…› የሚሉና ሌሎች መሰል መነሾዎች ናቸው፡፡ እንዲህ ያለ የድርጅቱ «እንዝህላልነት» ደግሞ የህዝቡ ልብ ይበልጥ ኦነግን እንዲናፍቅ ማስገደዱን መለስ ዜናዊ ጠንቅቆ ያውቅ ነበር፡፡ ለዚህም ይመስለኛል የክልሉን ባለስልጣናት ሁሉ ወደ ጎን ብሎ እታች ድረስ በመውረድ የወረዳ አመራሮችን ቀጥታ ያለ ሥልጣን ተዋረድ በስልክ እስከማናገር የተገደደባቸው ቀናት የበዙት፡፡ በርግጥ በድርጅቱ ስብሰባዎች ላይ መተላለፍ ያለባቸውን ውሳኔዎች በፅሁፍ መስጠት እና ለአመራርነት የሚመረጡ ሰዎችን መመደብ ድረስ ባሉ ጉዳዮች ጣልቃ የመግባቱ ነገር ማንም አሌ የማይለው በግልፅ ይታይ የነበረ ክስተት ነው፡፡

የሆነው ሆኖ ከምንጮቼ እንዳረጋገጥኩት አባዱላ ገመዳ ዕድሜውን ሙሉ ሲፈራ የኖረው መለስ ዜናዊን ብቻ ነበር፤ መለስ ደግሞ ይህችን ምድር ለመጨረሻ ጊዜ ከተሰናበታት አንስቶ የተቆጠሩት በርካታ ወራት ፍርሃቱን ጥሎ ነፃነቱን እንዲጎናፀፍ ለመርዳት ያስችሉታል ብዬ አስባለሁ፡፡ እናም በዚህ መልኩ ተፈጥሮ ያመቻቸለትን ታሪካዊ አጋጣሚ ተጠቅሞ ይደቆስ የነበረውን ኦህዴድ ከወደቀበት ለማንሳት ሙከራዎችን እያደረገ ይመስለኛል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኦህዴድ በሚያደርጋቸው ስብሰባዎች ላይ የሚቀርቡ አንዳንድ አጀንዳዎችና አቋሞችን የአባዱላ ግፊት እንዳለባቸው ስናስተውል፣ «ጄነራሉ» ወሳኝ ሰው ለመሆን እያደረገ ያለው የጥንጣን ጉዞ ምን ያህል እየሰመረለት እንደሆነ ለመረዳት ያስችላል፡፡ ይህንን መከራከሪያ ከለጠጥነው ደግሞ፣ ከህወሓት/ብአዴን ጋር ትከሻ መገፋፋት ጀምሯል ወደሚል ጠርዝ ይገፋናል፡፡ ይህም ባይሆን እንኳ ከኃይለማርያም ደሳለኝ የተሻለ ተሰሚነት እንዳለው ለመናገር የሚያስደፍሩ ማስረገጫዎች አሉ፡፡ ጠቅላይ ሚንስትሩ ቀን የከዳ ዕለት በተናጠል በኃላፊነት ሊያስጠይቁት የሚችሉ ጉዳዮችን ሳይቀር፣ በያዘው ሕገ-መንግስታዊ ሥልጣን ከመወሰን ይልቅ በቡድን እንዲያልቅ ሲስማማ፤ በግልባጩ አፈ-ጉባኤው ከዚህ ቀደም በምክር ቤቱ ውስጥ ተነስተው ለአቶ መለስ ይቀርቡ የነበሩ ጉዳዮችን ወዲያውኑ መፍትሔ እንዲያገኙ በማድረግ ሲቋጫቸው ተደጋግሞ ተስተውሏል፡፡ ኦህዴድንም በሚመለከት ‹በድርጅታዊ መደጋገፍ› ስም ማንም ጣልቃ መግባት እንደማይችል በይፋ እስከ መናገር መድረሱን ምንጮች ጠቅሰውልኛል፡፡ በቀጣይ አመት የሚደረገውን አምስተኛ ዙር አገር አቀፍ ምርጫን አስመልክቶም እየተደረገ ባለው ዝግጅት በሃሳብ አመንጭነት እየተሳተፈ ነው፡፡ ከጥቂት ወራት በፊት ለምክር ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ ከሁሉም የመንግስት መስሪያ ቤት ለተወከሉ እና ምርጫ ቦርድ ሀላፊዎች /ፕሮፌሰር መርጋ በቃና እና ዶ/ር አዲሱ ገ/እግዚአብሔር በተገኙበት/ «የአውራ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ባህሪያት» በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፍ ማቅረቡ አስረጅ ሆኖ ሊወሰድ ይችላል (በነገራችን ላይ ስርዓቱ በምርጫ ስም የሚፈፅመውን ደባ ፍንትው አድርጎ የሚያሳየው፣ ሁለቱ የቦርዱ ኃላፊዎች የዚህ አይነቱ ውይይት ላይ ተሳታፊ መሆናቸው ነው)፡፡ እንዲሁም ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ በአዳማ ለክልል አፈ-ጉባኤዎች ሰፊ ትንተና ሰጥቷል፡፡

የአባዱላ ገመዳንና የበረከት ስምኦንን መገፋፋት በጨረፍታም ቢሆን ሊያሳይ የሚችለው ሌላኛው ሁነት ደግሞ ወ/ሮ አና ጎሜዝን አስመልክቶ ሊነሳ የሚችለው ነው፡፡ በረከት «የሁለት ምርጫዎች ወግ» በሚለው መጽሐፉ «የቅኝ-ገዥነት መንፈስ ያልለቀቃት» ብሎ የገለፃትን አና ጎሜዝ (የመለስ በስድብ የተሞላ የኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጣ መጣጥፍ ሳይዘነጋ)፣ ከሁለት ወራት በፊት አዲስ አበባ

በመጣችበት ወቅት አባዱላ በጓዳዊ ስሜት እንዳስተናገዳት ራሷ ከመመስከሯም በዘለለ፣ እነርሱም በአዲስ ዘመን ጋዜጣቸው «እየተመካከርን ነው» የሚል የወዳጅነት መንፈስ የረበበበት የፎቶ ዘገባ ማቅረባቸውን እናስታውሳለን፡፡ ይህች ተራ የምትመስል ሁነት ለበረከት የምታስተላልፈው መልዕክት ቢኖር ‹እናንተ እንደሰይጣን የረገማችሁትን ሁሉ እየተከተልን አንረግምም» የምትል እኩዮች ነን አይነት ትከሻ መጋፋት ትመስለኛለች፡፡

በአናቱም አባዱላ አብዛኛው የኦህዴድ አመራርን በዙሪያው ማሰባሰብ ስለመቻሉ ይነገራል፡፡ ከዚህ ቀደም በአደባባይ እስከመዘላለፍ የተደራረሱትን አቶ ሙክታር ከድርንም ከጎኑ ማሰለፍ ችሏል፡፡ በአንድ ወቅት የግል ጠባቂው የነበረውና አሁን የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የሆነው አብይ አህመድ በእንዲህ አይነቱ ጊዜ ውለታ ለመመለስ የሚያደርገው ተጋድሎ የማይናቅ ጠቀሜታ አስገኝቶለታል፡፡ የሰሞኑ ሹም ሽርም የራሱ የሆነ አንድምታ አለው፡፡ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ በማዕከላዊ ኮሚቴ ድምጽ ከስልጣኑ የተሻረው የክልሉ ፕሬዚዳንት አለማየሁ አቱምሳ (እርሱን ማንሳት የሚችለው ጠቅላላ ጉባኤው ብቻ መሆኑን ልብ ይሏል፡፡ በርግጥ ሰውየው አሁን አልፏልና በባህላዊ ልማዳችን መሰረት ነፍስ ይማር ብለን እናልፋለን) በ2002ቱ ምርጫ ማግስት አቶ መለስ ከካድሬዎቹ ይሁንታ ውጪ አባዱላን ለመተካት ያመጣው እንደነበር ይታወሳል፡፡ (በነገራችን ላይ በወራት እድሜ ውስጥ በመለስ የተሾሙ የክልል ፕሬዚዳንቶች ከኃላፊነታቸው ሲነሱ ከሽፈራው ሽጉጤ እና አያሌው ጎበዜ ቀጥሎ አለማየሁ አቱምሳ ሶስተኛው ሰው መሆኑ ነው) የድርጅቱ ሊቀ-መንበር እና ምክትል ሆነው የተመረጡት ሙክታር ከድርና አስቴር ማሞም የአባዱላን የበላይነት ለመቀበል ግለ- ሂሳቸውን ውጠዋል፡፡ ይህም ሆኖ የክልሉ አስተዳዳሪ ማን ይሆናል? የሚለው ጥያቄ ገና መልስ አላገኘም፡፡ ምናልባት (ከስራ አስፈፃሚዎችም መካከል መምረጥ እንደሚቻል ታሳቢ ተደርጎ) በሌሎች አካባቢዎች እንደታየው ከድርጅቱ ሊቀ-መናብርት (ሙክታርና አስቴር) አንዳቸውን መሾም ቢፈልጉ እንኳ ዕውን የሚሆንበት ዕድል የለም፡፡ ምክንያቱም እነርሱ የህዝብ ተወካዮች እንጂ የጨፌ ኦሮሚያ ም/ቤት አባል አይደሉምና፡፡ በእኔ ግምት እስከሚቀጥለው የምርጫ ዘመን ድረስ ቦታው አዲስ ሰው ሳይሰየምበት በምክትል ፕሬዚዳንቱ አብዱል አዚዝ ስር እንዳለ የሚቆይ ይመስለኛል፡፡

ከምርጫው በኋላስ? ….አፈ-ጉባኤው በኦህዴድ ውስጥ ለማስፈን እየሞከረ ካለው «አምልኮ አባዱላ» ተነስተን «ተገፈተርኩበት!» የሚለውን ያደረ ቁጭቱን ስንደምርበት ወንበሩን ራሱ ይይዘው ይሆናል ከሚል ጠርዝ ያደርሰናል፤ አሊያም ከሽርኮቹ ሙክታር ከድር እና ወርቅነህ ገበየው አንዳቸውን አሾሞበት በጨፌ ኦሮሚያም የሚካኤል ስሁልን መንፈስ ማንበሩ አይቀርም ብሎ ቅድመ ግምት ማስቀመጥ ይቻላል (ይህ መላምት የህወሓት-ብአዴን ጥንካሬ በዚሁ ከቀጠለ እና የእነርሱ ፍላጎት ደግሞ የተለየ ከሆነ ከህልም ሊዘል አለመቻሉን በማመን ላይ የተመሰረተ ነው)

ኦህዴድን ካነሳን የሌንጮ ለታን ኦዴግን መፃኢ እድልም መመልከት ግድ ይለናል፤ ምክንያቱም ኦዴግ አገር ውስጥ ገብቶ በሰላማዊ መንገድ መታገል ወስኖ ጨርሷልና፤ ሂደቱንም ለማመቻቸት ከግንባሩ መሪዎች አቦ ሌንጮ ለታ፣ ዶ/ር ሌንጮ ባቲ፣ ዶ/ር ዲማ ነጎዎ፣ ዶ/ር ታደሰ ኤባ እና ዶ/ር በየነ አሰቦ ጋር ከስምምነት ለመድረስ፣ ኢህአዴግ በውጪ ሀገር ከሚገኙት የጄኔራል ታደሰ ብሩ ልጆች በተጨማሪ፣ ፕ/ር እንድሪያስ እሸቴ፣ ፕ/ር ኤፍሬም ይስሃቅ፣ ፓስተር ዳንኤል፣ ሻለቃ ኃይሌ ገ/ስላሴ፣ ሻለቃ ደራርቱ ቱሉ፣ አባቢያ አባጆቢር፣ አቶ በቀለ ነዲ (የአዋሽ ባንክ የቦርድ ሰብሳቢ የነበሩ)፣ ወ/ሮ ሙሉ ሰለሞንን የመሳሰሉ አደራዳሪዎችን ማሳተፉ ይነገራል፡፡

ይህም ሆኖ ድርድሩ በስኬት ተቋጭቶ ኦዴግ ሀገር ቤት መግባት ቢችል እንኳ፣ ኦህዴዶች ‹አያሰጋንም› የሚል እምነት እንዳላቸው ሰምቻለሁ፡፡ ግና፣ ያለፉት ሁለት አስርታት ዘግናኝ ክስተቶች አሻራ ዛሬም በረዣዥሞቹ የባሌ ተራሮች በጉልህ ተቸክችኮ የመታየቱ እውነታ፣ በስርዓቱ ላኮረፈው የኦሮሚያ ህዝብ፣ ኦዴግን አማራጭ የሚያደርግበት «አኪር» ሸሽጎ ይዞ እንደሆነ ማን ያውቃል? ይህ እንግዲህ እነ ሌንጮ «ካዳሚ» ለመሆን አይመጡም በሚል ስሌት ከተቃኘ ነው፡፡ ይሁንና ከድርድሩ ጀርባ ያለውን እንቆቅልሽ ለመፍታት ጊዜ የሚጠይቅ ቢሆንም፣ ጉዳዩን ውስብስብ የሚያደርጉ ክስተቶችን ግን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ይኸውም በአፈ-ጉባኤ አባዱላ ፊት አውራሪነት ስር ለመጠናከር እየሞከረ ያለው ኦህዴድ፣ ከሰዎቹ ሀገር ቤት መግባት ምን ያተርፋል? ምንስ ያጣል? ከሚለው ጋር ይያያዛል፡፡

መቼም የኦዴግን መምጣት፣ ኦቦ ሌንጮ «እንጮቴ» (ተወዳጅ ባሕላዊ ምግብ ነው) በአይኑ ላይ እየተመላለሰ እንደሆነ ከሰነዘረው ቀልድም ሆነ «ከሌሎች የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ዘመናዊ ፌደራሊዝምን እመሰርታለሁ» ብሎ በደምሳሳው ከገለፀው ዓላማው ጋር አያይዞ ማለፍ አይቻልም፡፡ አሊያም ያኔ እርሱ ሸገርን ተሰናብቶ ሲወጣ ገና ያልፀደቀውን አንቀፅ 39ን «አስፈፅማለሁ» በሚል ቀቢፀ-ተስፋ ተገፍቶ ነው ማለትም አይቻልም፡፡ በግልባጩ አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች ‹የኦዴግ መሪዎች በኦነግ ዘመን ለእስር የዳረጓቸውን በሺ የሚቆጠሩ የኦሮሚያ ተወላጆችን ለማስፈታት ሲሉ፣ በታማኝ ተቃዋሚነት ለመታገል ወስነው ነው የሚመጡት› የሚለውን መከራከሪያቸውን ለመቀበል የሚቸግረው ደግሞ፣ እስረኞቹን መፍታት ለሃያ አመታት ያህል በክልሉ ላይ ሰላማዊ ዜጎችን በማሰር የሚታወቀውን ኦህዴድን ሊያሳጣ የመቻሉ ነገር ነው፡፡ ያም ተባለ ያ፣ «ለሁሉም ጊዜ አለው» እንዲል ጠቢቡ
tplf-rotten-apple-245x300
ሰለሞን ሁሉም ቋጠሮ ጊዜ የሚፈታው ይሆናል፡፡ አሁን ላይ እርግጠኛ መሆን የሚቻለው በኦህዴድ ውስጥ አባዱላ ገመዳ ወሳኝ እየሆነ የመምጣቱ እውነታ ብቻ ነው፡፡

ህወሓት-ብአዴን

በዋናነት ሀገሪቷን እንደሚያሽከረክሯት የሚነገርላቸው ህወሓት እና ብአዴን፣ በመጪዎቹ ጊዜያት ‹ኢህአዴግ ለዳግም ክፍፍል ሊዳረግ ይችላል› በሚል ፍርሃት ድርና ማግ ሆነው እየሰሩ ስለመሆኑ እየሰማን ነው፡፡ በርግጥ ‹መለስ ህወሓትን አዳክሞ ነው ያለፈው› የሚል የትግርኛ ተናጋሪዎች ድምፅ መሰማት ከጀመረ ሰነባብቷል (በነገራችን ላይ ከ2000 ዓ.ም ወዲህ የህወሓትን የምስረታ በዓል የካቲት 11ን በብሔራዊ ደረጃ ማክበር መቅረቱን በይፋ ከማወጃቸውም በላይ፣ መለስ ራሱ ለመጨረሻ ጊዜ በመቀሌው የሰማዕታት አዳራሽ የተገኘው 35ኛው ዓመት በተከበረበት ወቅት ነበር፡፡ ይሁንና ከህልፈቱ በኋላ ድርጅቱ የደረሰበትን ድክመት ለመሸፋፈን በደመቀ መልኩ እያከበረው ይገኛል፤ ለዚህም ይመስለኛል በአምናውም ሆነ በዘንድሮው በዓል ላይ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ መቀሌ የሞቀ ተገኝቶ ንግግር ከማድረግም አልፎ ከሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኡመር ሀሰን አልበሽር ጋር በትግሉ ዘመን በተቀነቀኑ ዜማዎች ሲደንስ በቴሌቪዥን መስኮት ተመልክተን ሦስተኛው ሚሊንየም ገባ እንዴ? ብለን ግራ የተጋባነው፡፡ አልበሽርስ አንድ ቻርተር አውሮፕላን ለክልሉ በስጦታ ያበረከተው ዕውን በዓሉን አስመልክቶ ነው? ወይስ በምትኩ የተሰጠው ነገር ኖሮ? መቼም የህወሓት የምስረታ በዓል እንዲህ ሊያስፈነጥዘው እይችልም)

deberestion‹ህወሓት ተዳክሟል› የሚለውን ቅሬታ የሚያሰሙ የቅርብ ሰዎች፣ ድርጅቱ አቅምና ልምድ በሌላቸው መሪዎች ስር ማደሩን ይጠቅሳሉ፡፡ ተስፋ የጣሉበት ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልም ቢሆን ከአምባገነንነቱም በላይ ሀሳቡን አፍታቶ የማስረዳት ችሎታው ደካማ መሆን መፍትሄውን አርቆ ሰቅሎታል፡፡ እንደ ድርጅቱ የቅርብ ሰዎች አገላለፅ የ«ጠንካራ ተተኪ» አልቦነትን ለመረዳት፣ በቅርቡ ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ኃላፊነቱ በተነሳው አቶ ዘርዓይ አስገዶም ቦታ ላይ የዋልታ ስራ አስኪያጅ መመደቡ እና ራሱ ዘርዓይም በጓሮ በር የብሮድካስት ባለስልጣን ሆኖ መሾሙን (አዲስ ፊት አለመታየቱን) መመልከቱ በቂ ነው፡፡ በቅርቡ የዶክትሬት ዲግሪውን ያገኘው አርከበ እቁባይም ለአመራርነት ለቀረበለት ጥያቄ እያንገራገረ እንደሆነ ተሰምቷል፤ አቦይ ስብሃት ነጋም ኢ-መደበኛ በሆነ የጠረጴዛ ወግ ህወሓት «በግብር በላ» መሪዎች እጅ መውደቁን በቁጭት መናገራቸው ይጠቀሳል፡፡ ይሁንና በዚህ ቀውጢ ወቅት ሁለት ተቋማት ድርጅቱን ለጊዜውም ቢሆን ፖለቲካዊ ጉልበቱን እንዳይነጠቅ ታድገውታል፡፡ ደህንነቱ እና ሰራዊቱ፡፡

የሆነው ሆኖ ህወሓት ዛሬም ከብአዴን ጋር በማበር (በአባይ ፀሐዬ እና በበረከት ስምኦን የፊት መሪነት) የፖለቲካው አሽከርካሪነቱን እንዳስከበረ ይገኛል፡፡ ሁለቱ ሰዎች የስርዓቱን ርዕዮተ-ዓለምንም (በተለይም አብዮታዊ ዲሞክራሲን) ከሌሎች ጓዶቻቸው በበለጠ ማብራራት እንደሚችሉ ይነገራል፡፡ በጅጅጋ ከተማ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በተከበረበት ወቅትም ሆነ ከሳምንታት በፊት በመቀሌ ከተማ በተዘጋጀ መድረክ አባይ ፀሐዬ የርዕዮተ-አለሙ «ተንታኝ» ሆኖ የቀረበው ከዚህ አኳያ ነበር፡፡ በአናቱም አባይ እና በረከትን ጨምሮ ከኦህዴድ ኩማ ደመቅሳ፤ ከደኢህዴን ዶ/ር ካሱ ኢላላ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር አማካሪ ሆነው መሾማቸው ይታወሳል፡፡ በዋናነት ለኢህአዴግ የስልጣኑ መሰረት (ከታጠቀው ኃይል እና ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬው በተጨማሪ) ‹በልማታዊ መንግስት፣ በጥርነፋ፣ ሳር-ቅጠሉን በማደራጀት፣ የብሔር ጉዳይን በማጎን እና መሰል ጭብጦችን በማስጮኽ የሚያምታታበት ርዕዮተ-ዓለሙ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ የእነ በረከት የተሰሚነት ምስጢርም ከዚሁ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በርግጥም የካቲት 14 ቀን 2006 ዓ.ም. የተሰበሰበው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከልን ለማቋቋም የሚያስችል ደንብ ማፅደቁን እና የአራቱም ድርጅት የአመራር አባላት የተወከሉበት ከመሆኑ አኳያ፣ ቦታው ከማማከር የዘለለ የስራ ድርሻ እንዳለው መገመት አያዳግትም (በነገራችን ላይ የመለስ ፖለቲካ ሰለባ የሆነው የብአዴኑ ተፈራ ዋልዋ ድምፁን አጥፍቶና ከውጥንቅጡ አርባ ክንድ እርቆ በእንጦጦ ተራራ እና በረዣዥም ህንፃዎች አናት በመፈናጠጥ ቴሌስኮፑን ግራና ቀኝ እያዟዟረ ከዋክብት ሲመለከት መዋልን አይነት ፀጥተኛ ህይወት፣ አንዳንድ የቀድሞ ጓዶቹም ለተረፈቻቸው እድሜ የሚመኙት ይመስለኛል)

ለውጥ ይኖር ይሆን?

የስርዓቱ ልሂቃን ብሔሮቻቸውን ማዕከል ባደረገ መልኩም ይሁን፣ በሥልጣን ከፍታ ከሚያገኙት ግላዊ ጥቅማ-ጥቅም በመነሳት፣ ከላይ ለመተንተን እንደሞከርኩት ባለ የመከፋፈል መሰል ሂደት ውስጥ እንኳን ቢያልፉ በቀጣይ ጊዜያት ‹የፖለቲካ ማሻሻያ ያደርጋሉ› ብሎ ለማመን ነገሮች በእጅጉ አስቸጋሪ ናቸው፡፡ ለዚህም ሶስት ነጥቦችን እናንሳ፡- የመጀመሪያው የሀገሪቱ የደህንነት መዋቅር አደረጃጀት ባህሪ ነው፡፡ እንደሚታወቀው በእነ ጌታቸው አሰፋ የሚመራው የደህንነት ተቋም በሚታዩና በማይታዩ ድርጊቶች ለህወሓት የተገዛ ነው፡፡
ከዚህች ሀገር ጀርባ ለተፈፀሙም ሆነ ገና ለሚፈፀሙ ድርጅታዊ እና ግለሰባዊ (ባለሥልጣናዊ) ወንጀሎች አስፈፃሚና በደል አንፂ ነው፡፡


ዉርደት በጩኸት ብዛት ክብር አይሆንም

$
0
0

ባንድ ወቅት የቀዲሞ የኢትዮጵያ አየር ወለዶች ግዳጅ ተሰቶዋቸው በተሰማሩበት ዉጊያ ከባድ ድካም ዉስጥ በመግባታቸው የመፍረክረክ ሁነታ ይታያል በዚህን ጊዜ የብርጌዱ አዛዥ ኮሎነል ግሩም አበበ የምን መፍረክረክ ነዉ፣ አየር ወለድ ግንባሩን እንጂ ጀርባዉን አይመታም፣ በሉ ተከተሉኝ ብሎ ሳንጃዉን ወድሮ የጅቦምቡን ቅርቃር ነቅሎ ወደፊት ተንደረደረ። ሰራዊቱም ተከተለዉ ለሰዓታት ከምሽግ ምሽግ አይዘለለ ስዋጋ እና ሲያዋጋ ጦሩም በጠላት ላይ አያየለ መጣ፤ ከተወሰኑ አርሚጃወች በሖላ ኮሎኔል ግሩም ከፍጥነቱ አየቀነሰ በጉልበቱ በርከክ አለ፣ ወዲያዉም በሙሉ ሰዉነቱ መሬት ላይ አረፍ አለ። ከወዲወድያ እየተሯሯጡ ይዋጉ የነበሩ ኮማንዶች እንደገና ኮሎኔሉ አጠገብ መሰባሰብ ሲጀምሩ፣ እኔ ደሕና ነኝ ዉጊያዉን ቀጥሉ ብሎ ጋደም አለ። የተወሰኑ ወታደሮች ደግፈዉ አንዲት ዛፍ አስደግፈዉት በእልህ ወደ ዉጊያዉ ሮጡ። የመሰላቸዉ ላለፉት አርባ ስምንት ሰዓታት ምግብ ስላልቀመሰ ደክሞት ይሆናል ብለዉ ነበር። ከሰአታት አስቸጋሪ ትንቅንቅ በሖዋላ ጠላትን ደምስሰዉ ፩፮ኛ ሰንጥቅ መከናይዝድን ከከበባዉ በማዳን የተሰጣቸዉን ቦታ ከተቆጣጠሩ በሆዋላ በድል ወደ ኮሎኔል ግሩም በመሮጥ ድሉን ለማብሰር ስመጡ፣ ኮሎኔል ግሩም አበበ የ፭ኛ አየር ወለድ ብርጌድ ኣዛዥ ቅድም አንደተራ ወታደር በየሚሽጉ አይዘለለ ስዋጋ ተመቶ ኖሮአል ግራ ጎኑ በደም ርሶ የጦርነቱን መጠረሻ ሳያይ፣ ልጆቼን፣ በተሰቤን፣ ሳይል ለአገሩ ሲል አንዲት ሂይወቱን በመስጠት ለዘላለሙ አንቀላፍቶ አገኙት ።(የጦር ሜዳ ዉሎን ያንብቡ)

ኢትዮጵያ ብዙ ግሩሞች ነበሩዋት። ከነሱ ኣልፎ ለሌላዉ የምተርፍ ብዙ እዉቀት ብዙ ነገር እያላቸዉ ብቸኛ ህይወታቸዉን ለአገራቸዉ ክብር የሰጡ፤ ለነብሳቸዉ ሳይሳሱ የማይቻል የመሰለ መስዋእትነት የከፈሉ፣ ከዉርደት ይልቅ በክብር መሞትን የመረጡ። ኢትዮጵያ በጣም ብዙ ግሩሞች ነበሩዋት ከምንዳ ከገንዘብ ከትራፊና ከፍሪፋሪ ይልቅ ስለኣገራቸዉ መራብን የመረጡ። ኢትዮጵያ ብዙ ግሩሞች ነበሩዋት በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የሚያስገኝ አውቀታቸዉን ለሚስኪኑ ህዝባቸዉ ሲሉ ንቀዉ በድህነት ኖረዉ በድህነት የሞቱ። ኢትዮጵያ ዛሬም ብዙ ግሩሞች አሉዋት ገድላቸዉ አንድ ቀን የሚወራላቸዉ፣ እነ አስኪንድሮች፣ እነአንዱአለሞች፣ እነርዮቶች፣ እነበቀለወች፣ እነኦልባናወች፣ እነናትናኤሎች፣ እነዉብሸቶች፣እነ እነ እነ እነ እነ ብዙ ብዙዎች።
ኢትዮጵያ ለሎችም አሉዋት ሆድ አምላካቸዉ፣ ዉርደት ክብራቸዉ፣ ክሂደት ዝናቸዉ፣ ዉሸት እዉቀታቸዉ፣ ባርነት ስብዕናቸዉ፣ እነብርሃኑ ዳምጤወች (ኣባመላ የሚለዉ ስም ሰልማይመጥነዉ ነዉ)።
ዉርደት በጩኸት ብዛት ክብር ላይሆን ኢትዮጵያ ብዙ ከርሳሞች ሞልተዋታል የተደገሰ ቦታ የማይጠፉ በልተዉ የማይሄዱ አንደዉሻ ካልጮሁ ።ከጢቂት ወራቶች በፍት በሳኡዲ አረቢያ ኢትዮጵያዊያኖች ሲታረዱ ብዙሆች ጮኸዉ ነበር አብዛኛዉ ኢትዮጵያዊ ከጢቂት ከርስ አደሮች ጋር ሆነዉ። ዛሬ ከርስ አደሮቹ ከርሳቸዉን ወደ ሚሞሉበት ሲመልሱ አሁንም ኢንጮሃለን ከዱን ብለን። የሳኡዲ ጥቃት ሲያበሳጨን ጮኸን ፣ሆድ አደሮች ሲከዱንም ጮኸን አንችልም፣ ነብሰገዳዮች አገራችንን ሲበታትኑ ጮኸን ለዉጥ አላመጣንም፣ ቅርሳችን መለያችን ለባዳዎች ሲሳይ ሲሆን ጮኸን ጠብ ያለልን ነገር የለም። በጩኸት ብዛት ለነሆድ አደሮች ክብር እንደማይመጣ ሁሉ ለተቀረነዉም የነሱ አይነት ጩኸት ነጻነት አይሰጠንም። ነጻ የሚያወጣን እንደነ ግሩም አበበ ደም መክፈል ስንችል ብቻ ነዉ።ነጻ የሚንወጣዉ በአመንንበት ነገር ላይ ጸንተን መቆም ስንችል ብቻ ነዉ። የታላቁን ኢትዮጵያዊ የዓባመላን ስም ቅጥሉ አንዳደረገዉ አሳማ ወደነፈሰበት ብንዘም ውርደትን አንደ አካላችን ከማየት ያለፈ ነገር አይኖረንም፣ እንደ ኮሎኔል ግሩም ስንጸና ቢያንስ ሞታችን እንኩዋን በኩራት ዘንተ አለም ይነገራል። ሳኡዲወች አዋረዱን ብለን ስንጮህ የነበርነዉ በስተት ነበር ምክኒያቱም አራሳችንን ያዋረድነዉ አራሳችን መሆናችንን ስላልተረዳን። ብዙሺ ግሩሞች ጠዉልገዉ ያቆዩአትን አገራችይንን ለእነ አባአተላ ፣ለነ አባባንዳ፣ ለነ አባሆድ አምላክ፣አሳልፈን ሰተን ስደትን አንደመፍትሔ ቆጠርን በተሰደድንበትም ቢሆን ከነሱ መለየትን ባለመድፈር እራሳችንን አዋርደን ተዋረድን ኢንጂ በምንም መንገድ ሰኡዲወች አላዋረዱንም።
በምንም መንገድ አረቦች አላዋረዱንም ስብእናችንን አሳሞች ሲረጋግጡት መከላከል የተዉን፣ ከመሰሪዎች ጋር የተቆራኘን ጢቂቶች የተሻለ አማራጭ እያላቸዉ በሞታቸዉ ያስረከቡንን ነጻነት ዋጋ ያቃለልን እራሳችን እንጂ። በምንም መንገድ እራሳችንን ያዋረደን እኛዉ ነን፣ የእምቢ ጽናታችንን ከዉስጣችን አዉልቀን የጣልን፣ ከሃሰተኞች ጋር ቤተክርስቲያን የምናጣብብ፣ከአረመኔዎች ጋር መስግድ የሞላን ለእዉነት ካልቆሙ ለሃሰት ከምጸልዩ ጋር የተባበርን።አባቶቻችን ደም ከፍለዉ ያቆዩትን ነጻነት በፍርፋሪ ከሸጡ የሉኝንታ ካልፈጠረባቸዉ ከሃዲዎች ጋር እስከቆምን ድረስ እኛም ነጻነታችንን ለዘላለሙ እናጣዉ እንድሁ አንጂ መልሰን አናገኘዉም። መለየት የሚባልን ድፍረት የግድ መልመድ ካልተቻለ ዛሬም ነገም ብዙ ለሆዳችዉ ያደሩ ስያስጮሁን መኖራችን የማይቀር ነዉ። ጣይቱ በበቀለችበት ምድር ሊጁዋን እንዝርት ከማስያዝ ፋንታ ለዚሙት የምታሰማራን፣ ስብዕና በጎደላቸዉ አረቦች መጫወቻ ሆና አስክሬኑዋ የመጣን የጎሮቤት ልጃገረድ ቀብራ የራሱዋን የ፩፭ ዓመት ልጅ ባወጣዉ ያዉጣሽ ብላ መልሳ ወደዛዉ የምትልክን እናት፣የኮሎኔል ግሩም አይነት በሞሉባት ኢትዮጵያ ፣ ዛሬ እኔ ሞቼ ልጆቹን ከዉርደት ማዳን አለብኝ ከማለት ፋንታ እርሱም ፈርቶ ለመብታቸዉ የሚቆሙትን ሊጆቹን ለስደት ልኮ ባህር በላቸዉን ዜና ከሚጠብቅ አባት፣ መቀበሪያዉን ኢንኳን ለማትሞላ መሬት ማንነቱን የሸጠን ሰደተኛ ማህበረሰቡ በቃቹ ካላለ ፣ ለሆድ ማደር አገርን ማዋረድ ፣ ሃፍረት መሆኑ ቀርቶ ጥበብ በሆነበት ዘመን በሆድ አደሮች ጩኸት መደንቆራችን መልሰንም መጮሃችን ይቀጥል ኢንድሁ አንጂ ክብርን አያመጣም።ዉርደታችን የሚያበቃዉ የህዝብና የአገር ጠላቶች የሆኑትን የወያኔ ቅጥረኞች በቃቹ ብለን ፍትለፍት ለመጋፈጥ ስንቆርጥ ብቻ ነዉ።
ዉርደታችን የምያበቃዉ ትላንት እነሱ ተቀጥረዉለት የነበረዉን ሻቢያን ኢንዳላገለገሉት ሁሉ ዛሬ ከእናንተ ጋር ተዋረደን ከምንኖር ሞት ያሉትን በምንም መስፈርት የሻብያ አሽከር ብላቹ ብትጮሁ አንሰማቹሁም የማለት ብቃት ስናገኝ ነዉ።
ዉርደታችን የምያበቃዉ ገንዘባችንን በማዉጣት ለነጻነት የምደረግን ትግል ለማገዝ ስንቆርጥ፣ አስፈላጊም ከሆነ ለዘላለም ተዋርዶ ከመኖር እንደ ግሩም በክብርም ብሆን ለመሞት መቁረጥ ስንችል ነዉ።
ዉርደታችን የሚያበቃዉ በየእስር ቤቱ እየማቀቁ ያሉትን ወገኖቻችንን ልቀቁ ካልሆነም እናንተ ሌቦችን ከስር ቤት ኢያስመለጣቹ ለስልጣን ኢንደበቃቹ እኛም የወገኖቻችንን በዸል ለመበቀል ቆርጠናል ስንል ነዉ።
ዉርደታችን የሚያበቃዉ ከ፴ ሺ ብር በላይ ደሞዝ ፣ስም ፣ ዝና፣ ክብር፣ አለምን መዞር በጁ እያለ የወገኑን ብሶት ለአለም በማሳየት ወሂኒ መጣልን እንደመረጠዉ ሀይለመድህን አበራ እምቢ ስንል ብቻ ነዉ።መቀራረብን በመሻት፣ መቻቻልን ለመፍጠር የሚደረግ ነገር ሁሉ ለቅጥረኞች ለሆድ አደሮች ካልገባቸዉ ከነሱ መለየት አማራጭም አቆዋራጭም መሆኑ ግድ ነዉ።
ያለን አማራጭ ሁለት ብቻ ነዉ፣
አንድም እንደ ኮሎኔል ግሩም አበበ ወደፊት ሄዶ ግንባርን ሰጥቶ በክብር ማለፍ ሁለትም ከነዉርደት ፵ የማትሞላዋን ዕድሜ መኖር። አንድም እንደ ሀይለመድህን አበራ ሃምሳ ዓመትም ቢሆን ወይኒ መጣል ሁለትም በገዛ አገሩ የመጨረሻ ደረጃ ዜግነት መቀበል። አንድም እንደባህር ዳር ህዝብ መቆጣት ሁለትም በባዶ እግሩ የሚሄድ ለሃጫም አየተባሉ መኖር። አንድም የዓዱዋን ጀግኖች ፈለግ መከተል ሁለትም የደደቢትን ሹምባሾች ካልሲ ማጠብ። አንድም ሰዉ ሆኖ መራብ ሁለትም እንደ አባመላ ተብየዉ ትፋትን ልሶ መጥገብ።
ያለዉን ምርጫ መለየት ካልተቻለ ዉርደትን ከክብር የቆጠሩ አሳሞች ስጮሁ በአሳሞቹ የበገኑም አትጩሁ ኢያሉ ስጮሁ ዉርደቱም ጩኸቱም ይቀጥላል ኢስከወዲያኛዉ።

አዩም አያኔ ዘ ኢትዮጵያ

pompidoayane@ymail.com

የሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ አሳሳች መረጃዎችና የተምታታ አስተያየት

$
0
0

በመሠረቱ ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ ስለ አብዮቱ “ እኛና አብዮቱ “ የሚል መጸሐፍ ጻፉ የሚል
ዜና ስሰማ ፣ መጸሐፋቸው እንደ ሌ/ኮ መንግሥቱ ኃይለማርያም መጸሐፍ በቅጥፈት የተሞላ
አይሆንም ብዬ ተስፋ አድርጌ ነበር ፡፡ ግን ሳይሆን ቀረ ፡፡ በነገራችን ላይ የሻምበሉን መጸሐፍ ገና
አላገኘሁትም ፣ ነገር ግን አንድ ወዳጄ ከምዕራፍ 13–16 ያሉትን ገጾች ፎቶ ኮፒ አድርጎ ስለሠጠኝ
አየተገረምኩኝ አነበብኳቸው ፡፡ ሻምበሉን ምን ነካቸው ብዬም እራሴን ጠየኩኝ ፡፡ ደራሲው
በትምህርታቸው እንዳልገፉ ይገባኛል ፡፡ ሆኖም ግን በትምህርት ያለመግፋት ትንታኔ ላይ ችግር
ይፈጥር እንደሆን እንጂ ፤ “ በእጅ የገባን መረጃ ” አሳስቶ ማቅረብ ከምን ሊመነጭ እንደሚችል
ፈጽሞ ሊገባኝ አይችልም ፡፡ ፍቅረሥላሴ መረጃው በእጃቸው ከሌላቸው አርፈው መቀመጥ አለባቸው
እንጂ ባልሆነ ማስረጃ አንባቢን ማሳሳት የለባቸውም ፡፡ መረጃው በእርሳቸው በኩል መቅረቡ ደግሞ
የበለጠ አደገኛ የሚያደርገው ፣ ግለ-ሰቡ በደርግ ውስጥ በከፍተኛ ሥልጣን ላይ የነበሩ ሰለሆኑ
መረጃው አላቸው ተብሎ ስለሚገመት ነው ፡፡ ዕውቀት መቸም በሁለት መንግድ እንደሚገኝ
ይታወቃል ፡፡ አንደኛው መንገድ ቀጥተኛ የሚባለው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ቀጥተኛ ያልሆነው መንገድ
ነው ፡፡ ቀጥተኛ የምንለው ፣ በራሳችን ተመክሮ የምናገኘው ዕውቀት ሲሆን ፣ ቀጥተኛ ያልሆነው
ደግሞ ከሌሎች ሰዎች ተመክሮ የሚገኝ ነው ፡፡ እኝህ ደራሲ ግን ከሁለቱም የታደሉ አይመስለኝም ፡፡ የጻፉት መጸሐፍ በራሳቸው ዘመን ያውም ቁልፍ ተዋናኝ ሆነው በተሳተፉበት ወቅት ስለተከናወነ
ጉዳይ ከመሆኑም በላይ ፣ ስለወቅቱም የሚያወሱ መጸሐፍቶች በብዛት ተጽፈው ይገኛሉ ፡፡ አንዳንድ
ጉዳዮች ሊረሱ ስለሚችሉ ደራሲው መረጃዎችን ከነዚህ መጸሐፍቶችና ከምርመራ መዝገቦች ላይ
ማግኘት ይችሉ ነበር ፡፡ እርሳቸው ግን ይኸንን ሁሉ መቸገር የፈለጉ አልመሰለኝም ፡፡ እስቲ ትዝብቴን
እርሳቸው ከፍ ብየ በጠቀስኳቸው ምዕራፎች ውስጥ ካቀረቧቸው አስተያቶች አንዳንዶቹን እየመዘዝኩ
በመኢሶን ድርጅት ዙሪያ ባቀረቡት ነጥቦች ላይ ብቻ በማተኮር አስተያየቶቼን ለማቅረብ ይፈቀድልኝ ፡፡
I. የመረጃ ስህተቶችን በተመለከተ
ሀ – የሕዝብ ድርጅት አባላትን በተመለከተ
በሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ መጸሀፍ የቀረበልን የተሳሳተና ያልተሟላ መረጃ (
ገጽ 230 )
1 . አቶ የወንድወሰን ኃይሉ
2 . አቶ መሥፍን ካሱ
3 . ዶ/ር ሰናይ ሌኬ
4 . ዶ/ር ነገደ ጎበዜ
5 . አቶ ኃይሌ ፊዳ
6 . ዶ/ር ፍቅሬ መርዕድ
7 . አቶ አሰፋ መድሀኔ
8 . አቶ እሸቱ ጮሌ (ዶ/ር መባል አለበት)
9 . ዶ/ር መለሰ አያሌው
10 . አቶ ተስፋዬ ሸዋዬ
11 . አቶ ባሮ ቱምሳ
12 . ዶ/ር በዛብህ ማሩ
13 . አቶ ዮሐንስ አድማሱ ናቸው ፡፡ ( አቶ ዮናስ አድማሱ ለማለት ፈልገው
መሰለኝ ) የሚገርመው ነገር ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምም “ትግላችን” ብለው ባሳተሙት መጸሐፋቸው ላይ ቁጥሩን ወደ 11 ዝቅ አድርገውታል ፡፡ ሰዎቹ
ወይ ጃጅተዋል ፣ አለበለዚያም የማስረጃ ጥቅሙ ስለማይገባቸው ፣ አቀራረቡ ላይ
ደንታቢስ ናቸው ማለት ነው ፡፡ ስለዚህ አንባቢ የነርሱን ሥራ በሚያነብበት ወቅት
በጥንቃቄ ከሌሎች ማስረጃዎች ጋር እያመሳከረ መሆን ይኖርበታል ፡፡
በአቶ አንዳርጋቸው አሰግድ “በአጭር የተቀጨ ረጅም ጉዞ” የቀረበልን ትክክለኛና
የተሟላ መረጃ (ገጽ 296 )1 . አቶ ኃይሌ ፊዳ
2 . ዶ/ር ፍቅሬ መርዕድ
3 . ዶ/ር ከድር መሐመድ ( በኋላ ላይ ወደ ኢሉ አባቦራ የሕዝብ ድርጅት ጽ/ቤት
የተዛወረ )
4 . አቶ መስፍን ካሱ
5 . ዶ/ር ነገደ ጎበዜ
6 . አቶ ባሮ ቱምሳ
7 . አቶ ዮናስ አድማሱ
8 . ዶ/ር ሠናይ ልኬ
9 . አቶ ሸዋንዳኝ በለጠ
10 . ዶ/ር እሸቱ ጮሌ
11 . ዶ/ር መለስ አያሌው
12 . ዶ/ር አሰፋ መድኀኔ
13 . አቶ ተስፋዬ ሸዋየ
14 . ዶ/ር በዛብህ ማሩና
15 . አቶ የወንድወሰን ኃይሉ – ከነዚህ ውስጥ ዶ/ር እሸቱ ጮሌና አቶ ዮናስ
አድማሱ ከጽሕፈት ቤቱ እንደተሰናበቱ ፣ በምትካቸው ዶ/ር ንግሥት አዳነና ዶ/ር ዓለሙ
አበበ ተጨምረዋል ፡፡ ከነዚህም ሌላ በኋላ ላይ የአፋር ነፃነት ንቅናቄ መሪ አባል የነበረው
አቶ ዩሱፍ ያሲን የጽ/ቤቱ አባል ሆኗል ፡፡ ለ – ከአዲስ አበባ ህቡዕ የገቡትን የመኢሶን አባሎችን በተመለከተ
በሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ የቀረበልን ያልተሟላና የተሳሳተ መረጃ ( ገጽ 342-3 )
1ኛ ቡድን ፡- በጎጃም በር በሱልልታ በኩል ለመውጣት የሞከረ ፤
 ኃይሌ ፊዳ የቡድኑ መሪ (በነገራችን ላይ ህቡዕ ስንገባ ቡድን መሪ የሚባል
አልነበረንም ፡፡ ደራሲው ከየት እንዳመጡት አላውቅም ፣ ምናልባት በወታደር
ዓለም ውስጥ ያለ ቡድን መሪ መንቀሳቀስ አይቻልም መሰለኝ ?)
 ዳንኤል ታደሠ
 ዶ/ር ከበደ መሸሻ ( የዶ/ር ከበደ አባት ሥም ፣ መሸሻ ሳይሆን መንገሻ ነው )
 ደረጀ ዓለማየሁና ጥቂት የመኢሶን ካድሬዎች ፡፡ 2ኛ ቡድን ፡- በወለጋ በኩል ሊወጣ የሞከረ ፤
 ተፈራ ገ/ፃዲቅ የቡድኑ መሪ (ግለሰቡ ስማቸው ተፈራ ገ/ፃዲቅ ሳይሆን ፣ዶ/ር
ተረፈ ወልደፃድቅ ነው፡፡
 ዳነቢ ዲሳሳ የተፈራ ገ/ጻዲቅ ሚስት ( ደንቢ ዲሳሳ እዚህ ቡድን ውስጥ
አልነበረም )
 አማረ ተግባሩ
 መርዕድ ከበደ
 ኃይሉ ገርባባና ሌሎች የመኢሶን አባላትና ካድሬዎች ፡፡ ( ኃይሉ ገርባባ በዚህ
ቡድን ውስጥ አልነበረም ፡፡ እርሱ ከወለጋ ካድሬዎች ጋር ነው የወጣው )
3ኛ ቡድን ፡- በጂማ መስመር ለመውጣት የሞከረ ፤
 ኃይለሥላሴ ወ/ ገሪማ የቡድኑ መሪ
 በለጠ ወትሮና ሌሎች የመኢሶን አባላት ፡፡ 4ኛ ቡድን ፡- በሲዳሞ በኩል ለመውጣት የሞከረና በከፊልም ቢሆን የመትረፍ ዕድል
የገጠመው
 መስፍን ካሱ የቡድኑ መሪ
 ዶ/ር ንግሥት አዳነ ( ከዚህ ቡድን ጋር አልነበሩም ) ደስታ ታደሰ (ከዚህ ቡድን ጋር አልነበሩም )
 ዳዊት አሰፋ
 አበራ የማነአብ
 አንዳርጋቸው አሰግድ ናቸው ፡፡ በዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ተሟልቶ የቀረበ
ወደ ጫንጮ የተጓዙ ጓዶች
 አቶ ኃይሌ ፊዳ
 ዶ/ር ከበደ መንገሻ
 አቶ ዳንኤል ታደሠ
 አቶ አያሌው ወልደ መድህን
 አቶ አበበ ኃይሌ
 አቶ የራስወርቅ አድማሴ
 አቶ ደረጀ ዓለማየሁ
 አቶ ዳንኤል (የትግል ስም ፣ ሾፌር ሆኖ ያገለገለ)
 ደንቢ ዲሳሳና ምትኩ ተርፋሳ ባካባቢው የሕዝብ ድርጅት ጽ/ቤት ባልደረባ
ስለነበሩ ከዚህ ቡድን ጋር አብረው ነበሩ ፡፡ ወደ አምቦ የተጓዙ ጓዶች
 ዶ/ር ተረፈ ወልደፃድቅ
 ወ/ሮ አጥናፍዓለም ይማም ( የዶ/ር ተረፈ ባለቤት )
 አቶ ከበደ ደሪባ
 አቶ እዮብ ታደሠ
 አቶ መርዕድ ከበደ
 አቶ አማረ ተግባሩ
ወደ ከንባታና ሀዲያ የተጓዙ ጓዶች
 አቶ ደስታ ታደሰ
 ዶ/ር ንግሥት አዳነ
 አቶ ኃይለሥላሴ ወልደገሪማና
 አቶ ኤፍሬም ዳኜ ሲሆኑ ፤ አቶ በለጠ ሙቱሮ ከአዲስ አበባ የሔዱ ሳይሆን ፣
እዛው የአውራጃው የሕዝብ ድርጅት ጉዳይ ጽ/ቤት ሠራተኛ የነበሩ ናቸው ፡፡ ወደ ሲዳሞ የተጓዙ ጓዶች
 አቶ አበራ የማነአብ
 አቶ አንዳርጋቸው አሰግድ
 አቶ መስፍን ካሱ
 አቶ ግርማ ሥዩም
 አቶ ዳዊት አሰፋ
አቶ ጋሻው ታደሠ ናቸው ፡፡ የሚገርመው ነገር ሌ/ኮ መንግሥቱ ኃይለማርያምም ሆኑ ሻም / ፍቅረሥላሴም፣
መኢሶኖች የተገደሉት በገበሬዎች እንጂ በኛ አይደለም ብለው ሽምጥጥ አድርገው ይዋሻሉ ፡፡ ዕውነቱ ግን ፣
የኢትዮጵያ ገበሬ እኛን ስለደበቀን ብቻ አብሮን ከመታሰርም አልፎ በድብደባ ተሰቃይቷልም ፡፡ አብዳላ ሶኔሳ
የኢትዮጵያ ገበሬዎች ማኀበር ፕሬዘዳንት ሆኖ በአብዮት አደባባይ ገበሬውን ወክሎ ንግግር ባደረገበት ወቅት
በንንግግሩ ላይ ደርግን ስለእኛ ድንገተኛ መሰወር የጠየቀው ጥያቄ ፤ “ እነዚያ እንደሱካር ይጣፍጡን የነበሩት
ልጆቻችን ወዴት ገቡ “ ብሎ ነበር ፡፡ ከንግግሩ ቆርጣችሁ ካላወጣችሁት በማስታወቂያ ሚኒስቴር ቤተ- መጸሐፍት ይገኛል ፡፡ በከንባታና ሀዲያ የተሸሸጉት ጓዶችም የተያዙት እርሶ እንደሚሉት በገበሬዎች ሳይሆን ፣መንገድ መሪዎቹ በከተማው የሠዐት እላፊ ለውጥ መደረጉን ባለማወቃቸው የተነሣ ፣ በወቅቱ ከተማውን
በሚጠብቁ የከተማው ፖሊሶችና በቀበሌ ጠባቂዎች ነው ሊያዙ የቻሉት ፡፡ ከዚያም ገበሬዎቹም ጓዶቹም
አብረው ተይዘው አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ ነው ፣ ሁለቱን ማለትም ዶ/ር ንግሥት አዳነንና አቶ ደስታ
ታደሠን ከእስር ቤት ( ከከርቸሌና ከ4ኛ ክፍለ ጦር ) አውጥታችሁ ከነ ጓድ ኃይሌ ፊዳ ጋር አብራችሁ
የገደላችኋቸው ፡፡ ሀቁ ይኸው ነው ፣ የናንተም የምርመራ ሠነድ ቢፈተሸ ይኼንኑ ሀቅ ነው የሚመሰክረው ፡፡ ለምን የእናንተን ወንጀል በገበሬው ላይ እንደምታሳብቡ አይገባኝም ፡፡ እረስተውት ነው እንጂ ፣ በወቅቱ
ያስተላለፋችሁት ትዕዛዝ እኮ በተገኙበት ይገደሉ የሚል እንጂ እጃቸውን በሠላም ከሠጡ ያዟቸው የሚል
አልነበረም ፡፡ አንድ ቀን ይኸም የሕትመት ብርሃን ማየቱ አይቀርም ፡፡ እናንተ ያኔ የሚታያችሁ የነበረው
የተማረውን ክፍል አስወግዳችሁ ሥልጣን አለተቀናቃኝ መጨበጣችሁ ነው እንጂ ፣ አገሪቷንና አብዮቱን
ይዛችሁ ገደል መግባታችሁ አልታያችሁም ፡፡ አሁንም ለሠራችሁት ወንጀል ንሰሀ የገባችሁ አይመስለኝም ፡፡ ይኼ እንግዲህ ቀላሉን ነገር መረጃ ማቅረብን በተመለከተ የቀረበውን የግብር ይውጣ ሥራ ለማመልከት ስል
ያቀረብኩት ነው ፡፡ ይህችን ሰነድ አሰባስቦ መልክ በማስያዝ ማቅረብ ያቃታችሁ አገርን የመምራት የሚያህል
ኃላፊነት እንዲት ተሸከማችሁ ? እስቲ ደግሞ አስገራሚውንና እርስ በእርሱ የሚጣረሰውን ትንተናቸውን
እንመልከት ፡፡ መኢሶን ለምን እራሱን
ከኢማሌድህ አገለለ ? ለዚህ ጥያቄ ሻምበል ፍቅረሥላሴ የሠጡት መልስ የሚከተለውን ይመስላል ፤ “ የአገራችን ጠላቶች የከፈቱብንን የተቀናበረ ጦርነት በምን ዘዴ እንመክት ? አደጋውንስ እንዴት አድርገን
እናስወግድ ? ብሎ ከመመካከርና ጠንክሮ ከመቆም ይልቅ መኢሶን አብዮቱን በመክዳት ለመሸሽ ውሳኔ
ለማድረግ በመጋቢት ወር 1969 ኮንፈረንስ ጠራ ፡፡ የኮንፈራንሱ ተሳታፊዎች በአገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ
በስፋት ከተወያዩ በኋላ “ ከደርግ ጋር የመሠረትነው ትብብር ተቋርጧል ፣ የትግል ለውጥም አድርገናል “ የሚል ውሣኔ አሳለፉ ካሉ በኋላ ፤ ከአብዮቱ “የሸሸንበትን” ምክኒያት ግን በሁለት ከፍለው ያቀርቡታል ፡፡ “ አንደኛው ምክኒያት መኢሶን በአቋራጭ በብልጣብልጥነት ሥልጣን በአጭር ጊዜ እጨብጣለሁ ብሎ የቀየሰው
ዘዴ ተግባራዊነት እየራቀ መምጣቱ ፣ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የመኢሶን መሪ ካድሬዎች ፈሪና ድንጉጥ
መሆናቸው ነው “ በማለት ይደመድማሉ ፡፡ እስቲ የሻምበሉን ግምቶች አንድ ባንድ እንመልከታቸው ፡፡ ይህ
መኢሶን ባቋራጭ በብልጣብልጥነት ለሥልጣን ያበቃኛል ብሎ የቀየሰው ዘዴ ምን ይሆን ? እርሳቸው አዋጁን
ይጠቅሱታል እንጂ አንብበውትም የሚያቁ አይመስለኝም ፡፡ ይህ ገጽ 231 ላይ የጠቀሱትን አዋጅ አንብበውት
ቢሆን ኖሮ ፣ ሥልጣንን በተመለከተ የመኢሶንን ዕቅድ አዋጁ ላይ ያገኙት ነበር ፡፡ አዋጁ የሥልጣን ጥያቄን
በተመለከተ ፤ “ የሠፊው ሕዝብ ትግል ተደራጅቶና ገፍቶ አብዮታዊ ሕዝባዊ ግንባሩ እንደተቋቋመ በትግል
ውስጥ የተሳተፉት የግንባሩ አባል ፓርቲዎችና የፖለቲካ ድርጅቶች ከሚያቀርቧቸው ምልምሎች መሀከል
ሕዝቡ በሙሉ ነፃና ምሥጥራዊ በሆነ ምርጫ እንደራሴዎቹን መርጦ የመንግሥቱን ከፍተኛ ሥልጣን
ወደሚይዘው አብዮታዊ ሸንጎ ይልካል ፡፡ የሕዝቡ ወኪሎች አጥንተው ባፀደቁት ሕገ-መንግሥት መሠረት
የመንግሥቱ መዋቅሮች ፣ ዘርፎችና የሥልጣን ክፍፍሎች ተወስነው በወዝ-አደሩ ፓርቲ መሪነት ሕዝባዊ
ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ይቋቋማል ፡፡ “ ነው የሚለው ፡፡ እንግዲህ ይኼ አዋጅ ገና በ1968 ዓ/ም ለሕዝብ
አብረን ቃል የገባንበት ነበር ፡፡ አዋጁ የመኢሶን የሥልጣን መወጣጫ አቋራጭ መንገድ ሊባልም አይገባም ፡፡ እናንተ ግን በደርግ ውስጥ የነበሩትን ተቀናቃኞቻችሁን በግድያ ካስወገዳችሁ በኋላ ፣ አዋጁን ወደ ጎን በማለት
እኛን የወንጀላችሁ ተባባሪ በማድረግ ሥልጣን ያለሕዝብ ይሁንታ ለመቆናጠጥ ፈለጋችሁ ፡፡ እኛም ከሕዝብ
ጀርባ በሚዶለት ሴራ ተባባሪ አንሆንም በማለታችን ልታጠፉን ተነሳሳችሁ ፡፡ በግልጽ እንገላችኋለን እስከማለት
ደረሳችሁ ፡፡ ያወጣነው አዋጅ ስለሥልጣን ሽግግር የሚለው በሕዝብ ይሁንታ ፤ “በወዝ-አደሩ ፓርቲ መሪነት
ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ይቋቋማል” እንጂ ፣ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችና ከፍተኛ ሲቪል
ቢሮክራቶች ተባብረው ኢሠፓን ይመሠርታሉ አልነበረም ፡፡ እናንተ ግን ያደረጋችሁት ይኸንኑ ነው ፡፡ አንድ
ፓርቲ ሳይሆን መድበለ ፓርቲ መቋቋም አለበት የተባባልነውንም ሽራችሁ ፣ ሕዝቡም ምርጫ እንዳይኖረው
አንድ ፓርቲ ብቻ ይበቃል በማለት ወሰናችሁ ፡፡ የጉዳችሁ ጉድ ደግሞ ሕዝቡ ከናንተው መሀከል እንኳን
የፈለገውን ግለሰብ እንዳይመርጥ ፣ የአንበሳና የጎሽ ምልክት ያላቸውን ትታችሁ ፣ ዝሆን ምልክት ያለውን
ብቻ ምረጡ አላችሁ ፡፡ ሻምበል ፣ ተዲያ መኢሶን እዝህ ጭምልቅ ውስጥ ለምን አብሮን አልገባም ብለው ነው
“ መኢሶን ከአብዮቱ ሸሸ “ የሚሉን ? ከአብዮቱ የሸሸው የ1968 ቱን አዋጅ የሻረ እንጂ ለአብዮቱ ተግባራዊነት
በፅናት የታገለው መኢሶን ሊሆን አይችልም ፡፡ ለመሆኑ አብዮት ማለት ደርግ ማለት ነው ብሎ የነገሮት
ማነው ? እናንተ የወር ደሞዘተኞች ሆናችሁ የንጉሡን ሥልጣን ስትንከባከቡ ፣ መኢሶን እንደ ፖለቲካ
ድርጅት የንጉሡን ሥርዐት ለመለወጥ ከውስጥም ከውጭም ይታገል እንደነበር አለማወቆን ከመጸሐፎ
ተረድቻለሁ ፡፡ ለእርሶ የፖለቲካ ድርጅቶች የተቋቋሙት በናንተ የግዛት ዘመን ይመስሎታል ፡፡ ሌላው አስቂኝ
ነገር ደግሞ “መኢሶን የሸሸው የሱማሌን ጦር ፈርቶ ነው” ያሉት ነው ፡፡ እርሶ ያለፍርሀት ምንም የሚያውቁትነገር ያለ አይመስለኝም ፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ከየገጠሩ ተመልምሎ የመጣውን የሚሊሺያ ጦር ፣ የመኢሶንን
ያህል በቅርብ የምታውቁት አይመስለኝም ፡፡ የመኢሶን ጓዶች ከምልምል ሠራዊቱ ጋር አብረው በመሠልጠን
ወደ ጦሩ ግንባር ለመዝመት ጥያቄ ባቀረቡ ጊዜ እምቢ ማለታችሁን እረሱት ? እስቲ ስለዚህ ጉዳይ የእርሶው
ድርጅት አባል የነበሩት ገስጥ ተጫኔ ምን እንደሚሉ አብረን እንመልከት ፡፡ ገሥጥ “ነበር” ብለው በሰየሙት
የመጀመሪያው መጸሐፋቸው ገጽ 269 ላይ ፤ “ የሶማሊያን ወረራ ለመመለስ በታጠቅ ጦር ሠፈር እየሰለጠነ
በነበረው ሚሊሻ ሠራዊት ውስጥ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የኢማሌድኅ አባል ድርጅቶች የደርግን ፈቃድ ጠየቁ ፡፡ በግልም ሊቀ መንበር መንግሥቱን ተለማመጡ ፡፡ በተለይ መኢሶን ብዙ ወትውቶ ነበር ፡፡ “ ካሉ በኋላ
መኢሶን ፤ “ … አሰርጎ ያስገባቸው ካድሬዎቹም ተመንጥረው ወጡ ፡፡ “ ይላሉ ፡፡ መኢሶን ከሠራዊቱ ጋራ
እንዳይቀላቀል ይከልከል እንጂ ፣ የአብዮታዊ ሰደድ ፣ የወዝ ሊግና የማሌሪድ ካድሬዎች በጦሩ ከምፕ ውስጥ
እንደልባቸው ሲፈነጩበት እንደነበር ገስጥ ተጫኔ በዚሁ ገጽ ላይ ያብራራሉ ፡፡ መኢሶን ከጦሩ ጋር አብሬ
ልዝመት አለ እንጂ ከአገር ጉደይ ሸሽቶ አያውቅም ፡፡ ሻምበል ወደዱም ጠሉም ሀቁ እንግዲህ ይኸው ነው ፡፡ ሥልጣን ከሕዝብ ይሁንታ ውጭ አንፈልግም ማለታችንንም አሌ እንዳይሉ ፣ ይህን በተመለከተ አቶ ተስፋዬ
መኮንን “ ይድረስ ለባለታሪኩ “ ብለው ጥቅምት 1985 ያሳተሙትን መጸሐፋቸውን ገጽ 243ን ይመልከቱ ፡፡ ገስጥ ተጫኔም “ነበር” ብለው በ1996 ዓ/ም ያሳተሙትን መጸሐፍ ገጽ 270 ቢመለከቱ አቶ ተስፋዬ ያሉትን
ነው የሚያረጋግጡት ፡፡ ስለዚህ የራሳችሁን ሥልጣን ባቋራጭ የመያዝ ጉጉት የመኢሶን ዘዴ ነው አትበሉ ፡፡ ለሕዝብ በአዋጅ ቃል የገባችሁትን ያጠፋችሁት እናንተ እንጂ መኢሶን አይደለም ፡፡ ለነገሩ መኢሶን ከመደብ
ባህሪያችሁ በመነሳት ይኸንኑ እንደምታደርጉ ገና በ1968 ዓ/ም ግንቦት 11 ቀን ባወጣው በሰሕድ ቁጥር 40
አማካኝነት ለሕዝብ ፤ “ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ይህን ፕሮግራም ከሥራ ላይ ሊያውል አይችልም ፡፡ ስለዚህም ደርጉ የቀድሞ ወላዋይነቱን ካስቀረ ፤ የዚህን መለስተኛ አዋጅ ሥራ ላይ መዋል የሚያግዙ
እርምጃዎች በመውሰድ የሠፊውን ሕዝብ ትግል ሊያገለግል ይችላል ፡፡ ሠፊውን ሕዝብ ተክቶ ግን ይህን
ፕሮግራም ከሥራ ላይ ሊያውል አይችልም ፡፡ የዚህ መለስተኛ ፕሮግራም ታሪካዊ ቦታ ለአገራችን ችግሮች
ዛሬውኑ መፍትሔ ስለሚያስገኝ አይደለም ፡፡ ሠፊው ሕዝብ ለነዚህ መፍትሔዎች እራሱ እንዲታገል ለማንቃት
፣ ለማደራጀትና ለማስታጠቅ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር በመሆኑ ነው ፡፡ “ ሲል አስታውቆ ነበር ፡፡ ስለዚህ
ሻምበል የሥልጣን ጥመኝነቱ እናንተን የሚመለከት እንጂ መኢሶንን አይደለም ፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ያስቀመጡት
መላ ምቶ ደግሞ እኛ “ከአብዮቱ የሸሸነው” የሱማሌን ጦር ስለፈሩ ነው ነው የሚሉት ፡፡ ሻምበል ምን ነካዎት
? መኢሶኖች እኮ ባዶ እጃችንን “ ታጋይ ይሞታል ፣ ትግል አይሞትም “ እያልን ከፀረ-አብዮተኞች ጋር
እንደታገልን እርሶም ሳያውቁት በመጸሐፎ ውስጥ መስክረውልናል እኮ ፡፡ ከሸሸን ያኔ ነበር የምንሸሸው ፡፡ እስቲ
በመጸሐፎ ገጽ 318 ላይ ስለእኛ ያሉትን ላስታውሶት ፡፡ “ እነዓለማየሁ በደርግ ውስጥ ያካሔዱት ሰላማዊ
መፈንቅለ-መንግሥት በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያስገኝልናል ብለው የጠሩት ሕዝባዊ ስብሰባ ተቃራኒ ውጤት
አስገኘ ፡፡ መኢሶን ቀስቅሶ ወደ አደባባይ ላወጣው ሕዝብ አቋሙን ለማሳወቅ ጥሩ አጋጣሚ ስለተፈጠረለት
ተጠቀመበት ፡፡ በቀላሉ የማይታይ ኃይል እንደሆነም አሳየ ፡፡ በአደባባይ የታየው የተቃውሞ እንቅስቃሴ
የነዓላማየሁን ቡድን ሲያሳስብና ስጋት ላይ ሲጥል ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱንና ደጋፊዎቻቸውን ያበረታታና የልብ
ልብ የሰጠ ነበር ፡፡ “ ብለው ነው የመሰከሩልን ፡፡ እናንተ ወኔያችሁ በከዳችሁ ወቅት መኢሶን የሕዝብን
ድጋፍ በመተማመን ብቻ ባዶ እጁን ከነዓለማየሁ ኃይሌ ጋር ተጋፍጦ እርሶም እንዳመኑት ስላበረታታናችሁና
የልብ ልብ ስለሠጠናችሁ ፈሪ ይሉናል ፡፡ ምን ያድርጉ እርሶ ማሰብ የሚችሉት ፈሪና ደፋር በሚሉ ቃላቶች
ብቻ ስለሆነ ፣ ስለኛ ጀግንነት ሊመሰክሩ አይችሉም ፡፡ ሻምበል ፣ ” ሌባ እናት ልጇን አታምንም “ ይባላል ፡፡ እርሶም ፍርሀቶ መረን የለቀቀ በመሆኑ የተነሳ እኛም እንደ እርሶ ፈሪ መስለን እንታዮታለን መሰለኝ ፡፡ ፈሪ
መሆኔን በምን አወክ ? ይሉኝ ይሆናል ፡፡ ማን እንደነገረኝ ለማወቅ ብዙም አይጨነቁ እርሶው እራሶ ኖት
በመጸሐፎ ውስጥ ያሰፈሩት፡፡
ሌ/ኮ ፣ መንግሥቱ ኃይለማርያም እርሶን እንደማይተናኮሎት በብዙ አጋጣሚዎች አሳውቀዎታል ፣ እርሶ ግን
ከፈሪነቶ ብዛት የተነሣ አምነዋቸው ሊረጋጉ አልቻሉም ፡፡ ከሚገደሉት ማህል በስህተት እንደተደለደሉና በኮ/ል
ዳንኤል አስፋው አማካኝነት ከሞት እንደተረፉ በመጸሐፎ ተርከውልናል ፡፡ ይህ እንግዲህ እርሶ በሌ/ኮሌኔሉ
በክፉ ዐይን እንደማይታዩ ሊያረጋግጥሎት በተገባ ነበር ፡፡ እርሶ ግን ሊቀመንበሩ ከእልቂቱ የተረፋችሁትን ፣
በአዳራሽ ሰብስበው ስለጉዳዩ ሊያስረዷችሁ በፈለጉ ጊዜ ገና እንደተሸበሩ ነበር ፡፡ አስቲ ሁኔታውን እንዴት
እንደገለጹት ላስታውሶት ፡፡ በመጸሐፎ ገጽ 326 ላይ ፤ “ ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ ወደ አዳራሹ ሲገቡ
ከመቀመጫችን ተነስተን ተቀበልናቸው ፡፡ የተረጋጉ ይመስላሉ ፡፡ ከወትሮው ይበልጥ ተኮሳትረዋል ፡፡ ፊታቸው
አስፈሪ ነው ፡፡ የወሰዱትን እርምጃ ስለምናውቅ ትኩር ብለን ዐይናቸውን የመመልከት ድፍረት አጣን ፡፡ ወዘተ.” ብለው ፍርሀቶ ገደብ የለሽ እንደ ነበር አስረድተውናል ፡፡ እኔ የምለው ፣ አልነካህም ከተባሉ በኋላ
ምንድነው እንደዚህ መንፈሽፈሽ ? ወታደር አይደሉም እንዴ ? እተፋፋመ ውጊያ ውስጥ ቢገቡ ምን ሊውጦትነው ? ሌላው የገረመኝ ነገር ደግሞ ስለ እነ መቶ አለቃ ዓለማየሁ ኃይሌ ማልቀስ የነገሩን ነው ፡፡ ምነው
የእርሶን በአራት ማዕዘን የወረደውን እንባ ዘነጉት ? ያውም መትረፎን ካረጋገጡ በኋላ ፡፡ ሻምበል ፣ መኢሶን
እንደናንተ የለት የለቱን እያሰበ ብቻ የሚጓዝ ድርጅት አልነበረም ፡፡ እናንተ አታነቡም እንጂ ፣ መኢሶን
በትግሉ ወቅት ከአብዮቱ ካፈገፈጋችሁ ጥሏችሁ በሚያመቸው መንገድ እንደሚታገል ቀደም ሲልም ነግሯችሁ
ነበር ፡፡ እናንተ ግን የእኛን ህቡዕ መግባት ከአብዮቱ እንደመሸሽ ቁጠራችሁት እንጂ የትግል ስልት ለውጥ
መሆኑን አልተረዳችሁም ፡፡ መኢሶን የሚከተለውን የትግል ስልት ሚያዚያ 30 ቀን ፣ 1968 ዓ/ም ባወጣው
የሠፊው ሕዝብ ድምፅ ቁጥር 39 ላይ የሚከተለውን ብሎ ነበረ ፤ “ መኢሶን በፕሮግራሙ መግቢያ ላይ
እንደገለጸው ፣ ለነዚህ አበይት ዓላማዎቹና በጠቅላላው ለፕሮግራሙ ሥራ ላይ መዋል … ያለአንዳች
ማወላወል ፤ በምሥጢርና በይፋ ፤ በሕጋዊ መንገድና በሕገ-ወጥነት ፤ በሠላማዊ መንገድና በአመፅ ፤
እንደጊዜውና እንደሁኔታው በሚለወጥ ታክቲክ ፤ ምንም ጊዜና ምንም ሁኔታ በማይለውጠው ቆራጥነትና
ታታሪነት የሚታገሉ አብዮታዊያንን አስተባብሮ ለኢትዮጵያ ሰፊ ሕዝብ ነፃነትና አንድነት አሰልፏል ፡፡ የኢትዮጵያ ጭቁኖች የሚያደርጉትን ትግል ዳር እስከ ዳር አስተባብሮ ፤ የተጣራ አብዮታዊ አመራር ለመስጠት
በጭቁን ሕዝቦችና በታሪክ ፊት የተቀበለውን አደራ እስከ መጨረሻው ይጠብቃል ፡፡ ጭቁኖች በትግላቸው
እንደሚገፉ ፤ በትግል እሳት የተፈተኑ አባሎቹ አብዮታዊ ግዴታቸውን ለመፈጸም ወደኋላ እንደማይሉ ሙሉ
እምነት አለው ፡፡ “ ከዚህ መግለጫ የምንረዳው ነገር ቢኖር ፣ መኢሶን የሶማሌ ጦርነት ከመምጣቱ ቀደም
ብሎም የትግል ስልት ለውጥ ሊያደርግ እንደሚችል ማሳወቁን ነው ፡፡ ስለዚህ የትግል ስልት ለውጥ ማድረጉ
እርሶ እንደሚሉት ድንገተኛና ከፍርሀት ጋር የተያያዘ አልነበረም ማለት ነው ፡፡ በተለይ እናንተ ከጥር 30 ቀን
፣ እሰከ የካቲት 4 ቀን ፣1969 ዓ/ም ድረስ ዝግ ስብሰባ አድርጋችሁ ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱን ባለሙሉ
ሥልጣን ከአድርጋችሁ በኋላ ፤ በ1968 ዓ/ም በአዋጅ ለሕዝብ የገባነው ቃል ኪዳን እንደተሻረ ምንም ጥርጥር
አልነበረንም ፡፡ ከዚያ በኋላማ በአገሪቱ ጉዳይ አለኛ ማን አለ በማለት ለያዥ ለገራዥ አስቸግራችሁ ነበር ማለት
ይቻላል ፡፡ የሚገርመው ነገር እኛን ለማጥፋት ከተባበራችሁ በኋላ እርስ በርስ ደግሞ መጨራረሳችሁ ነው ፡፡ እርሶ ግን ለሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ሥልጣን ስጋት ስላልነበሩ ወዳጅ ጓደኞቾ ሲያልቁ ከዚህ ሁሉ
መአት አመለጡ ፡፡ በጦር ሜዳ ውሎ ልምድ የነበራቸውን የጦር መኮንኖች እንድ ባንድ አጠፋችኋቸው ፡፡ መድረክ ላይ የሚሠራ ትያትር ይመስል እነመጋቢ ሃምሣ አለቃ ለገሠን የሠሜን ጦር አዛዥ አድረጋችሁ
ሾማችሁ ላካችሁ ፡፡ አንድም ጥይት ሳይተኩሱ የሠሜን ግንባሩን ጥለው ተመለሱ ፡፡ እኝህ ሰው
በሕይወታቸው የመቶ ጦር እንኳን መርተው አያውቁም ፡፡ ባህር ኃይሉንም ፣ ፖሊስ ሠራዊቱንም በበታች
ሹማምንቶች አስያዛችሁ ፡፡ በዚሁም የከፍተኛ መኮንኖችን ሞራል ገደላችሁ ፡፡ በመጨራሻም አገሪቷን አሁን
ለወደቀችበት ሁኔታ ዳረጋችኋት ፡፡ ይኸው ነው እንግዲህ ሻምበል የናንተ ሥራ ፡፡ እስካሁን የመኢሶንን
አመራር የሚተቹ ግለሰቦች የመኢሶን አመራሮች የወጣላቸው ምሁራን ናቸው ፣ ለአብዮቱም ከፍተኛ አስተዋፆ
ማበርከታቸው አሌ አይባልም ካሉ በኋላ ፣ የሚያዥጎደጉዱት ስድብና ወቀሳ ነው ፡፡ ኢሕአፓና እነመንግሥቱ
ኃይለማርያም መኢሶንን በቅብብሎሽ በመግደልም ፣ በማሰርም ካዳከሙትና ፣ አገሪቷን አሁን ላለችበት ሁኔታ
ከዳረጓት በኋላም የሚወቅሱት መኢሶንን ነው ፡፡ በዚህ ዐይነት በአገራችን ስህተት የሚሠራው ምሁሩ እንጂ
መሀይሙ አይደለም ማለት ነው ፡፡ እኔ እርሶን ብሆን ፣ ይኸንን ሠርቻለሁ ብዬ መፎከር ይቅርና ቀና ብዬም
ሰው አላይም ነበር ፡፡ እርሶ ግን ባለፈው ጥፋቶ የተፀፀቱም አይመስሉም ፡፡ በዚሁ ላብቃ ፡፡

መርዕድ ከበደ

የጎሣ ፖለቲካ፣ የጎሣ ግጭቶች እና መዘዛቸው በኢትዮጵያ (በዘመነ ወያኔ)

$
0
0

(ክፍል አንድ)
ከያሬድ ኃይለማርያም
ብራስልስ፣ ቤልጂየም፤
መግቢያ
ይህ ጽሑፍ በኢትዮጵያ ላለፉት አስርት አመታት ጎሣና ኃይማኖትን መሰረት አድርገው በተደጋጋሚ ጊዜያት በተከሰቱት ግጭቶች ዙሪያ እና ግጭቶቹ ባስከተሉት ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት ላይ የሚያተኩር ነው። በተለይም ከ1983 ዓ.ም. ወዲህ ጎሣን መሰረት ያደረገውን የኢሕአዴግ ፌዴራላዊ የመንግስት አወቃቀር ተከትሎ በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች ውስጥ የተከሰቱ ዋና ዋና ግጭቶችን ይዳስሣል። ለግጭቶቹ መንስዔ ተደርገው የሚጠቀሱትን ጉዳዮች፣ በግጭቶቹ ሳቢያ በሰው ሕይወትና በሕዝብ ንብረት ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን፣ ግጭቶቹ እንዳይከሰቱ ለመከላከልም ሆነ ከተከሰቱ በኋላም ለማብረድ እና ዘላቂ በሆነ መልኩ ለመፍታት በመንግስት የተወሰዱ እርምጃዎች፣ የመንግስት የግጭቶች አፈታት ስልት፣ እና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮችን ይህ ጽሑፍ በመጠኑ ይዳስሳል።
የጽሑፉም ዋነኛ ዓላማ ጎሣን እና ኃይማኖትን መሠረት አድርገው የሚቀሰቀሱ ግጭቶች፤ ሰብአዊ መብቶች በገፍ በሚጣሱበት፣ ዴሞክራሲያዊ መብቶችና ነፃነቶች በማይከበሩበት እና የሕግ ልዕልና ባልተረጋገጠበት፤ እንዲሁም ነፃና ገለልተኛ የፍትሕ ተቋማት በሌሉበት እንደ ኢትዮጵያ ባለ አገር ውስጥ የሚኖራቸውን መጥፎ ገጽታ ማሳየት ነው። በተለይም የኢሕአዴግን የጎሣ ፖለቲካ አወቃቀር ተከትሎ በአገራችን ተደጋግመው በመከሰት ላይ ያሉት የጎሣ ግጭቶች በአገሪቱ የልማት እንቅስቃሴዎችና በሕዝቡ ሰላምና ደኅንነት ላይ የሚያስከትሉትን ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ቀውሶች ማመላከት ነው።
ወደዚህ ጽሑፍ ዋና ክፍል ከመግባቴ በፊት ለአንባቢዎቼ ከላይ ከገለጽኳቸው የጽሑፉ አላማዎች በተጭማሪ የተወሰኑ ነገሮችን ከግምት ውስጥ እንድታስገቡልኝ ለማሳሰብ እወዳለሁ። በመጀመሪያ ይህን ጽሑፍ ለማዘጋጀት ምክንትያት የሆነኝን ነገር ልግለጽ። ለስምንት አመታት በሰብአዊ መብት ጥሰቶች አጣሪነት በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) ውስጥ ተቀጥሬ ባገለገልኩበት ዘመን ድርጅቱ ተከታትሎና አጣርቶ መግለጫ ባወጣባቸው በርካታ የጎሣና የኃይማኖት ግጭቶች ውስጥ በምርመራ ሥራ ተሳትፌአለሁ:: የተወሰኑትን ግጭቶች ከሌሎች የሥራ ባልደረቦቼ ጋር በመሆን ሥፍራዎቹ ድረስ በመገኘት፤ የተቀሩትን ደግሞ ሌሎቹ የድርጅቱ የምርመራ ሠራተኞች፤ በአካል ተገኝተው ካሰባሰቡዋቸው መረጃዎች በመነሳት ያካፈሉኝን እውቀትና መረጃ በመንተራስ ነው። ለዚህም ጽሑፍ በዋነኛነት ኢሰመጉ በግጭቶቹ ዙሪያ የወጣቸውን መግለጫዎች በማጣቀሻነት እጠቀማለሁ። እንዲሁም ሌሎች አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ያወጡዋቸውን መግለጫዎችና ሰነዶች በአባሪነት እጠቅሳለሁ።
ይህ ጽሑፍ ሦስት ክፍሎች ሲኖሩት፤ በመጀመሪያው ክፍል በጎሰኝነት ስሜት ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ አደረጃጀት እና አስተሳሰብ፣ የጎሣ ግጭቶች እና ከሰብአዊ መብቶች አጠባበቅ ጋር ያላቸውን ግኝኙነት በተመለከተ አለም አቀፍ ድንጋጌዎችን እና ሌሎች ሰነደችን በማጣቀስ የሚዳሰስበት ክፍል ነው። የዚህ ክፍል አላማም በኢትዮጵያ ውስጥ እየታየ ያለውን የጎሠኝነት ስሜትና እያስከተለ ያለውን ግጭት ባህሪይ እና አካሄድ በቅጡ ለመረዳት ይረዳ ዘንድ መሰረታዊ በሆኑ ጠቅላላ አስተሳሰቦችና በሌላው የአለም ክፍልም ይህ አይነቱ ችግር ያለውን ገጽታ በመጠኑ የሚዳስስ ነው። ሁለተኛው ክፍል በኢትዮጵያ ውስጥ በተደጋጋሚ ስለተከሰቱትና እየተከሰቱ ባሉት ግጭቶች ላይ የሚያተኩር ነው። በዚህ ክፍልም ውስጥ ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰቱትን ግጭቶች ባህሪ፣ መንሰዔያቸውን፣ የደረሱትን ጉዳቶች፣ የመንግስትን ሚና እና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ያነጣጠረ ነው። የመጨረሻውና ሦስተኛው ክፍል የኢሕአዴግ መንግስት የሚከተለው ፖሊሲ፣ ያወጣቸው ሕጎች፣ ግጭቶችን ቀድሞ እንዳይከሰቱ የመከላከልና ሲከሰቱም በቀላሉ ተቆጠጥሮ ዘለቄታዊ መፍትሔ የመስጠቱ ሂደት ምን እንደሚመስል በመጠኑ የሚፈትሽ ነው።

I. ጎሠኝነት፣ የጎሣ ግጭቶች እና ሰብአዊ መብቶች
1.1. ጎሠኝነት
የሰው ልጆች ሁሉ በሰብአዊ ፍጡርነታቸው ክቡር መሆናቸውን፤ እንዲሁም እኩልና ሊነጣጠሉ የማይችሉ መብቶች እና ነፃነቶች ያሏቸው መሆኑን በአለም አቀፍ ድንጋጌዎች ላይ ሰፍሯል። የእነኚህ መብቶች እና ነፃነቶች በአግባቡ መረጋገጥና መከበር ለአለም ሰላም እና ለሕዝቦች ደኅንነት ዋነኛ ምሰሶም እንደሆነ ተገልጿል። የሰው ልጆች በሰብአዊ ፍጡርነታቸው ተገቢውን ክብር በማያገኙበት፣ ሰው በመሆናቸው ብቻ የተጎናጸፉዋቸው መብቶች እና ነፃነቶቻቸው ባልተረጋገጠበት እና በገፍ በሚጣሱበት ሥፍራዎች ሁሉ አይነታቸውና ደረጃቸው ይለያይ እንጂ ግጭቶች፤ ከፍ ሲልም ጦርነቶች ይከሰታሉ። በመላው አለም መብቶቻቸው የተረገጡባቸውና ሰብአዊ ክብርን የተነፈጉ ሰዎች ለነፃነቶቻቸው መረጋገጥ እና ከጨቋኞቻቸው ነፃ ለመውጣት የሚያደርጉትን ትግል ተከትሎ በርካታ ጦርነቶች እና ግጭቶች በአለም ተከስተዋል፤ አሁንም በተለያዩ ሥፍራዎች ይታያሉ። አለማችን እጅግ ዘግናኝ የሆኑ እና በሚሊዮኞች ለሚቆጠሩ የሰው ልጆች መጥፋት ምክንያት የሆኑ በዘር ጥላቻና በጎሠኝነት ስሜት የተቀጣጠሉ በርካታ ግጭቶችን እና ጦርነቶችን አስተናግዳለች።
የተባበሩት መንግስታት ባወጣቸው የተለያዩ ሰነዶች ላይ እንደተጠቆመው ድርጅቱ ከተቋቋመበት፣ እ.ኤ.አ. ከ1945 ወዲህ እንኳን ከተከሰቱት በርካታ ጦርነቶች ውስጥ ዐብይ በሚባሉት ከመቶ በላይ በሆኑ ትላልቅ ጦርነቶች ብቻ ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሞተዋል። በአሥር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ደግሞ በጦርነቶቹ ሳቢያ ለስደት፣ ለርሃብ፣ ለድህነት እና ለበሽታ ተዳርገዋል። አብዛኛዎቹ ግጭቶች የዘር ልዩነትን መነሻ ባደረጉ ውጥረቶች፣ ያመረረ እና ጽንፍ የያዘ ብሔራዊ ስሜትና አክራሪ ጎሠኝነትን ተከትለው የተቀሰቀሱ ናቸው። አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት ከሆነ ከሁለተኛው የአለም ጦርነት ወዲህ በመላው አለም በፖለቲካ ብጥብጥ ሳቢያ ከሚሞቱ ሰዎች መካከል 80 በመቶ የሚጠጉት በጎሣ ግጭቶች ምክንያት ነው። በአለም ታሪክ ውስጥ ጎላ ብለው ከሚጠቀሱት ግጭቶች መካከል በአይሁዳዊያን ላይ የደረሰው ስቃይና የጅምላ ጭፍጨፋ፣ በጂፕሲዎችና በሶዶማዊያን ላይ የተካሄደው እልቂት፣ በሩሲያ እስታሊን በሰው ዘር ላይ የፈጸመው አሰቃቂ ወንጀል፣ በደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ ሥርዓት፤ እንዲሁም በዚምባብዌና በናሚቢያ ንኡሳን ነጮች (አውሮፓዊያን) የፈጸሙዋቸው እልቂት፣ በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በሱዳን፣ በሱማሌ እና በሌሎች የአፍሪካ አገሮች በተከሰቱ የእርስ በርስ ግጭቶች ሳቢያ ሚሊዮኖች ያለቁባቸውን ሁኔታዎች መዳሰስ እንችላለን።
በመጀመሪያ ደረጃ በጎሣ (ethnicity) እና በዘር (racial) ማንነት መካከል ያለውን ልዩነትና ዝምድና በመጠኑ ለመዳሰስ እወዳለሁ። የጎሠኝነት ስሜትና ማንነት የሚመነጨውና የሚጎለብተው እያንዳንዱ ሰው እራሱን ከአንድ በቋንቋ፣ በባሕል፣ በአካባቢያዊ ሁኔታ፣ ልማዶች እና ሌሎች ማኅበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከተሳሰረ የዘር ግንድ ጋር መነሻ በማድረግ የተደራጀ ወይም የተሰባሰበ የኅብረተሰብ ክፍል አባል አድርጎ ሲቆጥር እና በእነዚሁም መስፈርቶች እራሱን ከሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች የተለየሁ ነኝ ብሎ ማሰብ ሲጀምር ነው። በዘር ላይ የተመሰረተው ማነነት በርካታ ጎሣዎችን በውስጡ ያቀፈ ሲሆን ተመሳሳይ የሆነ ተፈጥሮአዊ የሆነ አካላዊ መገለጫዎችን መሰረት በማድረግ የቡድንኑ አባላት እራሳቸውን ከሌሎች ለይተው የሚገልጹበት ወይም በሌሎች ዘንድ የተለዩ የተርገው የሚገለጹበት ሁኔታ ነው፡፡ ይህ አይነቱ የቡድን ዘር መገለጫ በሥነ-ተፈጥሮ ሳይንስ የተደገፈ ሳይሆን ለቡድኑ
Ethnicity, conversely, is defined as a sense of common ancestry based on cultural attachments, past linguistic heritage, religious affiliations, claimed kinship, or some physical traits (1998, 19)፡ http://stanford.library.usyd.edu.au/entries/race/#RacVerEth
Racial identities are typically thought of as encompassing multiple ethnic identities (Cornell and Hartmann

መገለጫ በሚሰጠው ሰው አስተሳሰብና ምርጫ ላይ የተመሰረተ ነው። በሁለቱ መካከል ያለው ትልቁ ልዩነት የጎሣ ማንነት በእያንዳንዱ የጎሣው አባል መርጫና ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ነው። አንድ ሰው የአንድን ጎሣ ባህል፣ ቋንቋ፣ ልማዶች እና ሌሎች መገለጫዎችን ወዶና ፈቅዶ ሲያደርጋቸውና እራሱ የዛ ጎሣ አባል አድርጎ ሲቆጥር ነው የማንነቱ መገለጫ የሚሆነው። የዘር ማንነት መገለጫ ግን በእያንዳንዱ ሰው ፍላጎትና ምርጫ ሳይሆን በሌሎች አካላት ውሳኔ የሚጫን ነው። ለጥቁሮች መገለጫ የተደረገውን negro የሚለውን አገላለጽ የወሰንድ እንደሆነ በነጭ አክራሪዎች በመላው አለም ጥቁር የቆዳ ቀለም ላላቸው የሰው ልጆች ሁሉ የሰጡት መጠሪያ ነው።
የጎሣ ማንነት ቋንቋን፣ ባህልን፣ ኃይማኖታዊ ሥርዓቶችን ለማስተዋወቅ፣ ለማበልጸግ እና ይዞ በማቆየትም ከትውልድ ትውልድ እንዲተላለፉ ለማድረግ በመነጨ ፍላጎት ላይ ብቻ ሲወሰን እና ከዚህ አልፎ ለፖለቲካ ፍጆታ ሲውል የሚኖረው ውጤት እና ገጽታ ፍጹም የተለያየ ነው። በመጀመሪያው የአስተሳሰብ መስመር ላይ የተመሰረተው የጎሣ ማንነት ልዩነቶችን አጉልቶ በማውጣት ለመናቆሪያ ሳይሆን እንደ ጥለት ክር የተጠላለፉት የእያንዳንዱ የኅብረተሰብ ክፍል ባህሎች፣ ቋንቋዎች፣ ኃይማኖታዊ እና ታሪካዊ ትውፊቶች ለጠቅላላው ማኅበረሰብ የጥንካሬ እና ኅብረ ውበት ምንጮች ተደርገው ነው የሚቆጠሩት። በዚህ አይነቱ ማኅበረሰብ ውስጥ የአንዱ ክፍል ቋንቋ፣ ባህልና ሌሎች ማኅብራዊ እሴቶች ሁሉ የሌሎቹ የኅብረተሰብ ክፍሎች ሃብትና ጌጦች ናቸው። አንዱ ያለሌሎቹ፤ ሌሎቹም ያለአንዱ ውበትና ጥንካሬ የላቸውም። ይህ አይነቱ ማኅበረሰብ በውስጡ ግጭቶችና ቅራኔዎች ባያጡትም አንዱ የሌላውን ዘር ከምድረ ገጽ ለማጥፋት በመነሳት ወደሚፈጸሙ ዘግናኝ እልቂቶች አያመሩም። ልክ በአንድ ቤተሰብ አባላት መካከል ግጭቶች ተነስተው በእርቅ እንደሚፈቱት ሁሉ በዚህ አይነቱ ማኅበረሰብ ውስጥም የሚነሱ ቅራኔዎችና አለመግባባቶች በየአገሩ ወግና ባህል ወይም በሕግ አግባብ አፋጣኝ መፍትሄ ሲለሚያገኙ ወደ እልቂት አያመሩም።
ሁለተኛውና ለፖለቲካ ግብ ማሳለጫ መንገድ ተደርጎ የሚወሰደው ጎሣን መሰረት ያደረገው የማንነት መገለጫ እና የኅብረተሰብ ክፍሎች መቧደን ከላይ ከተጠቀሰው የጎሣ ምልከታ ጋር ከሚጋራው አንድ ነገር ውጪ እጅግ የተለየ መልክ እና ይዘት ያለው ነው። ሁለቱም የጎሣ ምልከታዎች መነሻቸው አንድ ነው። ይህውም በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ በቋንቋ ወይም በባህል ወይም በኃይማኖት ወይም በሌሎች የማንነት መገለጫ ተደረገው በልማድ በሚወሰዱ ልዩነቶች ዙሪያ የተሰባሰቡ የኅበረተሰብ ክፍሎች መኖራቸው ነው። አንድ ወጥ የሆነ ቋንቋ፣ ባህል፣ ኃይማኖትና ታሪክ ባለው ማኀበረሰብ መካከል የተለያየ የኅብረተሰብ ደረጃዎችና ክፍሎች ቢኖሩም የጎሣና የጎሠኝነት ጎዳዮች ጭርሱኑ የሚታሰብ ነገሮች አይደሉም። የጎሣ ልዩነቶች ከኅብር ውበት መገለጫነትና ባህልን፣ ቋንቋን፣ ታሪክን እና ኃይማኖታዊ እሴቶችን ለማስተዋወቅና ለማዳበር ከሚኖረው ፋይዳ ባለፈ የፖለቲካ አስተሳሰቦች ማቀንቀኛ እና የፖለቲከኞች የመታገያ መሳሪያ መሆን ሲጀምር ውበቱ ይደበዝዛል ወይም ጭርሱኑ ይጠፋል። ጎሠኝነት ፖለቲካዊ ገጽታው እጅግ ተጋኖና ጎሎቶ በወጣ ቁጥር ያንን ማኅብረተሰብ አቆራኝተው እና አፋቅረው ያቆዩትን ሠንሰለቶች የመበጣጠስ ኃይል አለው። በጎሣ በተሰበጣጠረው የኅብረተሰብ ክፍል ውስጥ የሚኖረው አወንታዊ ሚና ይቀርና የልዩነት ግንብ ይሆናል። የእያንዳንዱ ጎሣ ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክና ኃይማኖታዊ እሴቶች የራሱ ብቻ ይሆናሉ። አንዱ የሌላው ውበትና የጥንካሬ ምንጭ መሆኑ ይቀርና በፉክክርና በመበላለጥ ስሜት ላይ የተመሰረተ ልዩነት ይፈጥራል። ከዚያም አልፎ በጠላትነት የመተያየት ስሜት ይመነጫል። እያንዳንዱ ጎሣም በልዩነት ግንብ ውስጥ የራሱን ደሴት ይመሰርታል። በእንዲህ አይነቱ ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረው ጎሣን መሰረት ያደረገ ቅራኔ ሁለት መልክ ይይዛል።
የመጀመሪያው በእያንዳንዱ የጎሣ ክፍል ውስጥ ፖለቲካዊ ይዘት ያለው ፉክክርና ግብግብ ጥላቻን ይወልድና ወደ አካላዊ ግጭትም ያመራል። ጎሠኝነት ከዘረኝነት ጋር የተዛመደ እንደመሆኑም የጎሠኝነት ስሜት የሚመነጨውና የሚጎለብተው እያንዳንዱ ሰው የኔ የሚለው የዘር ሀረግ ወይም ጎሣው ከሌሎች ሰዎች ዘር ወይም ጎሣ የተሻለ ወይም የበለጠ ነው ብሎ ማሰብ ሲጀምር ነው። ይህ አይነቱ አስተሳሰብም ሰዎች ሁሉ በፈጣሪያቸው ፊት እኩል እንደሆኑ የሚገልጸውን ኃይማኖታዊ አስተሳሰብ የሚቃረንና ይህንኑ መሰረት በማድረግም “ሰዎች ሁሉ እኩል ክብርና መብቶች ይዘው ነፃ ሆነው ተፈጥረዋል። የማሰብና የማመዛዘን ችሎታ በተፈጥሮ ስለታደሉ እርስ በርሳቸው በወንድማማችነት መንፈስ ሊተያዩ ይገባል።” በማለት የሚደነግገውን የሰብአዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳን አንቀጽ 1 የሚጥስ ነው።
ሁለተኛው ግጭት ደግሞ በእያንዳንዱ የጎሣ ቡድን ወስጥ የሚፈጠረው የግለኝነትና ጤናማ ያልሆነ የመበላለጥ ስሜት ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች አንድ አድርገው ይዘው ያቆዩትን ታሪካዊ እና ሌሎች አገራዊ መገለጫዎች ይንዳል፤ እንዲሁም የጋራ ጥቅምን ማስከበሪያ የሆነውን ሕገ-መንግስታዊ ሥርዓትን ያናጋል። አልፎ ተርፎም አገርን እስከማፍረስ የሚዘልቅ ችግርን ያስከትላል። በዚህ አይነቱ ችግር ምክንያት በርካታ ትላልቅ አገሮችች ፈርሰው በጎሠኞች ደሴቶች ተቀይረዋል። የጎሠኝነት ስሜት በጠነከረና አብጦ በወጣ ቁጥር አገራዊ ስሜት ይከስማል፣ የአብሮነት ታሪክ ይዘነጋል፣ ጠባብነትና ጎጠኝነት ይነግሳሉ። እዚህ ደረጃ ላይ የደረሰ ማኅበረሰብ በበቀልና በጥላቻ ስሜት ተወጥሮ ስለሚቆይ የእልቂት አፋፍ ላይ ነው የሚቆየው። ተያይዞ ለመጥፋትና ቁልቁል መቀመቅ ለመውረድ ትንሽ ነገር ይበቃዋል። በሩዋንዳና በሌሎች የአለማችን ክፍሎች አስከፊ በሆነ መልኩ የተፈጸሙት የዘር ማጥፋት ወንጀሎች ምንጫቸው ይሄው ነው።
በአለም አቀፍ ደረጃ የተደረጉ አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ጎሠኝነትን ወይም የጎሣ-ብሔረተኝነትን መነሻ ያደረጉ ግጭቶች ባህሪያቸው እና መገለጫቸው የተለያየ ነው። ጥቂቶቹን ለመዳሰስ ያህል፤ የፖለቲካ ሥልጣንን በማዕከላዊነት በያዘ የኅብረተሰብ ክፍል እና ከፖለቲካ ምህዳሩ ተገልሎ የዳር ተመልካች እንዲሆን በተደረገ የኅብረተሰብ ክፍል ማካከል ያለውን ቅራኔ መሰረት ያደረገው የጎሣ ግጭት አንዱና በዋነኝነት የሚጠቀሰው ነው። ሁለተኛው ደግሞ በብሄር ምንጫቸው ምክንያት ወይም በቆዳ ቀለማቸው ወይም በሚከተሉት እምነት ወይም በኃይማኖታቸው ወይም በሌሎች ምክንያቶች የተነሳ በእኩልነት የመኖር መብታቸውን እና መሰረታው መብቶቻቸውን በተነፈጉ እና ጥላቻን መሰረት ላደረገ መድልዎ እና ጥቃት የተጋለጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚያነሱትን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ የእኩልነት ጥያቄዎችን ተከትሎ የሚቀሰቀሰው የጎሣ ግጭት ነው። ሦስተኛው ደግሞ፤ በሚኖሩበት ማኅበረሰብ ውስጥ ተገቢውን የፖለቲካ እና ኢኮኖሚያዊ ድርሻ ተነፍገናል ወይም የሚገባንንን ያህል አላገኘንም የሚል ጥያቄን መነሻ በማድረግ ከሌላው ማኅበረሰብ ተገንጥዮ የራሴን አገር እና ግዛት እመሰርታለው የሚሉ ኃይሎች የሚያነሱትን ጥያቄ መነሻ አድርጎ ከሌላው የኅብረተሰብ ክፍል ጋር የሚደረገ ግጭት ነው። አራተኛው የጎሣ ግጭት ደግሞ በአንድ ግዛት ውስጥ ሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ የጎሣ ቡድኖች መካከል የኢኮኖሚና የፖለቲካውን የበላይነት ለመቆናጣጠርና የማዕከላዊውን መንግሥት ሥልጣን በበላይነት ለመቆጣጠር የሚደረጉ ፉክክሮችን ተከትሎ በሚፈጠር አለመግባባት የሚቀሰቀስ ግጭት ነው።
ከላይ የተጠቀሱት የጎሣ ግጭቶችና መንሰዔዎቻቸው በግልጽ እንዲሚያሳዩት ጎሠኝነትን መሠረት ያደረጉ የማንነት መገለጫዎች የፖለቲካ ግብ ማሳኪያ ሲሆኑ መድረሻቸው ጥላቻና ሌሎችን ‘የእኛ ጎሣ አካል አይደሉም’ የሚሉዋቸውን የኅብረተሰብ ክፍሎች ማግለልና ሲከፋም ዘራቸውን ከምድረ-ገጽ ለማጥፋት እስከ መሞከር ይዘልቃል። ይህ ችግር የተከሰተው እንደ ኢትዮጵያ ባለ እጅግ በተሰበጣጠረ ማኅበረሰብ ውስጥ ሲሆን የዘረኝነት መርዙ በብዙ መንገዶች ሊንጸባረቃ ይችላል። በልማት እንቅሳቅሴ፣ በትምህርት ዘርፍ፣ በኢኮኖሚና የንግድ ዘርፍ፣ በመሬት አጠቃቀም ፖሊሲ፣ በግብር አከፋፈል ሥርዓት፤ እንዲሁም በተለያዩ አስተዳደራዊ ዘርፎች ሁሉ የጎሠኝነቱ ስሜትና ውጤቱ በግልጽ ይስተዋላል። ለምሳሌ በፊሊጲንስ ቅጥ አጥቶ የነበረው ጎሠኝነት በአገሪቱ የኃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል አጠቃቀም ላይ ጭምር በግልጽ ይስተዋል ነበር። በማሌዢያ እና በታንዛኒያ ደግሞ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት አቅርቦት ላይ የጎሣ መድልዎ አፍጥጦ ይታይ ነበር። በሌሎች አገሮችም የተለያዩ መገለጫዎች ያላቸው ጎሠኝነትን መሰረት ያደረጉ ክፍፍሎችና መድልዎች ተስተውለዋል፤ አስከፊ ግጭቶችንም አስከትለዋል።
በጎሣ የሚደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች መነሻቸው ከሁለት ክስተቶች የሚመነጭ ነው። የመጀመሪያው ውስጣዊ ምክንያት ነው። ይኽውም በእያንዳንዱ የጎሣ ክፍል ውስጥ ካለው ማኅበረሰብ ከራሱ የሚመነጭ ነው። የአንድ ጎሣ አባላት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፓለቲካዊ ጥቅማቸውን በተሻለ ሁኔታ ለማስጠበቅ ሲሉ በፖለቲካ የሚደራጁበት ሁኔታ ነው። ሁለተኛው ደግሞ ውጫዊ ምክንያት ነው። ይኽውም የአንድ ጎሣ አባላት በተደጋጋሚ ከአንድ ወይም ከሌሎች ጎሣዎች ጥቃት ሲደርስባቸው፣ ከሌሎች ጎሣዎች በተለየ መልኩ መድሎና መገለል ሲደርስባቸው፣ ከኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥቅሞችና ተሳትፎዎች እንዲገለሉ ሲደረግ እና በሌሎች ተመሳሳይ ምክንያቶች አደጋ ሲጋረጥባቸው ይህን መሰሉን ጥቃት ለመከላከል በሚል አካባቢው በፈጠረባቸው አስገዳጅ ሁኔታ በመነሳት የጎሣቸውን አባላት ጥቅም እና ደኅንነት ለማስጠበቅ በማሰብ በፖለቲካ የሚደራጁበት ሁኔታ ነው። በመሆኑም ጎሣን መሰረት አድርገው የሚመሰረቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ የሚያገኙት እንወክለዋልን ከሚሉት የኅብረተሰብ ክፍል ብቻ ስለሆነ የሚታገሉትም ሆነ ሥልጣን ሲቆናጠጡ ቅድሚያ ተጠቃሚ የሚያደርጉት የደገፋቸውን እና የሚወክሉትን የጎሣ ክፍል ብቻ ነው። ጎሣን መሰረት ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከጠቅላላው ማኅበረሰብ ጥቅም አንፃር እጅግ ጠባብ የሆነ የቡድን ፍላጎትና አጀንዳን ነው የፖለቲካ ግብ አድርገው የሚነሱት። እነዚህ ኃይሎች የፖለቲካውን ሥልጣን በተቆናጠጡበት ሥፍራ ሁሉ ታዲያ የእኛ ከሚሉት ጎሣ ክፍል በተነጻጻሪ ባለው ቀሪው የኅብረተሰብ ክፍል መካከል ግልጽ የሆነ የጥቅምና የመብት መበላለጥን ይፈጥራሉ። ይህ ሁኔታም እያደር ቅራኔንና ጥላቻን ያራባል።
የጎሠኝነት ስሜት አብጦ በወጣበትና ድርጅታዊ ቅርጽ ይዞ በጎለበተበት አገር ሁሉ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችና አስተሳሰቦች የሚመዘኑትና የሚመነዘሩት በእያንዳንዱ ጎሣ መስፈርት ነው። የፖለቲካ ፓርቲዎችም የሚደራጁትና የሚታገሉት ጎሣዎችን መሰረት በማድረግ ነው። የጎሠኝነት ስሜት ገኖ በሚታይበት ሥፍራ ሁሉ ሰብአዊ መብቶችን ችላ ማለት፣ አሰቃቂ የሆኑ የመብት ጥሰቶችን በሌሎች ላይ መፈጸምና ሰዎችን በፍርሃትና በከፋ ችግር ውስጥ መጣል የተለመዱ ተግባራት ናቸው። ይህ አይነቱ ሁኔታ እጅግ በተከፋፈለ ማኅበረሰብ ውስጥ ሲከሰትና ፓርቲዎችም የጎሣን መስመር ተከትለው መደራጀት ሲጀምሩ ጠንካራ የፖለቲካ ተፎካካሪ ኃይሎች መሆናቸው ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል። ምክንያቱም ድጋፍ የሚያገኙት ከሚወክሉት ጎሣ አባላት ብቻ ስለሆነ። ከዚህም ባሻገር ለጠቅላላው ሕዝብ ጥቅም የሚቆሙ ብሔራዊ የፖለቲካ ኃይሎች እንዲዳከከሙ እና እንዲጠፉም ምክንያት ይሆናል። ለዚህም ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ፣ ኢስያ እና ካረቢያን አገራት ዛሬ የሚገኙበትን ሁኔታ ማጤን በቂ ነው። በዚህ መጠነኛ የዳሰሳ ጽሁፍ ውስጥ የጎሠኝነተን አስተሳሰብ፣ መሰረታዊ እና ታሪካው ምንጭ እንዲሁም በጎሣ ግጭቶች ዙሪያ የሚነሱ የተለያዩ ሃሳቦችን ሁሉ ለማካተትም ሆነ በመጠኑም እንኳን ለመቃኘት አይቻልም። እራሱን የቻለ ሰፊ ጥናትና ምርምር የሚጠይቅ ስለሆነ ይህ ዳሰሳ ለዚህ ጽሁፍ ቀጣይ ክፍሎች እንደ መንደርደሪያ ተደርጎ እንዲወሰድ ለማሳሰብ እወዳለሁ።

በቀጣዩ ክፍል እስከምንገናኝ በቸር እንሰንብት።
ያሬድ ኃይለማርያም

http://humanrightsinethiopia.wordpress.com/

ኢህአዴግ 42 ዓመት መግዛትን አስቧል?

$
0
0

ሳሙኤል ተወልደ በርሔ/ሃርስታድ ኖርዌይ/

ሳሙኤል ተወልደ በርሔ/ሃርስታድ ኖርዌይ

ሳሙኤል ተወልደ በርሔ/ሃርስታድ ኖርዌይ


ዛሬ በዓለማችን ላይ በርካታ የሆኑ ለውጦች ተፈጥረዋል፡፡ ህዝብ ይመረጣል፣ ህዝብ ያወርዳል፡፡ ሥልጣን እርስት አይደለም፡፡ የዚህ አይነቱነገር ደግሞ በከፍተኛ ሁኔታ እየሰላ መጥቷል፡፡ ልክ እንደዚህ አይነቱ ሁኔታ በሚታይበት ሁኔታ ደግሞ በተቀራኒው ሥልጣንን የሙጥኝ ብለው ዘላለማዊ አገዛዝን ለመግዛት የሚያስቡ መኖራቸው አልቀረም፡፡ የጠ/ሚ/ር ኃ/ማርያም ደሳለኝ አማካሪ በመሆን የተሾሙ አቶ በረከት ስምኦን ባለፈው ሰሞን “ኢህአዴግ የጀመረውን የልማት ሥራ ለመጀመር በቀጣይነት 42 ወይም 45 ዓመታት ያፈጅበታል” ሲሉ ገለጹ፡፡ ይህ የአቶ በረከት ስምኦን ንግግር ምናልባትም በምርጫ ዋዜማ ሠሞን የተነገረ ከመሆኑ አንፃር ብዙ ነገር እንዲታሰብ ያደርጋል፡፡ ሁልጊዜም ቢሆን ምርጫ በደረሰ ቁጥር በኢህአዴግ ውስጥ ስልት አለ፡፡ የአሸናፊነት መንፈስን በማሰብ ሳይሆን፣ ሁልጊዜም ቢሆን ተሸናፊነትን እያሰበ ይወጣል፡፡ በዚህ ወቅት ደግሞ የተለያዩ ሕጐችንና ደንቦችን በማውጣት ምርጫው ሕጋዊ ወይም ተገቢ ያልሆነ መንፈስ እንዳይኖረው ያደርጋል፡፡ ታዲያ አቶ በረከት ስምኦን እንደሚሉት ሆነ ወይም በቀጥታ ትርጓሜው ሳይሆን፣ በኢህአዴግኛው ትርጓሜው ‹‹በቀጣይም እቺን አገር የምንስተናገደው እኛ ነን›› የሚል መንፈስ ያለው ነው፡፡

ኢህአዴግ በሃገሪቱ በሶስት አይነት ዘርፍ የልማት ሥራ ጀምሯል፡፡ የህዳሴው ግድብ፣ የባቡር ሃዲድ ዝርጋታ እና በንግድ፡፡ እነዚህ ሶስት ሥራዎች ግን ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠይቁ ከመሆናቸው አንፃር በተፈለገው መንገድ ተፋጥነው ሊያልቁ የሚችሉ አይደሉም፡፡ ይህ አለመሆኑ ደግሞ ምናልባትም ኢህአዴግ እንደ አቶ በረከት ስምኦን አባባል በፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ለመጠቀም ያስቀመጠውም የሚመስልበት ሁኔታ አለ፡፡ የኢህአዴግ ያለፉት 22 ዓመታት ጉዞ ምናልባትም እርሱ ‹‹ዕድገት›› ይበለው እንጂ፣ በብዙ መልኩ ውድቀቶችና ድህነቶች የበዙበት ነው፡፡

የ11 በመቶ ዕድገት ለሌሎች ሳይሆን፣ ለኢህአዴግ ብቻ የሚገለጽ ነው፡፡ የህንጻ መብዛት ‹‹የሃገር ዕድገት ነው›› የሚለው ኢህአዴግ እንጂ፣ ከሚሠሩት ፎቆች ስር በርካታዎች ማደሪያ አልባ መኝታ ማድረጋቸውን በየቀኑ የሚታይ አሣዛኝ ገልጻ ነው፡፡ የሃገር ለውጥ የህዝብ ለውጥ ነው፡፡ ማንም ሰው ቢሆን፣ የደሞዝ ጭማሪ በሚደረግበት ጊዜ በራሱ ላይ የተወሰነ ለውጥ ይታይበታል፡፡ የሃገር ዕድገትም 11 በመቶ ከደረሰ፣ ህዝቡ በራሱ ላይ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል ወይም አንዱ በአንዱ ላይ የሚመለከተውም ለውጥ ይኖራል ማለት ነው፡፡ በነዚህ 22 ዓመታት ግን የዚህ አይነቱን ነገር ለማየት አልተቻለም፡፡ ያ ማለት ዕድገቱ የስም ነው ማለት ነው፡፡ የፎቅ ግንባታዎች እና መንገዶች ተሰርተዋል፡፡ ያ ማለት ግን ሃገራዊ ለመፍጠር አንድ ምሣሌ ልንገራችሁ፡፡ ለልጅቱ 14 ዓመቷ ነው፡፡ የሰውነትዋ ግዝፈት ደግሞ 20 ዓመት ዕድሜ ክልል ውስጥ ያለች አስመስሏታል፡፡ አንድ ሰው ደግሞ ልጇቷን ለጋብቻ ጠየቀ፡፡ የ14 ዓመት ልጅ መሆኑዋን የሚያውቀው አባት፣ ‹‹አይ ማግባት አትችልም›› አለ፡፡ ምክንያቱም ገና 14 ዓመቷ ስለሆነ ለጋብቻ የፈለጓት ወገኖች 14 ዓመት የሚለውን ነገር ፈጽሞ ሊቀበሉ አልፈቀዱም፤ አልተዋጠላቸውምም፡፡ የልጅቱዋን የሰውነት ግዝፈት በመመልከት “ኢህአዴግ እየነገረን ያለው ዕድገትም ቢሆን የዚህ አይነት ምሳሌ ያለው ነው፡፡ እንደሚታወቀው ዛሬ ሙስና የስርዓቱ መለያ ሆኗል፡፡ በርካቶች በአንድ ጀምበር የፀሐይ ፍጥነት በሚያስደንቅ መልኩ ተቀይረው ሃብታም ሲሆኑ ይታያል፡፡ የዚህ የሃብት ምንጭ ግን አይታወቅም፤ ምክንያቱም ሥራው ሙስና ነው፡፡

አቶ በረከት

አቶ በረከት


ይህ የሙስና ተግባር ደግሞ በተለይ በአሁን ሰዓት ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት ውስጥ ሳይቀር የገባበት ሁኔታ ታይቷል፡፡ ስርዓቱ ለይምሰል ብቻ እንደ ህዝብ ገፀ-በረከት ከዝቅተኞቻችን ተሿሚዎች መካከል ሙሰኞች እያለ ለህዝብ ቢያጋልጥም ዋናዎቹን ግን ለመንካት ታስቦ አይደለም፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት ደግሞ ምንም ሳይሆን አንዱ ከተነካ ሌሎችንም ይዞት የሚሄድበት የተሳሰረ የሙስና ሰንሰለት ስላለ ነው፡፡ ሌላው ነገር እንዳይነካው ሲጥር የሙስና ተግባር እየተስፋፋና አሁን አሁን ይበልጥ ወደ ሕጋዊነት እየተቀየረ የመጣበት ሁኔታ በመሰማት ላይ ይገኛል፡፡ በአንድ ሃገር ላይ ትልቁ ችግር የመንግስት ሹማምንት ሙሰኛ መሆን ነው፡፡ የሙሰኞች ቁጥር እየሰፋ በመጣ ቁጥር ተጐጂ የሚሆነውና አደጋ ላይ የሚወድቀው ማንም ሳይሆን ህዝቡ ነው፡፡ ኢህአዴግ ይህንን የሙስና ተግባር ፈጽሞ ሊያጠፋው አልቻለም፡፡ ሲታይም እንዲጠፋ የሚፈልግም አይመስልም፡፡ ባለፉት ዓመታት ‹‹የባለሥልጣናት ሃብት ምዝገባ›› በሚል አንድ ምዝገባ ተከናውኖ ነበር፡፡ ይህ ምዝገባ በቅርቡ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ ቢገለጽም፣ አቶ መለስ ከመሞቱ አስቀድሞ የተደረገው ምዝገባ ለህዝብ ይፋ ሊደረግ አልተቻለም፡፡ ምክንያቱም ህዝቡ የሚያየው ሃብትና የሚገለጸው ነገር ፈጽሞ አይገናኝም፡፡ ህዝቡ የቱ ድርጅት የየትኛው ባለሥልጣን እንደሆነ አብጠርጥሮ ያውቃል፡፡ ስለዚህ የዛኔም ቢሆን ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ከዓለም ባንክ የተቸረውን ገንዘብ ለማግኘት ሲል ይህንና ድራማ ይተውን እንጂ፣ የባለሥልጣናቱን ሃብት ለህዝብ ይፋ ያደርጋል ተብሎ ግን አይጠበቅም፡፡ ከዛ ባለፈ ደግሞ በሃገሪቱ የትምህርት ጥራትና የተማረ ኃይልን የምንመለከተው ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ ነው፡፡ የትምህርቱ ጥራት ከመውረዱ የተነሳ ዲግሪው የከበዳቸው ወይም በ‹‹በዲግሪው›› የሚያምኑ ተማሪዎች በዝተዋል፡፡ ኢህአዴግ የትምህርት ጊዜውን ዓመት ከመቀነሱም በላይ በገፍ ተማሪዎች ያስመርቃል፣ ወደ ስር ሲገባ ግን ፈጽሞ የማይመጣጠን እየሆነ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ትውልዱን እየገደለና እያወረደው መጥቷል፡፡ ተስፋና ለሃገርና ለወገን የሚጠቅም ተግባር የሚፈጽም ወጣት ሳይሆን፣ቀድሞተስፋ የቆረጠ ሲመረቅ ለድንጋይ ጠረባ /ኮብልስቶን/ የተዘጋጀ መሆኑን አውቆ ሃሞቱ የፈሰሰ ትውልድ ለዚህች ሃገር እያስረከበ ይገኛል፡፡
ይህ ብቻም አይደለም፡፡ በእውነቱ ከሆነ የየትኛው ባለሥልጣን ልጅ ነው በሃገር ውስጥ ወይም እነርሱ በወጣ ፖሊሲ የሚማረው? የእነርሱ ልጆቻች በአውሮፓና በአሜሪካ እያስተማሩ ሌላውን እዚህ ሃገር ውስጥ እየታሸ ለአራትና አምስት ዓመት ተምሮ ዕውቀቱን በድንጋይ ጠረባ ላይ እንዲያፈሰው እየተደረገ እንዴት የተማረ ኃይል በዚህች ሃገር ውስጥ ለራሱ ይቻላል፡፡ የህዝቡ እና የጤና ላይም ቢሆን ይበልጥ የወረደ የተለየ ለውጥ የታየበት አይደለም፡፡

eprdfኢህአዴግ ባለፉት 22 ዓመታት ቆይታው የመራው ነገር ብዙም ሚዛናዊ የሆነ ነገር አይደለም፡፡ ፖሊሲው በፈጠረው ችግር በርካቶች ከሃገር እንዲሰደዱ አድርጓል፡፡ ዛሬ በርካታዎች የሚሰደዱት የሃገሪቱ ኢኮኖሚ በመውረዱ፣ ሥራ አጥነት፣ ከዛ ባለፈ ደግሞ ፖለቲካው የሚፈጥረው ጫና ከሚፈጥርባቸው አደጋ ጋር ተያይዞ ነው፡፡ በዚህ ስርዓት የመጣ ለውጥ የለም፡፡ እስቲ ሌሎችም ጐልተው ዕድሉን በማግኘት ይሰሩ ቢባል፣ ምርጫው ግን ፈጽሞ ነፃ ሊሆን አልቻለም፡፡ “እኛ ታግለን ነው የገባነው፤ እኛ ብቻ ልንመራ ይገባል” የሚለው አካሄድ የኢህአዴግ መለያው ሆኗል፡፡ ትግል ለሕዝቦች ነፃነት እኩልነት እንጂ፣ ለአንድ ወገን ብቻ ዘላለማዊ ሥልጣን የሚሰጥ አይደለም፡፡ በፈሰሰው ደምና በተከፈለው መስዋዕትነት ሃገር ስታድግ፣ ህዝቡ ዲሞክራሲያዊ መብቱ ሲከበር ደስ ይላል፡፡ ይሄ ግን ኢህአዴግ ጋ አይሰራም፡፡ ቢቻል ዘላለማዊ አገዛዝን በመያዝ ወይም ‹‹ልንመራ የሚገባን እኛ ነን›› የሚል ፖሊስ ይዟል፡፡ ይህ ደግሞ ሊሆን የሚችል አይደለም፡፡ ዛሬ ዓለም ተቀይሯል፤ ምናልባት ኢትዮጵያን ጨምሮ ውስን የአፍሪካ ሃገራት ላይ የአንድ ፓርቲና ወገን በበላይነት ሰፍኖ ሊታይ ይቻላል፡፡ ከዛ ባለው ግን ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለማድረግ የሥልጣን ሽግግር እያየን ነው፡፡ አቶ በረከት ባለፈው ሰሞን የነገሩን “የዘፈንዳር ዳሩ ነው” እንደሚለው፣ ተረት አሁንም በሥልጣን ላይ ለመቆየት እንደሚፈልጉና ይህንን ለማድረግ ደግሞ የተጀመሩትን የልማት ሥራዎች ‹‹በቀብድነት›› በማስገባት እንደው ነገሩን ለማስመሰል ጥረዋል፡፡ ኢህአዴግ ይህን አያደርግም አይባልም፡፡ ባቀጣይነት የሃገሪቱ ውድቀት እንደሚቀጥል መዘንጋት የለበትም፡፡

ሞት የስብሐት ነጋ በርን እያንኳኳ ነው (ሁኔ አቢሲኒያዊ ከፒተርቦሮው ዩ.ኬ)

$
0
0

አቶ ስብሃትን ጠጋ ብለው የሚያውቁት ሰዎች “አቦይ ብላችሁ አትጥሩት። አባታዊ አንደበትና ምግባር የለውም እርሱን አቦይ ማለት ትግራይ የሽማግሌ መሀን እንደሆነች መቁጠር ነው” ይሉታል፡፡

ሰውዬው ስብሐት ነጋ የህወሓትን አመሰራረት ቅድመ ታሪክ ለሚያውቅ ሰው ምን ያህል ተንኮለኛ እና በዘር ልክፍት የተለከፈ እንደሆነ ግልጽ ይሆንለታል፡፡ በ1963 ዓ.ም እንደተመሰረተ የሚነገርለት ማገብት (ማህበር ገስገስቲ ብሔረ ትግራይ) የተመሰረተው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የትግራይ ተወላጅ ተማሪዎች ነበር፡፡ የማህበሩ ተልእኮም የተለያዩ የበጐ አድራጐት ስራዎችን በክረምት ወደ ትግራይ በመሄድ ማከናወን የሚል ነበር፡፡ በሂደት ሙሉ በሙሉ ወደ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በመቀየር ለተሐህት/ህወሓት መመስረት መሰረት ሆነ ለዚህ ዓላማ የማስቀየር ስራ ትልቁን አስተዋፅኦ ካደረጉት መካከል ደግሞ ዛሬ ታሞ የሚማቅቀው ስብሐት ነጋ አንዱ ነው፡፡
ስብሐት ነጋ የህወሀትን መስመር እና ዓላማ መሀንዲስ ከመሆንም አልፎ እስከዛሬ ለብዙ ሰዎች ምስጢር በሆነ መልኩ መለስ ዜናዊንም ወደ ህወሀት ሊቀመንበርነት ብሎም የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስተር ያደረገ እና በህወሀት ክፍፍል ወቅትም ትልቅ ሚና ከነበራቸው ቀደምት የህወሀት ታጋዮች አንዱ ነው፡፡

ለባለፉት 23 ዓመታት የኢትዮጵያን ህዝብ ከጀርባ ሆነው ሲያንቀጠቅጥ የነበረው አይተ ስብሐት ነጋ እርሱም ተራው ደርሶ ቤልጅየም ብራሰልስ በሚገኘው ሴንት ሚካኤል ሆስፒታል Hôpital Saint Michel – (Brussels) መመላስ ከጀመረ 11 ዓመታት እንደሞላው የውስጥ አዋቂዎች ቢገልፁም የበሽታው አይነትና የሰውዬው የጤንነት ሁኔታ እስካሁን ድረስ ከቅርብ ሰዎች ውጪ ሳይወጣ ቀርቷል ሆኖም የህወሀት የውስጥ ሹኩቻን ተከትሎ ሚስጥሮ እያፈተለኩ መውጣታቸውን ቀጥለው ዛሬ ስለ ስብሀት ነጋ ጤንነት በተመለከተ ለዚህ ጽሁፍ ፀሀፊ አፈትላኪ መልዕክት ደርሷል፡፡

ከታማኝ ምንጮች የተገኙት መረጃዎች እንደሚያሳዩት ሰውዬው ማለትም ስብሐት ነጋ brainstem glioma በተባለ የካንሰር አይነት መጠቃቱን ገልፀዋል፡፡ ይህ የካንሰር አይነት በብዛት በህፃናት ላይ የሚታይ ሲሆን በአዋቂዎች ዘንድ ግን በዚህ የካንሰር ዓይነት የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከ100,000 አንድ እንደሆነ የሳይንስ ማስረጃዎች ያሳያሉ፡፡

Brainstem glioma ስለተባለው የካንሰር አይነት መንስዔ እስካሁን የህክምና ባለሙያዎች ምንም ያሉት ነገር ባይኖርም በካንሰሩ የተጠቃ ሰው ግን ከፍተኛ የሆነ የራስ ህመም፣ ራስን የመቆጣጠር እና የማስመለስ ችግር እንደሚያጋጥመው ያስረዳሉ፡፡

በዚህ ካንሰር ተጠቅተው ወደ ህክምና ከሄዱ ሰዎች መካከል 37% የመኖሪያ እድሜያቸው ቢበዛ ዓንድ ዓመት 20% ያህሉ ሁለት ዓመት 13% ቢበዛ ቢበዛ ከሶስት አመት በላይ በህይወት የመኖር እድላቸው አነስተኛ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

ከህወሀት አፈትልኮ የወጣው መረጃ እንደሚያሳየው ስብሐት ነጋ ባለፉት 11 ዓመታት ቤልጂየም ሲመላለስ የነበረው በዚሁ የካንሰር ምክንያት እንዳልነበረ እና የዚህ አይነት የካንሰር ተጠቂ እንደሆነ የተነገረው ፌብራዋሪ 9 እለተ እሁድ ቀን እንደነበር ጨምረው ገልፀዋል፡፡
Sbehat_Nega
የአቶ ስብሐት ነጋን መታመም ተከትሎ በሰውዬው ላይ በየዕለቱ የተለያየ ባህሪ እንደሚመለከቱ ገልፀው በተደጋጋሚ ከተለያዩ ስብሰባዎች ላይ አቋርጠው እየሄዱ እንደሚገኙ አክለው ገልፀዋል፡፡

በጦርነቱ ዘመን የትግራይ ህዝብ እጅግ የከፋ ድርቅና ረሀብ ሲፈራረቅበት፤ ከመሀል አገር የእርዳታ እህል እንዳይደርሰው መንገድ በመዝጋት፤ እነሱ በተቆጣጠሩት አካባቢና ባልተቆጣጠሩትም አካባቢ “እኛ ነን ለህዝባችን ረድኤት ድርጅቶች የሚያቀርቡትን እርዳታ ማደል ያለብን” ብለው የተባበሩት መንግስታትን ግራ አጋብተው ለረሀብተኛው እንዲያከፋፍሉ መድሀኒትና ምግብ ይሰጣቸው የነበሩ ሲሆን ያንን በብዙ ሚሊዮን የሚገመት የእርዳታ እህልና ቁሳቁስ ከአረብ ነጋዴዎች ጋር በመመሳጠር በቀጥታ ባህር እያሻገሩ በመሸጥ፤ በኩንታሎች አሸዋ እየሞሉ ለጋሾችን በማታለል እንዲገዙአቸው በማድረግ፤ በሚሊዮን ዶላር ሲንበሸበሹ፤ የጦር መሳሪያ ሲሸምቱ፤ የትግራይ ህዝብ እንደቅጠል ይረግፍ ነበር። እነሱ በየጫካው ከሰራዊቱ እየተሸሸጉ አረቄ ጠግበው ከውሽሞቻቸው ጋር ከበሮ እየደለቁ እየጨፈሩ ይዳሩ እንደነበር ህወሀትን ጥለው የኮበለሉ የቀድሞ አባላቶች የሚገልፁ ሲሆን ለእነዚህ ሁሉ ግፍ እና በደል መፈፀም ከፍተኛ ሚና የነበራቸው እኚሁ የካንሰር ተጠቂ ነበሩ፡፡

ሞት ፍትሃዊ ነው በቅርቡ እንኳን አፈ ቀላጤ መለስ ዜናዊን ከህወሀት አለማየው አቶምሳን ከኦህዴድ ( ኦህዴድ ብዬ ስጠራው የዋሸው ይመስለኛል) የወሰደ ሲሆን አሁን አፉን ከፍቶ ከስብሐት ነጋ ደጃፍ ደርሷል ስብሀት ነጋም ሞትን ወደ ቤቱ ላለማስገባት ከአዲስ አበባ ወደ ብራሰልስ በየዕለቱ እየተመላለሰ ይገኛል ግና ሞትን ሸሽቶ እስከመቼ ሊደበቅ እስከ አንድ ወር ወይስ?

የአባ መላ (ብርሃኑ ዳምጤ) መገለባበጥና ኢሳት

$
0
0

ከእንደልቡ/ዳግም (ከቫንኮቨር፣ ካናዳ)

አባ መላ ማን ነው?

በቅጽል ስሙ “አባ መላ” በእውነተኛ ስሙ ደግሞ ብርሃኑ ዳምጤ ተብሎ ይጠራል፣ በ60ዎቹ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ አዛውንት ነው (ምንም እንኳ ስራው እንደ እድሜው ባይሆንም)። ፓልቶክ የሚባለውን የማህበራዊ መገናኛ መድረክ በመጠቀም በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዲስኩር በማሰማት ይታወቃል። በወጣትነቱ ኢህአፓ ውስጥ ነበር የሚባለው ብርሃኑ ዳምጤ ወዲያውም የኢህአፓን መዳከም አይቶ ወደ ደርግ ቡድን መቀላቀሉን የሚያውቁት ይናገራሉ። በወቅቱ አብረውት በኢህአፓ ውስጥ ይሳተፉ የነበሩ ወጣቶችን ለደርግ በእጅ መንሻ መልክ አሳልፎ ሳይሰጥ እንዳልቀረ በደርግ ካድሬነት ቆይታው የሚያውቁት ይጠረጥራሉ አንዳንዶች ደግሞ አፋቸውን ሞልተው ይናገሩታል።
aba-mela-esat
ብርሃኑ ዳምጤ ከደርግ መውደቅ በኋላ በስደቱ ዓለም (ዳያስፖራ) ፖለቲካ መድረክ ብቅ ያለው በምርጫ 97 ወቅት የዝነኛውን ቅንጅት ማልያ ለብሶ ነበር። ይሁንና በስልጣን ላይ ያለው የህወሃት/ወያኔ መንግስት ምርጫውን አጭበርብሮ፣ የምርጫውን መጭበርበር የተቃወሙትን በገፍ በአደባባይ በጥይት ደብድቦ፣ ህዝቡ የመረጣቸውን የቅንጅት አመራሮች፣ ጋዜጠኞችና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን ጨመሮ ከ50 ሺህ በላይ ባብዛኛው ወጣቶችን አስሮና በየጦር ካምፖቹ አጉሮ በአምባገነንነቱ ለመቀጠል ሲወስን ብርሃኑ ዳምጤም ባፋጣኝ የቅንጅትን ማልያ አውልቆ የህወሃት/ኢህአዴግን ማልያ ለብሶ ቁጭ አለ።

ሰሞኑን ደግሞ ብርሃኑ ዳምጤ አስደናቂ መገለባበጥን ፈጽሞ የህዝብን አይን አስበልጥጧል። እነዚህ ብርሃኑ ዳምጤ (አባ መላ) ሰሞኑን የሚፈጽማቸው መገለባበጦች በ1960ዎቹ እና 70ዎቹ ከነበሩት የመገለባበጥ ትሪኢቶቹ ለየት የሚያደርጋቸው ነገር ቢኖር አሁን መገለባበጡን የሚፈጽመው በቀጥታ ስርጭት ወቅት (በፓልቶክ) መሆኑና ጉዳዮን በመሪ ዜና መልክ የሚዘግብለት የቴሌቪዥን ጣብያ “ኢሳትን” ማግኘቱ ነው።

ብርሃኑ ዳምጤ ከጥቂት ወራቶች በፊት ነበር የተሰለፈበት የህወሃት/ኢህአዴግ ጎራ በተለይም ከወያኔው ቁንጮ መለስ ዜናዊ ሞት በኋላ እየተዳከመ መምጣትን አይቶና ገምቶ ወያኔዎችን “አፍንጫችሁን ላሱ፣ እኔ ከአሁን ብኋላ የድሮው አባ መላ አይደለሁም፣ እንዲያውም ጉዳችሁን አዝረጠርጣለሁ…” በማለት ፉከራ ቢጤ አሰምቶ የዲሞክራሲና የነጻነት ታጋዮችን ጎራ መቀላቀሉን ያበሰረው።

መንፈቅ እንኳ ሳይሞላ አባ መላ በመጣበት አይነት መንገድ ተመልሶ ህወሃት/ኢህአዴግን ለማገልገል መወሰኑን ይፋ አደርጓል። ለሱ እምብዛም አዲስ ያልሆነውን የክህደት ቁልቁለትም ዳግም ተያይዞታል።

አባ መላ፣ ኢሳትና ዳያስፖራው

የኢሳት ጋዜጠኞች፣ አንዳንድ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና የተቃዋሚ ፖለቲከኞችም ጭምር ይህ አባ መላ የሚባለውን ቦታ እየቀያየረ ይሚጫወት ዝቅተኛ ካድሬ ከሚገባው በላይ ቦታ ሰጥተውት እንደነበር እገምታለሁ፣ በውጤቱም ተከታዮቻቸውን ያሳሳቱና ያዘናጉ ይመስለኛል። ይህንን ጉዳይ ማንሳቴ “ብዬ ነበር” ለማለት ሳይሆን ይልቁኑም ይህ ክስተት እንደ መማሪያ ሆኖ እንዲያልፍ በመፈልጌ መሆኑን አባብያን እንዲረዱልኝ እፈልጋለሁ።

እንደ አባ መላ አይነቱ ቀደም ሲል በተደጋጋሚ የመገለባበጥ ብቃቱን ያሳየ ወለፈንዴ ተቃዋሚ ጎራ ገብቻለሁ ሲል አያያዛችን ጥንቃቄ የተሞላበት፣ ሊሆን ይገባል። በቅርቡ ተገልብጦ ሊያሳፍረን ይችላል ብሎ መስጋት፣ ለጉዳዩ መጠነኛ የአየር ሰዓት መስጠትና ውሎ አድሮ ደግሞ መርጋቱን እያዩ ወደሌላው መተላለፍ ተገቢ ነው። እንደው በአንድ ጊዜ ይህን ከምላስ በስተቀር ቁም ነገር የሌለው ተራ ካድሬ ወደላይ ቆልሎ አንድ ጊዜ “አክቲቪስት” ሌላ ጊዜ ደግሞ “የፖለቲካ ተንታኝ” እያሉ በኢትዮጵያውያን ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ የተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅትን እንዲመራ ማጨት ድረስ መጓዙና አሉ ከሚባሉ ፖለቲከኞች ጋር መድረክ እንዲጋራ ሁኔታዎችን ማመቻቸቱ አገባብ አልነበረም።

የኢሳት ባልደረባ ደረጀ ሃብተወልድ የአባ መላን መገልበጥ አስመልክቶ በፌስቡክ ገጹ ላይ እንዳሰፈረው ከሆነ ግን ኢሳቶች ከስህተቶቻቸው ሊማሩ የተሰናዱ አይመስልም ይልቁኑም አባ መላን አስመልክቶ ሊቀርቡ የሚችሉ ትችቶችን ቀድሞ ለመከላከል ነው ሙከራ የሚያደርጉ ያሉት። ደረጀ ሃብተወልድ እንዲህ ነበር ያለው፣

“ነገሩ ወዲህ ነው። አባ መላ ኢህአዴጎችን እየሰደበ ወደ ተቃዋሚው ጎራ ሲቀላቀል “አገኛለሁ” ብሎ ያሰላው ጥቅም ነበር። ሆኖም ሀሳብን በነፃነት ለመግለጽ ከሚያስችል ነፃ መድረክ ውጪ ሌላ ነገር ሊያገኝ አልቻለም። ባገኘው ነፃ መድረክም ማንም ሳይቆነጥጠው ከትንሽ እስከ ትልቅ የቀድሞ አለቆቹን እስከ ዶቃ ማሰሪያቸው ነግሯቸዋል። እኛንም አስቆናል። ስንስቅለት ጨምሮ ጨማምሮ አቅምሷቸዋል። እኛም፦“የአገሩን ሰርዶ ባገሩ በሬ” እያልን ተዝናንተናል። ከዚያ ባለፈ ግን ለቁም ነገር ያሰበው ሰው ስለመኖሩ እጠራጠራለሁ።”

የደረጀን አባባል ሁሉም ሰው የተቀበለው አይመስልም ይህን ለማሳየት ከተቃውሞ ሃሳቦች መካከል አንዱን ከዚያው ከደረጀ ሃብተወልድ የፌስቡክ ገጽ ልበደር፣

“የአባ መላን መገልበጥ ተከትሎ ኢሳቶች ከተወቃሽነት ለመዳን የዘየዳችሁት ይሄው ነው? ደረጀ “አባ መላን ለቁም ነገር ያሰበው ያለ አይመስለኝም” ያልከው ፈጽሞ ከእውነት የራቀ ነው፣ በሳውዲ ወገኖቻችንን ለመታደግ በተቋቋመው አለም አቀፍ ድርጅት ውስጥ ከታማኝ እና አበበ ገላው ቀጥሎ ሶስተኛ ሰው ተደርጎ አልነበረም? በጣም ብዙ ማለት ይቻላል… “እጄን በጄ” ሆኖብን እንጂ። ለማንኛውም ከስህተቶቻችሁ ተማሩ፣ በጣምም አንፍጠጥ ያስተዛዝባል።” Ethiopian Unity

ለማጠቃለል ያህል የሚሰራ ጋዜጠኛ፣ ለውጥ ለማምጣት የሚተጋ ፖለቲከኛና የዲሞክራሲ ታጋይ በሂደት ውስጥ ስህተት ሊሰራ ይችላል፣ ከስህተቶች ትምህርት ወስዶ ለሁለተኛ ጊዜ ተመሳሳይ ስህተትን ላለመድገም ጥረት ማድረግ ግን ሊለመድ ይገባል። ነገሮቻችን ሁሉ “ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ” እንዳይሆኑ ሃላፊነት ወስደን ከስህተቶቻችን ለመማር ዝግጁ እንሁን።

[የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ጉዳይ] –ማን ለጠበቃ ፈረመ???

$
0
0

ሰላም ለሁላችሁ፤
debereselam Minnesota
ለሰላም እና ለአንድነት ከቆሙ ምዕመናን የተላለፈ መልዕክት፦

በቤተክርስቲያናችን መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ቤተክርስቲያኑን ወክሎ ማንኛውንም ውለታ/ሰነድ መፈረም የሚችለው ሊቀመንበሩ ብቻ እንደሆነ በግልጽ ተቀምጧል። የእየአንዳንዱ የቦርድ አባል የሥራ ድርሻ በተዘረዘረበት አንቀጽ 6 ላይ ማን በቤተክርስቲያኑ ስም ሰነዶችን
መፈረም እንደሚችል ተደንግጎ እናገኛለን ። አንቀጽ 6 ክፍል 3 ሀ ተ.ቁ 7 እንዲህ ይላል፦

“ሊቀመንበሩ፦

7. ጠቅላላ ጉባኤው፤ የባለአደራዎች ቦርድና የሥራ አስፈጻሚው ኮሚቴ የተስማሙባቸውን ሰነዶችና ስምምነቶች ቤተክርስቲያኒቱን በመከወከል ይፈርማል”

ቤተክርስቲያኑን ወክያለሁ የምትለው ይህች ጠበቃ ግን ገና ሊቀመንበሩ በቦርድ ሕገወጥ ስብሰባ ታግደዋል ሳይባል ነው የቤተክርስቲያኑ ጠበቃ ነኝ ያለችው። ይህም ለሕጋዊው ሊቀመንበር በማያገባት ገብታ የሕዝብ ተምራጭ የሆኑትን ሊቀመንበር ከቦርድ ተባረዋል ብላ በጻፈችው ደብዳቤ ተጠቅሷል። እነርሱ ሊቀመንበር ያሉት እኛ ግን በሊቀመንበርነት የማናውቀው ሰውም ይህን ሰነድ የመፈረም ስልጣን የለውም። እነርሱም መርጠነዋል ያሉት ከዛ በሗል ነው። እናም የማርች 9ኙ ቤተክርስቲያኑ ተከሰሰ አዋጅ አጣብቂኝ ውስጥ የመግባታቸው ውጤት ነው። ድሮም ወያኔ ወንዝ አያሻግርም።
የእምነት ሕፀጽ የሌለባትን ቤተክርስቲያን በጥብጠው፣ ሲካፈሉት የኖሩትን ቅዱስ አገልግሎት እንደ መርገም ቆጥረው ቀኖና ያጎደለ ቤተክርስቲያን ነው ሲሉ የማይሰቀጥጣቸው፣ ሕዝቡን በማሸበር የፖለቲካ ተልእኳቸው ተከታይ የሚሆን መስሏቸው የሌለውን ችግር ፈጥረው ሰላማችንን ሲያምሱ መክረማቸውን
ያየ መድኃኔዓለም ቤቱን ባጸዳበት ቀን እነዚህንም ሊያጸዳ እያጻፋ አናገራቸው። በጥፋት ላይ ጥፋት በክስረት ላይ ክስረት ብቻ ስለሆነ ትርፉ እባካችሁ የበደላችሁትን ጌታ አና ኅዝብ ይቅርታ ጠይቃችሁ አርፋችሁ ተቀመጡ። የባሰ ሳይመጣ። ጊዜው ለዚህ የተመቸ ነውና።

ይህ ሕዝብ ሳይፈቅድና ሳያምንበት በቤተክርሲታኑ አቋም ላይ አንዳች ለውጥ አይመጣም!!! አሁንም ወደፊትም በአባቶች መካከል ያለው መለያየት እስኪወገድ ድረስ ከቤተክርስቲያናችን ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ሳይሆን ከስልጣን ሽኩቻ፣ በዘረኝነትና በሙስና ከተጨማለቀ አስተዳደር ገለልተኛ ነን !!! ወዳጆቼ የአስተሳሰብ ልዩነት እኮ እንዲህ በግትረኝነትና ለምን ፍርስርስ አይልም እያሉ የሚያራምዱት አይደለም። ሕዝብ ወሰነ። እናንተ ግን 40/50 ሰው ጎድሎ ነበርና በክፍተኛ ድምጽ የተወሰነውን ውሳኔ አንቀበልም ብላችሁ በማያዋጣ ጎዳና መጓዝ ጀመራችሁ። መጨረሻችሁም ይኽው ከፍተኛ ወጪ አስከተለ። አሁንም አስቡበት አያዋጣችሁም። ሽንፈትን መቀበል ከባድ ቢሆንም ሊመጣ ካለው ከባድ ሽንፈት ይሻላልና ክርስቲያን ከሆናችሁ ይብቃችሁ። ባስቸኳይ ኅዝቡ ባቀረበው አጀንዳ መሠረት ጠቅላላ ጉባኔ ጥሩ። ሕዝቡ ከፈለገ ትቀጥላላችሁ ካልፈለጋችሁ ደግሞ እንደመረጣችሁ ያወርዳችኋል።
እስኪ እንደ ክርስቲያን ይቅርና እንደሰው ለደቂቃ አስቡት? በዚህ ባመጣችሁት ጉዳይ ምክንያት ምን ተጠቀምን? ምን አተረፍን? ችግር ተፈታ? ተቃለለ? ወይንስ ተባባሰ? ገለልተኝነት ቀረ? የችግሩ ምንጭ ፖለቲካ ነው። ችግሩ የሚፈታውም ፖለቲካው የሆነ ለውጥ ሲያመጣ ነው ወይንም ሲለወጥ ነው። ማንም ቢዳክር የተለያዩት አባቶች ሳይስማሙ/ሳይታረቁ ይህ ችግር አይፈታም!!!

በደብራችን በደብረሰላምም ሆነ በተዋሕዶ እምነታችን ላይ ምንም ከወትሮው የተለየ የእምነት ችግር የለም!!! ችግሩ የአስተዳደርና የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ነው። የእምነት ችግር አለ ለሚል ሰው ግን እስካሁን በገለልተኛ ቢተክርስቲያናት የተካፈለውን መንፈሳዊ አገልግሎት ምን ሊያደርገው ነው? ንሰሐ ሊገባበት ነው? ከዚህ በኋላስ በገለልተኛ ቤተክርስቲያን ይገለገላል? በርግጥ ያየበት መነጽር ስሕተት እንደነበረ ካመነ ምንም አይደል። አለበለዚያግን ክርስትናው አጠያያቂ ነው። ለማንኛውም መድኃኔዓለም ልቦና ይስጣችሁ። እውነት የቤተክርስቲያን ነገር ካሳሰባችሁ ብዙ የሚሰራ ሥራ አልና እዛላይ ብንሰራ ይሻላል። እናም እባካችሁ ይብቃችሁ!!!


የብርሃኑ ዳምጤ (አባመላ) ቅልቅል (ከክንፉ አሰፋ) ጋዜጠኛ

$
0
0

ብርሃኑ ዳምጤ እንደገና ሲገለበጥ የአስር አመት ልጅ ሳለሁ ያጋጠመኝን አንድ ክስተት አስታወሰኝ። በሰፈራችን ውስጥ ልጆችን ሁሉ የሚጠሉ አንድ ሰውየ ነበሩ። አንድ ቀን በድንገት ተነሱና የሰፈሩን ሰው ሁሉ መሰናበት ጀመሩ። በእጃቸው 3 ሜትር የሚያህል ርዝመት ያለው ገመድ ይዘዋል። “የሰፈሩ ልጆች ስላስቸገሩኝ ራሴን ልስቅል ነው። ደህና ሁኑ…” እያሉ ሁሉንም ተሰናብተው ሲያበቁ ለመሰቀል መንገዳቸውን ጀመሩ። የእኝህ ሰው ውሳኔ ለመንደሩ ሰው ሁሉ ደንታ አልሰጠውም።

የሰፈር ልጆች ግን ተከተልናቸው። ብዙ ነበርን። ሰውየው ተራራ ሲወጡ አብረን ወጣን። ቁልቁል ሲወርዱም አብረን ወረድን። ጉዞው አሰልቺ ነበር። ግን ተስፋ ሳንቆርጥ ጉዱን ለማየት ስንል ተከተልናቸው። በመጨረሻ አንድ ዛፍ አገኙና የሚሰቀሉበትን ገመድ እዛፉ ላይ ማሰር ጀመሩ።

ሰው ሲሞት አይተን ስለማናውቅ ሁኔታውን እንደ ልብ አንጠልጣይ ፊልም ነበር በጉጉት የምንከታተለው። ሰውዬው በዚህ ሁኔታ ለመሞት መወሰናቸው ብዙም አላስደነገጠንም። ይልቁንም ከኛ እየቀሙ በግቢያቸው ያጠራቅሙዋቸው ኳሶቻችን ነጻ ሊወጡልን ነው ብለን ተደስተናል።

ገመዱን አስረው ራሳቸውን ለመሰቀል ካመቻቹ በኋላ ዘውር ብለው እኛን ተመለከቱን። «እባኮን ይተው!» የሚላቸው አንድ እንኳን ሰው አልነበረም። ለደቂቃዎች በአትኩሮት ከተመለከቱን በኋላ እንዲህ አሉ። «እንዲያውም ደስ አይበላችሁ። ሃሳቤን ቀይሬአለሁ። አልሰቀልም!»

ዛፉ ላይ ያሰሩትን ገመድ ፈቱትና ወደ ሰፈር አቀኑ። ካልተሳከው የጎልጎታ መሰውያ ሲመለሱ እመንገድ ላይ ያገኛቸው አንድ ሰው ሲመክራቸው ሰማን። «ሌላ ግዜ መሰቀል ከፈለጉ ለሰው አይናገሩ። ድምጽ አጥፍተው ለብቻዎ ያርጉት። የዚህ ሰፈር ልጆች አብዝተውታል። ሰው በሰላም እንኳን እንዳይሞት እያደረጉ ነው።»
aba mela
ሰውየው ለመካሪያቸው ምንም ምልስ አልሰጡም- ግን ወደኛ እየተገላመጡ «እርሱት። አታገኙዋትም!» የማለት አይነት በአይናቸው እየዛቱብን እቤታቸው ገቡ።

ከልጅ ጋር የሚጫወቱት እንቁልልጬ መሆኑ ነው። ለዚያማ ማን አክሎን። የባሰ እልህ ውስጥ አስገቡን። … በመጨረሻ ብቻቸውን መንገድ ላይ እያወሩ መሄድ ሲጀምሩ ተውናቸው። …

የሳይበሩ አንበሳ የመታጠፉ ፍጥነት ሳይገርመን የድጋሚ ቅልቅሉን በከአዲስ ዜማ አከለበት። “እንደውም ደስ አይበላችሁ። ወያኔን ተቀላቅያለሁ!” የሚል ዜማ። የልጅነት እንቁልልጬ ጨዋታ ይመስላል። ለመዞርማ ምድርም ብርሃንና ጨለማን ለማፈራረቅ በራስዋ ዛቢያ ላይ ትዞራለች። የኋላውን ለማየት ሲል አንገትም ይዞራል። ብረትም ይዞራል – በእሳት ሲፈተን። … ቆርቆሮ ግን እንዲሁ ይጠመዘዛል።

«..እኔ እንኳን ትንሽ መቆየት ፈልጌ ነበር።» አለ ኦቦ ዳምጤ፤ ለሁለተኛው ዙር ከወያኔ ጋር ያደረገውን ቅልቅል ሲያበስር። ይህችን አነጋገር የተጠቀመባት ያለ ምክንያት አልነበረም። ወደዚህኛው ጎራ የገባው የጥምር ሰላይ (double agent) ስራ ለመስራት እንደሆነ ለማስመሰል መሞከሩ ነበር። ፈረንጆቹ (match fixing) ማች ፊክሲንግ የሚሉት በእግር ኳስ አለም ውስጥ ለተቃራኒው ተገዝቶ የመስራት ውስልትና አይነት መሆኑ ነው። እንዲህ የተራቀቀ ቢሆንማ ኖሮ እናደንቀው ነበር። ግና በዚያው ቃለ-ምልልስ ላጠፋው ጥፋት ይቅርታ ጠይቆ ጨዋታውን አበላሸው። ድንጋይ በትከሻው ባይሸከምም ህሊናውን ዝቅ አድርጎ ከአክራሪ ዲያስፖራ ጋር በመዋሉ በጣም ተሰምቶታት። ወያኔዎች ይቅርታ የሚላቸውን ለምን እንደሚወዱ አይገባኝም። ይቅርታ የሚጠይቋቸውን ሰዎች በጣም ሲወድዱ እንጂ ምህረት ሲያደርጉላቸው ግን አይተን አናውቅም። ታምራት ላይኔን በፓርላማ ካዋረዱት በኋላ ቀፈደዱት። ሰለሞን ተካልኝም ከይቅርታ አልፎ ከዲያስፖራው ርኩስነት ለመጽዳት ሲል አባን ጸበል እርጩኝ ብሎ ነበር – በዘፈን። መቀሌ ድረስ ሄዶ በኢህአዴግ ጸበል ቢጠመቅም፣ እነሱ ግን ቂማቸውን አልረሱም። ሁሉንም ማኖ እያስነኩ በአየር ላይ ያንሳፍፏቸዋል።

አባመላ ከነሱ ጋር ተጣልቶ ወደ ተቃውሞ ጎራ በሄደ ጊዜ ወያኔዎች አንድም ነገር አልተነፈሱም ነበር። ምክንያቱም ጸቡ የመርህ እንዳልነበር ያውቁታል። ጉዳዩ የግል ጥቅም ነው። መፍትሄውም ቀላል። በፈለጉት ግዜ እንደ ቆላ በሬ አሞሌ ጨው አልሰው እንደሚመልሱት አስቀድመው ያውቁታል።

በቃለ-ምልልሱ አባ መላ በካፒቴን ሀይለመድህን አበራ ዙርያ የተነሳውን ክርክር ሊቋቋመው እንዳልቻለ አልካደም። በክርክር ሲሸነፍ እንደመፍትሄ የወሰደው የወያኔን ጎራ መቀላቀል መሆኑም አዲስ ነገር አይደለም። ያኛው ጎራ በሃሳብ የተሸነፉ መሃይማን መሰብሰብያ ጎራ ከሆነ ሰንበትበት ብሏል።

ንግግር መቻል አንድ ነገር ነው። እየቀለዱ ሰውን ማሳቅም ቀላል ሊሆን ይችላል። በመናገር ሰዎችን ማሳመን መቻል ግን ሌላ ጉዳይ ነው። ይህ ጥበብን፣ ብስለትን እና አስተዋይነትን ይጠይቃል። በንግግር ሰዎችን ማሳመን መቻል ደግሞ ሮኬት ሳይንስ መሆንን አይጠይቅም። አንዳንዶች በትምህርት ያገኙታል። ሌሎች በማንበብ ይለወጣሉ። የህይወት ተመክሮም በራሱ ብዙ ነገር ያስተምራል። ከስህተታቸው እየተማሩ የሚበስሉ ሰዎችም ብልሆች ናቸው።

«አቶ መለስ ዜናዊ እድሜ ልካቸውን የአማራን ህዝብ ሲሳደቡ ሰንብተው፤ አንድ አማራ ሲሰድባቸው ግን ደግም ላይመለሱ አሸለቡ።» የሚል ቀልድ ሰምቼ በጣም ነበር የሳቅኩት። ነገሩ ልክ ነው። በሌላው ላይ የሚቀልዱ ሰዎች በራሳቸው ላይ ሲደርስ በቶሎ ይሰበራሉ ይባላል።

እናም በሃይለመድህን ጉዳይ «ከጽንፈኞች» ሳይስማማ በመቅረቱ የጠፋው በግ ወደ ቤቴ ተመለስኩ ነው እያለን ያለው። ይህ ሰው ግን ስንት ጊዜ ነው ከቤቱ የሚጠፋው?

ደግሞ ፍጥነቱ። የብርሃን ጉዞም እንደብርሃኑ ዳምጤ አይፈጥነም። ወደዚያኛው ጎራ ሲቀየስ የለበሰውን የዲያስፖራ ማልያ እንኳ ለመለወጥ ግዜ አልወሰደም። የቡናን ማልያ ለብሶ ለደደቢት የሚጫወት አይነት ሰው ነው የሆነው።

እንደዚህ አይነት ሰዎች ስብእናቸውን የሚሸከም አንገት ስለሌላቸው ወደግራም ሆነ ወደቀኝ፣ ወደፊትም ሆነ ወደኋላ ለመተጣጠፍ ችግር የለባቸውም። ይህ ሰው ወደ ቀኝ ታጥፎ በነበረበት ግዜ ከአንዴም ሶስቴ ደውሎ በስልክ አናግሮኝ ነበር። አቀራረቡ፣ አነጋገሩና ጨዋታው ያራዳ ልጅ ይመስላል። ተግባሩ ግን የአራዳ ልጅ አይደለም። ያራዳ ልጅ ባልንጀራውን ይረዳዋል እንጂ በቁሙ ሊያርደው አይዳዳም።

ወያኔ የመሆን መብቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህንን ለመሆን የሄደበት መንገድ ግን በጣም ይደብራል። ድርጊቱ ሰሞኑን በፈረንሳይ ሃገር ከተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ ጋር ተመሳሳይ ነው የሆነብኝ። የክህደት ትንሽ የለውም። ልዩነቱ አባ መላ ያስጠጉትን ወገኖች በቁም አለመግደሉ ብቻ ነው።

አንዲት የዋህ ወይዘሮ፤ በፓሪስ ከተማ እመንገድ ላይ ወድቆ የሚለምን ኢትዮጵያዊ ወገን አግኝተው እጅግ አዘኑለት። እቤታቸውም ወስደው ማረፍያ ሰጡት። መሰረታዊ የሆነውን ነገር ሁሉ አሟሉለት። አምነው ያሳደሩት ይህ ሰው ግን ውለታቸውን በአሰቃቂ ሁኔታ መለሰላቸው። አራት ወር እንደቆየ ይህንን የሶስት ልጆች እናት ከትንሽ ልጃቸው ጋር በሴንጢ አርዶ ተሰወረ። አባመላ አብረውት ሲሰሩ የነበሩትን በቢላ ባያርዳቸውም በአነጋገሩ ስጋቸውን እንደበላው ነው የሚቆጠረው። አምነው አስተጉት ይህ ሰው እንደጴጥሮስ ጎህ ሳይቀድ ካዳቸው። የክህደት ቁልቁለት ይሏል እንዲህ ነው። «የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ!» ይላሉ አበው። ቃልን ማጉደል ምን ያህል ከባድ ነው!

ታማኝ በየነ እና አበበ ገላው ከብርሃኑ ዳምጤ ጋር በሳውዲው ቀውስ አብረው መስራት ሲጀምሩ በፍጹም ቅንነት እና በየዋህነት ነበር። ይህንን በማድረጋቸውም በርካታ ትችት ቀርቦባቸዋል። እነሆ አባ መላ ዛሬ ለቅልቅሉ እጅ መንሻ እነሱን በመሳደብ እንደመስዋዕት አቀረባቸው።

የብርሃኑ ዳምጤ አካሄድ ያሳሰባቸው ሁለት ወዳጆቼ በዚያን ሰሞን በዚሁ ጉዳይ ላይ በሰል ያለ አስተያየት ጽፈው ነበር። በልጅግ ዓሊ (ከፍራንክፈርት) እና እንግዳሸት ታደሰ (ከኦስሎ)። እነዚህን ጽሁፎች እንደገና እንድታነቧቸው እመክራለሁ። በልጅግ ዓሊ «ዘመንን ለማሰር» በሚለው ጽሁፉ ይህ ሰው እንደ ጴትሮስ ይክደናል ነበር ያለው።
…ለአንዲት የሰሙኑ የፖለቲካ ጥቅም ሲባል ብርሃኑ ደቡርን እላይ የሰቀላችሁት በኋላ እንደለመደው ሲክዳችሁ ስትንጫጩ መስማታችን አይቀርም። ትንቢት እንዳይመስላችሁ ደቡርን በደንብ አድርገን እናቀውቀዋለን። ቆዳችሁን ገፎ ይሸጠዋል፣ ደቡር ሃገሩን አይደለም እናቱንም ቢሆን ይደልላል። አታውቁት እንደሆን መርካቶ ላይ ሄዳችሁ የተሰራውን ግፍ ጠይቁ። እንኳን የቀይ ሽብሩን ፣ እነ ሽብሬን ረስተን የለም እንዴ !! ምን ይደንቃል።
ብሎ ነበር። እንግዳሸት ታደሰ ከኖርዌይ የጻፈውም ተመሳሳይ ነገር ነበር። «አባ መላ ልብ ሲበላ! » በሚለው መጣጥፉ «የዲያስፖራ ኃይል በአራዳ ስልትና በወያኔ ቆረጣ ለመሰንጠቅ ፣ የሚደረግም ጨዋታ ሊሆን ይችላል ብሎ መገመትም የዋህነት አይመስለኝም።» ነበር ያለው። እነዚህን መጣጥፎች ደግሜ ሳነባቸው ትንቢት ነው የመሰሉኝ። በወቅቱ ግን እነዚህን ጽሁፎች በድረገጽ በማውጣቴ የስድብ ናዳ ወርዶብኝ ነበር። አንዱ የፓልቶክ ታዳሚ እንዲህ ብሎ ነበር የጻፈልኝ። «የማናውቅህ እንዳይመስልህ! አንተ የዳዊት ከበደ ወንድም!»
የትኛው ዳዊት እንደሆነ ግን ግልጽ አላደረገልኝም። የአትላንታው ወይንስ የአውራምባው?

እርግጥ ነው። በፖለቲካ ቋሚ ወዳጅ ወይንም ቋሚ ጠላት የለም – ጥቅም እንጂ። በመርህ ላይ ሳይሆን ይልቁንም ለግል ጥቅም ሲሉ የሚዋዥቁ ሰዎች ናቸው ሀገርን የሚያጠፉት። በተለምዶ መሃል ሰፋሪዎች ይባላሉ። እንደዚህ አይነቶቹ ሰዎች በተቃዋሚውም ጎራ ነፍ ናቸው። ደጋፊ ሳይሆን ተደጋፊ ሆነው ለመኖር ሲሉ ብዙ ጥፋት ይሰራሉ። የሃይል ሚዛኑ እስካዘነበለ ድረስ ለአለቆቻቸው እጅግ ታማኝ ይሆናሉ። የሃይል ሚዛኑ ሲዛባ ደግሞ ለመካድ የመጀመርያዎቹ ናቸው።

ይህ የመርካቶ ቁጭበሉ ሼም አያውቅም። ትንሽ ብትጠብቁት እንደገና ይመለሳል። በዚህ አይነት ሰው ላይ እምነት መጣል እና መስጋት ከየዋህነት ያለፈ ነው። አንድ ጅል ትምህርት ቤት ሲሄድ የሙዝ ልጣጭ አዳልጦት ወደቀ። ከትምህርት ቤት ሲመለስ ያችኑ የሙዝ ልጣጭ አይቶ ቆመ። ከዚያም ማልቀስ ጀመረ። ለምን እንደሚያለቅስ ሲጠየቅ ወደ ልጣጩ እያመለከተ እንዲህ አለ። «እንደገና ልወድቅ ነው።»

አባ መላ እና መላ ያጣው ንግግራቸው (በዳጉ ኢትዮጵያ)

$
0
0

አቶ ብርሃኑ ዳምጤ (አባ መላ) በቅርቡ ስላደረጉት የአቋም ለውጥ ለቢንያም ከበደ (ቤን) የሰጡትን ቃለ መጠይቅ አነበብኩት፡፡ ላልተጠበቀው የ180 ዲግሪ የአቋም ለውጥ በመንስኤነት ከጥቅመኛ ፖለቲከኝነት እስከ የጠበቁትን አለማግኘት በርካታ ምክንያቶች እየተጠቀሱ በብዙዎች ትንታኔ እየተሰጠበት ይገኛል፡፡ እኔ በዚህ ረገድ ምንም ለማለት አልፈልግም፡፡ ይልቁንስ በቃለ ምልልሳቸው ኢሳትን በተመለከተ በሰነዘሯቸው አንዳንድ የተሳሳቱ ነጥቦች ላይ ጥቂት ብል እመርጣለሁ፡፡ የትኩረት ነጥቦቼን በተናጠል ተራ በተራ እዘረዝራለሁ፡፡

Aba Mela
“ምንም አይነት የዜና ምንጭ የሌላቸው”
አቶ ብርሃኑ ስለኢሳት ከተናገሯቸው ነጥቦች የመጀመሪያው “ኢሳት ምንም አይነት የዜና ምንጭ የለውም” የሚል ነው፡፡ እውነት ለመናገር ራሳቸው አቶ ብርሃኑም በዚህ ንግግራቸው የሚያምኑበት ከሆነ አስቂኝ ነው፡፡ እንዴ አቶ ብርሐኑ፡- መቼም የጠቅላይ ሚኒስትርዎትን ሞት ቀድመው የሰሙት ከኢቲቪ አልያም ከፋና አይደለም፡፡ የብአዴን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለምነውን አስፀያፊ ንግግር ከዝግ የካድሬዎች ስብሰባ ላይ ቀድቶ አየር ላይ ያዋለው የሰሞኑን ወዳጅዎ (መቼም እርስዎ በዚህ ተለዋዋጭ አቋምዎ ዘላቂ ወዳጅ አይኖርዎትም ብዬ ነው) አቶ ቢንያም አይመስለኝም፡፡ ኸረ ስንቱ ስንቱ… ከጉራ ፋርዳ የአማራ ተወላጆች መፈናቀል እስከ የኦህዴድ ውስጣዊ ህንፍሽፍሽ… ኢሳት ይህን ሁሉ ከህዝብ ተደብቆ የነበረ መረጃ አደባባይ ያወጣው ያለአንዳች የመረጃ ምንጭ ነው ካሉን በአመክኒዮ ሳይሆን በስሜት እንደሚነዱ በራስዎ ላይ እየመሰከሩ ነው፡፡
“የዜና ምንጫቸው በአብዛኛው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ነው”
ይህ ነጥብ ደግሞ አስቂኝነቱ ያመዝናል፡፡ ኢሳት የኢቲቪን ዜና “ትዊስት እያደረገ የመጀመሪያውን መጨረሻ የመጨረሻውን መጀመሪያ” አድርጎ የሚያቀርብ ከሆነ አራተኛው የኢቲቪ ቻናል ሆነ ማለት ነው፡፡ የኢቲቪን ዜና ዳግም የሚያሰራጭ (Rebroadcast) ጣቢያ ከሆነ ደግሞ እኔን ጨምሮ በሚሊዮን የምንቆጠር ኢትዮጵያውያን አማራጭ የመረጃ ምንጭ ባላደረግነው ነበር፡፡ ለምን ቢሉ ኢቲቪን ዲሽ መትከል ሳያስፈልገን፤ አንዱ የስርጭት ሞገድ ሲዘጋ በመቶዎችና በሺዎች የሚቆጠር ብር ከእለት ጉርሳችን ነጥቀን ለዲሽ አስተካካዮች ሳንከፍል መከታተል እንችላለን፡፡ እውነቱን ለመናገር የኢሳት የተሰሚነት ሚስጥር እርስዎ ከተናገሩት ተቃራኒው ነው፡፡ ከአሰልቺውና ከእውነት ከተጣላው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ፕሮፖጋንዳ የሚያስጥል አማራጭ አድርጎ ኢሳት ራሱን ማቅረቡ ነው የተሰሚነቱ ምክንያት፡፡ እስኪ ለዛሬ ለእውነት ታማኝ ለመሆን ይሞክሩና የኢቲቪንና የኢሳትን የዜና ፕሮግራሞች ይከታተሉ፡፡ ኢቲቪ የሐረር የውኃ ችግር እንደተቃለለ “አንዳንድ ነዋሪዎችን” እማኝ አድርጎ ሲዘግብልዎት ኢሳት ግን በህዝቡ አዕምሮ ውስጥ የሚብሰለሰለውን የሐረር የግንብ መደዳ ሱቆች ቃጠሎ ክስተት ተጎጂዎቹን እያነጋገረ ያስደምጥዎታል፡፡ እርስዎ በሐረር ከተማ ቢኖሩ አሊያም በከተማው ውስጥ የሚኖር አንዳች የቅርብ ዘመድ ካለዎት የኢቲቪን “ሐረር ሠላም ነው ምንም አልተፈጠረም” የዘወርዋራ ፕሮፖጋንዳ ለመስማት የሚያስችልዎት አንዳች ፍላጎት ይኖርዎ ይሆን?
“ተአማኝነት የሌለው”
በቅርቡ የብአዴን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የአቶ አለምነውን ስድብ-አዘል ንግግርና የፓርቲያቸውን የዝምታ ስምምነት በመቃወም በባህር ዳር ከተማ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተሳተፉበት ደማቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሒዶ ነበር፡፡ ሠልፈኞቹ ለተቃውሞ የወጡበትን የአቶ አለምነውን ንግግር የሰሙት በሌላ በማንም ሚዲያ ሳይሆን በኢሳት ነው፡፡ ከአዲስ አበባ በ500 ኪ.ሜ ርቀት የሚኖሩ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በኢሳት የሰሙትን መረጃ አምነው ለተቃውሞ የባህር ዳር ከተማን ጎዳናዎች አጥለቅልቀዋል፡፡ ተአማኝነት ማለት እንግዲህ ከዚህ በላይ ምን ማለት ይሆን?
“ኢሳት ከግንቦት ሰባት ውጪ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶችን አያስተናግድም”
አቶ ብርሐኑና እኔ የምንሰማው ሁለት የተለያዩ ኢሳቶችን ካልሆነ በቀር በየእለቱ የኢሳት ፕሮግራሞች የአንድነት፣ የሠማያዊ፣ የአረና ወዘተ እንቅስቃሴዎችና መግለጫዎች ሰፊ ሽፋን የሚያገኙት በኢሳት ነው፡፡ ቀደም ሲል የጠቀስኩት የባህር ዳር የአንድነት ፓርቲና የመኢአድ የተቃውሞ ሠልፍ የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኘው በኢሳት ነበር፡፡ ኢቲቪማ በሠልፉ ተደናግጦ ስለሰልፉ አንዳች ቃል ሳይተነፍስ ይልቁንስ “መድረክ አንድነትን ከአባልነት ማገዱን” እያጋነነ ሲዘግብልን ነበር፡፡ “ተቃዋሚዎች ተከፋፈሉ” ነው መልዕክቱ፡፡ ሁለት ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች (አንድነት ፓርቲና መኢአድ) በትብብር መሬት-አርዕድ የተቃውሞ ሠልፍ ማድረጋቸው ሳይሆን አንድ ፓርቲ ለጊዜው ከመድረክ መታገዱ ለገዢው ፓርቲ የሚጠቅም ዜና ስለሆነ ሽፋን ያገኛል- በኢቲቪ መስፈርት፡፡
“በኢሳት ከግንቦት ሰባት ውጪ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ሽፋን አያገኙም” ለሚለው የአቶ ብርሐኑ አስተያየት ራሱ ገዢው ፓርቲ ከሳምንታት በፊት በሐገር ውስጥ በህጋዊነት ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች መሪዎች በኢሳት መግለጨ መስጠታቸው ህገወጥ ነው ሲል መክሰሱና አንድነትና ሠማያዊ ፓርቲም “ይህን ማድረግ መብታችን ነው” ሲሉ በጽኑ መቃወማቸው ጉልህ ማስተባበያ ነው፡፡ ሌላው ቢቀር ግንቦት ሰባት “ከኤርትራ በማገኘው ድጋፍም ጭምር ተጠቅሜ የአገዛዝ ስርዓቱን አወርዳለሁ” ሲል በሰጠው መግለጫ ላይ ጊዚያዊ የሽግግር ምክር ቤቱ ተቃውሞ ማሰማቱን ከዋና ፀሐፊው አንደበት የሰማነው በዚሁ በኢሳት እንደነበት አቶ ብርሐኑ አይዘነጉትም ብዬ አምናለሁ፡፡
በአጠቃላይ የያዙትን የፖለቲካ አቋም በማናቸውም ምክንያት ትቶ የአቋም ለውጥ ማድረግ ሊከበርለት የሚገባ የማንም ሰው መብት ነው፡፡ ነገር ግን አዲስ የተቀላቀሉት ካምፕን ደስ ለማሰኝትና ድርጎ ቢጤም ለማግኘት በማሰብ የባሰ ትዝብት ላይ የሚጥል ንግግር መናገሩ ፋይዳው ብዙም አይታየኝም፡፡ አገዛዙ እንደሆነ ደጋፊህ ነኝ ብሎ ለሚመጣለት (በተለይም ከተቃዋሚው ጎራ) ከህዝብ አንጡራ ሐብት ላይ ዘግኖ ላለመስጠት የሚያስችል አንጀት እንደሌለው የታወቀ ነውና አቶ ብርሐኑም ያሰቡትን ለማግኘት ብዙ መቀባጠር የሚኖርብዎት አይመስለኝም፡፡ አበቃሁ!

ትዝብት –ደርሶ መልስ ዲያስፖራ (ኢትዮጵያ ደርሶ የመጣ ዲያስፖራ የሚነግራችሁ እውነት) (አንደኛ)

$
0
0

አትክልት አሰፋ (ቫንኩቨር) – ጋዜጠኛ

ነገሩ የሆነው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ነው። ቆነጃጅት ወጣት ሴት ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውጭ ባሉ የከተማው ደለላዎች ጋር በመተባበር እጅግ ዘግናኝ ስራ ይሰራሉ። ደላሎቹ የቆነጃጅቶቹን ተማሪዎች ፎቶ የያዘ ትልቅ ካታሎግ ይዘው ከአዲስ አበባም ሆነ ከአቅራቢያው ከተሞች አለዚያም ከዚያው ከዲላ ከተማ ብቅ የሚሉ ሃብታም ደንበኞቻቸውን የተማሪ ኮረዶችን ፎቶ በመስጠት ያስመርጣሉ።

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

ሰውየው ውብ ወጣት ተማሪ ኮረዳ እንደሚፈልግ በሰው በሰው የተገናኘውን ደላላ ይጠይቃል። እናም ከተሰጠው የፎቶ ድርድር ላይ ማመን ያቃተውን የአንዷን ውብ ፎቶ እያሳየ ‘ይህችን ታውቃታለህ?’ ሲል ይጠይቃል። የደላላ መልስ አንድ ነው… ሁሉንም ስለሚያውቃቸው አልተቸገረም ‘አዎ እሷን ይፈልጋሉ?’ ሲል ይጠይቃል። ሰውየውም ‘እባክህ’ ሲል በመማጸን ፈቃደኝነቱን ይገልጻል። ከፊቱ የመጣለትን ገቢ ተደራድሮ ልጅትን ለመጥራት ይሮጣል። ደላላው።

እናም ቆንጅት ተበጃጅታ፣ አምራና ደምቃ ትመጣለች። በቀጥታ ወደ ሰውየው መኪና ስትደርስ ሰውነቷ ይርዳል። በቁጣ አይኑ የተንቀለቀለው ሰውየም ወደ ልጅቷ ያፈጣል… በቀጥታ ተንደርድሮ የልጅቷን ክርን ይይዛል… ደላላው እየሆነ ያለውን ሊረዳ አልቻለም… የልጅቷን እጅ የያዘው ሰው (ደንበኛ) የልጅቷ ወላጅ አባት ኖሯል።

ኢትዮጵያ ደርሶ የሚመጣ የውጭ ሀገር ነዋሪ (ደርሶ መልስ ዲያስፖራ) በተለያየ አይነት እይታ የተለያዩ እውነታዎችን ይዞላችሁ ይመጣል።

አንዳንዱ የህንጻውን ግንባታ አዳንቆ ሲያወራ፤ ሌላው ስለጭፈራ ቤቶች ይዘክራል። ጓደኞቹን በስራ ብዛት ሊያገኝ እንዳልቻለ የሚያወራላችሁ እንደመኖሩ ሁሉ በስራ አጥነት ችግር የተነሳ ዱርየ መበራከቱን የሚተርክላችሁ አታጡም። የቆነጃጅቶችን ውበትና የዳንኪራ ቤቶችን ሁናቴ የሚነግራችሁ፤ በየቡና ቤቱ ብሎም በየትምህርት ቤቱ ያሉ ወጣቶችን ችግር ያስረዳችኋል። የሀገሪቱን እድገት በኮንስትራክሽን መጥለቅለቅ የሚያጫውታችሁ፤ በመንገዱን መቆፋፈር ሰው ስለመማረሩ በማንሳት ያትትላችኋል። አዲስ አበባን በመመስረት ላይ እንዳለች ታላቅ ከተማ አድርጎ የሚተርክም አታጡም።

ይሄ ሁሉ እንደ እድገት በአንዲት መንግስት የሚባል አካል አላት በተባለች ሀገር መታየቱ ምኑ ይገርማል?። አንዳንዴ ሀገሩን አይቶ ዘመድ ወዳጅ ጠይቆ መምጣትም ሆነ ሰው ሀገሩ ደርሶ መመለሱ እጅግ መልካም ነገር ነው። ያየውን ግልብ ነገር ከራሱ አይን ጥግ ስር አንጻር ብቻ ተመልክቶ በሰዎች ላይ የሚደርስን ስቆቃ ሸፋፍኖ ያለጥናት የተሰሩ መንገዶችንና ህንጻዎችን እንደትልቅ ለውጥ ማውራት ግን የሞራል ጥያቄን ያመጣል።

በእርግጥ የውብ ሀገር ነችና ውቦች ሊኖሩ ይችላሉ። መሸታ ቤቶቹም ደማምቀው ሊሆን ይችላል። ህንጻ ግምባታውም ቢጧጧፍ አያስነውርም። መንገዶች ተንጣለው ቢታዮም ጸጸት የሚገባው የለም። ነገር ግን ሰው በቀላሉ ቆሎ ሽጦ ይኖርበት ከነበረ መንደር ተባሮ መግቢያ ያጣበት ሀገር፤ ውሃ ልማት የቆፈረውንና ውሃ ቧንቧ ቀብሮ ያበጀውን መንገድ ነገ ቴሌ የሚያፈርሰው ከሆነ… ከዚያም ማዘጋጃ ቦይ ተደፈነ ብሎ ከተረተረው… ወጣት እንስት ህጻን ታናሽ እህቷንና ወንድሟን ትምህርት ቤት ለመስደድ መንገድ ከወጣች፤ ጥቂት የባለጊዜ ልጆች የሚሰሩት አጥተው በተንፈላሰሱባት ሀገር መለመንን ተጠይፈው ዱሮ የነበራቸውን ጽዱ ልብስ ለብሰው ፊታቸውን የከለሉ ሰዎች በየጥጋጥጉ የሚለምኑባት ሀገር ከሆነች… አባት ትምህርት ቤት ብሎ የላካት ወጣት በኮሌጅ ያለውን ፍላጎቷን ለማሳካት ገበያ መውጣት… ዘግናኝ ነው…

የሚሰራው መንገድ ተሸርሽሮ ከአመት በላይ አገልግሎቱ አልቆለት ተቦርቡሮና ውሃ ቋጥሮ የሚታይበት ሀገር እየገነቡ መሰረት መጣል አይቻልም ነው ጥያቄው። ደረጃቸውን ባልጠበቁና በይድረስ ይድረስ የተሰሩ ህንጻዎች ጋጋታ የከተማንም የሀገርንም እድገት ሊያሳዩ አይችሉም ነው እየተጮኸበት ያለው ነገር። ፍትህ ራሷን ችላ የምትራመድበትን ሀገር የሚመራ መንግስት ይኑር ነው ልፈፋው። የህወሃት ሰዎችና ጥቂት አሸርጋጆች የሚያደርጉት አገራዊ ጥፋት ይቁም። ልጆቻችን እርስበርስ የዚህና የዚያ ብሄር ወይንም ከወዲያ አለዚያም ከወዲህ መንደር የመጡ እየተባባሉ በጥርጣሬ እየተያዩ የሚኖሩበትንና የሚያድጉበትን ሀገር እናፈራርስ ነው እሪታው። የህወሀት አለያም ጥቂት ሽርጉደኞች በገፍ የሚገነቧቸው ህንጻዎች ከሙስና ባሻገር ሆኖ ራሳቸው ኢንጂኒዬርና አርክቴክት ሆነው የሚገነቡት ሀገር ሀገር አይሆንም ነው ጉዳዩ።

22 አካባቢ የተሰራው ጎላጎል ህንጻ ባለጊዜው ባለቤት ህንጻውን ሲያስገነባ ዋናው መንገድ ውስጥ መግባቱን ያየ መሀንዲስ ወይንም ኢንጂኒዬር ‘አግባብ አይደለም፤ ወደፊት መንገድ ይዘጋል’ ብሎ ምክር ቢሰጠው ‘እኔ ያልኩህን አድርግ’ ብሎ ጀርባውን የተማመነው ባለቤት ሲያዘውና ያ ባለሙያ የታዘዘውን በማድረጉ ግንባታው ከተጠናቀቀ በኋለ አሁን መንገዱን የዘጋውን ህንጻ የሚደፍረው ጠፍቶ፤ መረማመጃው ዘግቶ መታየቱ የሚወራው ዝም ብሎ ከመሬት ተነስቶ አይደለም።

አሁንማ የህወሃት ሰዎች እጅግ ከመድፈራቸው የተነሳ አዲስ አበባ ውስጥ በስማቸው ሆኗል ፎቅ የሚያስገነቡት ተክላይ ህንጻ፣ ገብረጻዲቅ ህንጻ… ብሎ ያጫወተኝ ወዳጄ ታዲያ ምን ችግር አለው? ስለው ‘ምንም ችግር የለውም በህዝቡ ውስጥ ግን የማህበራዊ ህይወት መራራቅንና ሃሜትል ያስከትላል ብሎም ህዝቡን እነሱ እና እኛ የሚያስብል የሳይኮሎጅ ጣጣ ውስጥ ከቶታል።” አለኝ

ሀገሪቱን የህወሃት ጄኔራሎችና መኮንኖች ብቻ በሀብት የወረሯት ሀገር ተሸክሞ የት እንደሚደረስ ማሰብ ሰው መሆን ነው። ይህ ወዳጄ ታዲያ በአንጻሩ የሽንኩርትን ገበያ ለማየት ጉሊት ወርዶ ያየውን ጉድ በልኩ አስተውሎ መጥቷል። አንድና ሁለት ራስ ትንንሽ ሽንኩርት አልያም ቲማቲም ለሳምንት ለማብቃቃት የሚሰቃይ ህዝብን ይዞ ጉዞው የት ነው የሚያደርሰን።

የአገሪቱን የዘር ችግር ጥግ ላይ መድረስ ባለፈው 767 አውሮፕላንን ይዞ ጄኔቫ የገባው ወጣት ረዳት አብራሪን በሚመለከት መግለጫ የሰጡት ሬድዋን ሁሴን “ጠላፊው ከየት ነው?’ ተብለው ሲጠየቁ ‘ኢትዮጵያዊ ነው’ ብለው ሲመልሱ አረ ከየትኛው ክልል ተብለው መጠየቃቸው ጉድጓድ ውስጥ የሚከት ቅሌት ነው። መልሳቸውም እረሪሪሪሪሪ የሚያስብል ነበር። ‘ከየትኛው ብሔር እንደሆነ አልታወቀም።’

መጠጥና ዳንኪራ ቤቶች

ከ5 ሚሊየን ህዝብ በላይ (እስከ 8 ሚሊዮን ይገመታል) የሚኖርባት አዲስ አበባ የጭፈራ ቤቶችን ብዛትና የጨፋሪውን አይነት የነገረኝ ወዳጄን ቀኑን ሙሉ ሲተራመስ የሚውለው አዲሳቤ በጊዜ በ12 ሰዓት ከቶ በየፊናው ሲገባ ከተማው ምን ያህል ጭር እንደሚል አላስተዋለም። 100 የማይበልጡ ምሽት ቤቶች (አጋንኘው ነው) 100 ሰው እያንዳንዳቸው ቢያገኙና ቢያስጨፍሩ 10ሺህ ሰው… እንጨምረው እና 50ሺህ ሰው በምሽት ስለጨፈረና ስለደነከረ ሀገር በጥጋብ እንደዘለለ ማውራት ነውር ነው ነው ጨዋታው። ይሄንኑ ግምት እናስላው ከተባለ የገዥው ህወሃት/ኢህአዴግ ባለስልጣናትና ጥቅም ተሻራኪዎች 70 በመቶውን ቢያነሱ 15 በመቶ በዲያስፖራና ዘመዶች እንዲሁም የተቀረው ለፍቶ አዳሪ አለያም ከቤተሰቡ የሚቃርም ሊሆን ይችላል።

ለነገሩማ የዘመነኞቹ ሰዎች ልጆች የሚገቡበት ቡና ቤት ውስጥ ቀድሞ የገባ ሌላ ደንበኛ ሾልኮ እንዲወጣ የሚደረግባት ምድር። በድርድር የታሰረ ብር ለአስተናጋጅ ተሰጥቶ ቆጥረሽ ውሰጅ የሚል ረብጣው ያጨናነቀው የዘመኑን ሰው ማየት የተለመደ መሆኑንም እየሰማን ነው።

ምን እዚህ እኛ በብርድ እየወጣን ሰላማዊ ሰልፍ እያልን እንጮሃለን እነሱ ሚሊየነሮች ሆነዋል ያለኝና ሀገር ቤት ሄዶ በጓደኛው የቀና ሰው ያጫወተኝም አለ። ያ ጓደኛው ከዘመንኛ ሰዎች ጋር ገጥሞ ህዝብ እየቦጠቦጠ መሆኑን የነገረኝ ደርሶ መልስ ዲያስፖራ… አሁንም እዚህ ኖርዝ አሜሪካ ከተመለሰ በኋላ እዚያው አገር ቤት ቢሆን እንደጓደኛው ሚሊየነር ይሆን እንደነበር ሲያወጋኝ በመቆጨት ነበር። ዘመንኞቹና ጓደኛው የሚቦጠቡጠው ህዝብ ስቃይ በሚሊየን ብር ተጋርዶበት። አረ እየተስተዋለ! እዚያኮ ሀገር እየተቆራረሰ ነው! አረ ስለአምላክ! ሀገሪቱም በመንደር እየተተበተበችኮ ነው! ስለእመብርሃን! ምድራችን ፍትህ የጠፋባት ሆናለችኮ! በሽብርተኛ ስም ስንቱ ታጎረ… አረ ስለአላህ! ሰው ኑሮ መረረኝ እያለ ነው እኮ! እንኳን ከአሜሪካ ከመንግስተ ሰማያትም አመጣኻለሁ የሚል ለስራው ብቁ ያልሆነ ሰው የሚሾምበት ሀገር ውስጥ የሚኖር ህዝብ እኮ ነው የያዝነው። ጭራሽ የሶማሌ ክልል ባለስልጣን ይባስ ብሎ ምኒባስ ታክሲ በከተማ እንዳይገባ ብሎ በራሱ ስልጣን አግዶ እገዳውን የጃፓን መንግስት ቢመጣም እንኳን አልቀበልም እያለ እኮ ነው ጎበዝ… ሰሚ የለም እንዴ በግዜር!?

ለዛሬ ላብቃ!

ቸር ለእናንተ!!!

ሙሰኞችና “ሙሰኛው” ፀረ ሙስና

$
0
0
(ናትናኤል ካፕትይመር)

(ናትናኤል ካፕትይመር)

ናትናኤል ካብትይመር (ኦስሎ ኖርዌይ)

. . . . . . .የኢትዮጲያ ፀረ ሙስና ኮሚሽን የህዝብንና የመንግስትን ንብረት ለግል ጥቅማቸው በማዋል ክስ የመሰረተባቸውን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን  . . . . . . የኢቲቪ ዜና

. . . . . ጉድ ፈላ በቃ ቀጥሎ ሴትዮዋ ነች  . . . . . የዋህ ኢትዮጲያውያን

. . . . . . . እባካችሁ በጥቂት ሺህ ብሮች የወር ደሞዝ የህዝብ አገልጋይ ነን እያላችሁ የሰባት ሚሊዮን ብር መኪና አትንዱ . . . . .” አፈጉባኤው

. . . . . . .የቀድሞው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሙስናን በማጋለጥ ጋር በተያያዘ በታሸገ ውሃ ተመርዘው ነው የሞቱት መባሉን ባናረጋግጥም ከቅርብ ግዜ ወዲህ ግን በኦሮሚያ ክልል መንግስታዊ ስብሰባዎች የታሸገ ውሃ መቅረብ መቆሙን አውቀናል  . . . . . . ለስርዓቱ እጅግ የቀረቡ የመንግስት ጋዜጠኞች
alemayehu atomsa
ባለፈው ሰሞን ጥቂት የመንግስት ባለስልጣናት በሙስና ሰበብ ተብሎ ዘብጥያ ሲወርዱ የታሳሪዎች ቁጥር ከወትሮው ለየት በማለቱ ፀረ ሙስና ስራውን ጀመረ ብለው ተስፋ የጣሉ ኢትዮጲያውያን ጥቂት አልነበሩም። እንደው የህዝባችን የዋህነት ነው እንጂ ፀረ ሙስና ከተመሰረተ ጀምሮ አንድም ቀን እንደስሙ ስራውን ሰርቶ እንደማያውቅ ፣ ጥቅሙም ሌላ እንደሆን የታወቀ ነው። እንጂማ ገና ያኔ እነ አቶ ታምራት ላይኔ ፣ እነ አቶ አባተ ኪሾ የመሳሰሉት በሙስና ሰበብ ወደ እስር ሲወርዱ በህዝብ ገንዘብ ጠግበው የደለቡ የመንግስት ባለስልጣናትና አጋፋሪዎቻቸው የውስኪ ብርጭቆአችውን እያጋጩ ሲሳለቁ ማንም የነካቸው አልነበረም። ምክንያቱም ነገሩ ሌላ ነው። የፀረ ሙስና ኮሚሽንም ለመንግስት የሚሰጠው ጥቅም ሌላ ነው።

ሁሌ ሳስበው የሚያስገርመኝ እንደ ህወሃት መንግስት የተለያዩ አለማቀፋዊ መሰረት ያላቸውን ህግጋትና ደንቦች ለራሱ የስልጣን እድሜ ማራዘሚያ እየሸነሸነ የሚያውል መንግስት ያለ አይመስለኝም።

የኢትዮጲያ ፀረ ሙስና ኮሚሽንን የህወሃት መንግስት ሲያያቸው ያላማሩትን ፣ የውስጥ ጉዱን የሚያወጡበት የመሰለውን የገዛ ባለስልጣናትና ሹመኞቹን ማስወገጃ አርጎ ይጠቀመዋል ፥

የፀረ ሽብር ህግን ህዝብ የወደዳቸውን ፣ አካሄዳቸው ያሰጋውን ፣ እውነትን ለህዝብ የሚያጋልጡትን ጋዜጠኞችንና አማራጭ የፖለቲካ ሃሳብ አመንጪ አካላትን ማስወገጃ አርጎ ይጠቀመዋል ፥

መሰረታዊ የስራ ሂደት ለውጥን (Business Process Reengineering) የህወሃት ካድሬዎችንና በሲቪል ሰርቪስ በኢሃዴጋዊ አገዛዝ ያጠመቃቸውን ጆሮ ጠቢዎች በየመንግስት መስሪያ ቤቶች ለመሰግሰግ ይጠቀመዋል ፥

አገር አቀፍ የመረጃ ደህንነት ጥበቃ (National Information Network Security) ሲስተሙን የተለያዩ የዜና አውታሮችንና ድረ ገፆችን በሃገር ውስጥ እንዳይታዩ ለመዝጋትና አማራጭ የፖለቲካ ሃሳብ አመንጪ አካላትን መረጃ ለመበርበሪያ ይጠቀመዋል ፥

አንዳቸውም ለተፈጠሩበት ፍልስፍና በሃገራችን በአግባቡ ስራ ላይ ሲውሉ አይታዩም : ሌሎችም ብዙ አሉ።

“ኧረ ይሄ አሰራር መጥፎ ነው” ሲባል ዋናውን ጥያቄ ሆን ብሎ በማድበስበስ “ህጉን የገለበጥነው በቀጥታ ካደጉት ሃገራት ነው” ይባልና ያልተጠየቀው ይመለሳል።

“የለም የለም ህጉን አተረጓጎማችሁ ልክ አይደለም” የሚል ጫን ያለ ጠያቂ ሲመጣባቸው “መጠነኛ የአፈፃፀም ችግር ስላለ ነው በቅርቡ እንቀርፋለን” ይላሉ ከዛሬ ስንት አመት ጀምሮ።

ወደ ዋናው ሃሳቤ የሙስና ጉዳይ ልመለስና በአንድ ወቅት ከአንድ ጋናዊ ጓደኛዬ ጋር ስለ አህጉራችን አፍሪካ መሪዎችና ባለስልጣናት መረን የወጣ ሙስናና ገንዘብ መውደድ ባህሪ ስንወያይ በማልረሳው መልኩ እንዲህ አለኝ

“የሚገርምህ በምሳሌ ባስረዳህ የአፍሪካ ሃገራት ፕሬዝዳንትና ጠቅላይ ሚኒስትር በሃገራቸው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ሲወያዩ ‘. . የሚያስፈልገን ከሃምሳ ሚሊዮን ዶላር በላይ ነው ስለዚህ እነዚህን ሃገራት ብድርና እርዳታ እንጠይቃለን በተጨማሪም ከህዝቡ መዋጮ እንጠይቃለን . .’ ብለው ስብሰባውን ይቋጫሉ ነገር ግን ሁለቱም እያንዳንዳቸው ከመቶ ሚሊዮን ዶላር በላይ በአውሮፓና አሜሪካ በሚገኙ ባንኮች በድብቅ እንዳስቀመጡ ይተዋወቃሉ።  መሪዎቻችን ከግለኝነትና ከስግብግብነት ካልወጡና ከነዚህም ችግሮች የፀዳ አመራር ካላገኘን ገና የአፍሪካችን መከራ ብዙ ነው” አለኝ።

እኔም የሃገሬ መንግስት ከቀበሌ ጀምሮ የሾማቸው ሹመኞችና ባለስልጣናት ፣ የሚነዷቸው መኪኖች ፣ የሚኖሩበት ውብ ቪላዎች ፣ ታማኝ ምስኪን የመንግስት ሰራተኞች ፣ እንደ ቁመናው ያላማረበት የፀረ ሙስና ኮሚሽን ህንፃ ፣ የኢቲቪ ሙስና ነክ ዜና በቅፅበት በአምሮዬ ውልብ ውልብ እያሉ አለፉ።

በኢትዮጲያ የመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ አነስተኛ መሆኑን ሁላችንም እናውቃለን። በተያያዘም የመንግስት ባለስልጣናትና ሹመኞችም የመንግስት ሰራተኞች መሆናቸውንም እናውቃለን። ይህ ማለት ደግሞ የመንግስት ባለስልጣናትና ሹመኞች ደሞዛቸው ከመንግስት ሰራተኞች እኩል በመንግስት የደሞዝ እርከን መሰረት ነው ማለት ነው። ሌላው የመንግስት ሰራተኛ በኑሮ ውድነት ናላው ሲዞር ባለስልጣናቱ ግን ደሞዛቸው ስንት እንደሆነ እንኳን አያውቁትም ምክንያቱም የገንዘቡ መጠን የሚነዱትን የሚሊዮኖች ብር መኪና የቀናት ነዳጅ እንኳን አይሸፍንም ፥ ታዲያ ማወቁ ምን ያረግላቸዋል።

ደሞዛቸው ትዝ የሚላቸውና ብዙ ግዜ በርካቶቻችንን የሚያስገርመንና በቁጭት ፈገግ የሚያስብለን የገቢ ማሰባሰቢያ ወይም ቴሌቶን ሲዘጋጅ “ክቡር ሚኒስትር እከሌ የአንድ ወር ደሞዛቸውን ሰጥተዋል ሞቅ ያለ ጭብጨባ” ሲባል ወይም የሚንስትሮቹ ሚስቶች ምን ያህል ቆጥበው ፣ ለፓርቲያቸው አዋጥተው ፣ ተቸግረው ፣  ተቸጋግረው ፣ ልጆቻቸውን እንደሚያስተምሩ ሲያወሩ ነው።

ኧረ ይሄ ነገር ልክ አይደለም ሲባል ፥ “ሃገር ለማሸበር” ወይም “የጥላቻ ፖለቲካ” ይባላል። ሲጀመር ውል ያለው የፖለቲካ ስርዓት የህወሃት መንግስት የለውም ሲቀጥል . . . . . . . .ግድ የለው አሁን ከዋናው ርዕሴ አልውጣ።

በርካታ የመንግስት ሹመኞችና ባለስልጣናት ቢሮ እንደው እግር ጥሏችሁ ከሄዳችሁና ቀና ብላችሁ አስተውላችሁ ከሆነ በግርግዳቸው ላይ የለጠፏት ወረቀት “ታማኝነት ፣ ግልፅነት ፣ የህዝብ አገልጋይነት ፣ ቅንነት ፣ የመሳሰሉት ውብ ቃላቶች” በተርታ ተለጥፈው ይታያሉ ነገር ግን ዝቅ ብላችሁ የሹመኛውን ወይም የባለስልጣኑን ፊት ስትመለከቱት “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል” የሚባለው አበው ለምግብ ይሁን ለህዝብ ገንዘብ በውል ሳይለዩ ያወረሱን ብሂል ሁለመናውን ወርሶት ታዩታላችሁ። ሹመኛና ባለስልጣን እየተፈራረቀ “ምነው በኔ ተጀመረ እንዴ” እየተባባለ ያችን ምስኪን ሃገር ይግጣል።

ሙስናና ንቅዘት በሃገር ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊም ሆነ ዲሞክራሲያዊ እድገት ላይ ያለው አሉታዊ ተፅእኖ እጅግ ብዙ ነው። ስልጣንን መከታ በማድረግ የሚገኝ ገቢ መዘዝ የሃገርን ሃብት በማውደም ብቻ አያበቃም። የመንግስት ስልጣንና ሹመት ሃገርንና ህዝብን ማገልገል መሆኑ ይቀርና የቤተሰብ እንዲሁም የዘመድ አዝማድ የገቢ ምንጭና ህልውና ወደመሆን ይሸጋገራል። በዚህም ሳቢያ ደግሞ በተገቢው መልኩ የአገልግሎት ግዜ ሲያበቃ በሂደት የመተካካት ፣ ለተተኪው ስልጣንን ማሳለፍ ወይም መልቀቅ የሚለው መሰረታዊ የዲሞክራሲና የሃገር እድገት መርህ ይጣስና ስልጣንና ሹመት የቤተሰብና የዘመድ አዝማድ የኑሮ ምሰሶ ሆኖ ስለሃገር እድገት ማሰብ በራስ ወዳድነትና በግለኛ የማይጠረቃ ፍላጎት ይተካና ስልጣን ወይም ሹመት ላይ እስከወዲያኛው ሙጭጭ ማለትን ያመጣል።

በቅርቡ የተካሄደው የኢህአዴግ ስብሰባ  “ . .  የፓርቲያችን ዋናው ችግር ሙስናና አድር ባይነት ነው ስለዚህ . . . “

የሚቀጥለው የኢህአዴግ ስብሰባ “ . . . . ባለፈው ያልናችሁ ዋናዎቹ ችግሮቻችን ሙስናና አድርባይነትን የምንዋጋበትን እቅድ በአፋጣኝ በሚቀጥሉት አምስት አመታት ውስጥ እናወጣለን  . . . . .”

እኔ በዚህች ላብቃ  . . . . . መስናና ዘረፋው ግን አምሮበት እንደቀጠለ ነው።

natnaelkab@gmail.com

 

በለው! ቄንጠኛ ዳንስ በዕንባ ሲደንስ

$
0
0

haile Mariam Desalegn 1

ሥርጉተ ሥላሴ 13.03.201 (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

siraateምን አለባቸው አልሞተባቸው፤ ጥቁር አለበሱ፤ የተራበ ወግን የላቸው፤ የታሰረ ሥጋ የላቸው፤ ባለጊዜ እንዲህ በቄንጥ ዳንሱን ያስነኩት፤ ይጨፍሩ! በጣም አምሮባቸዋል! ተዋጥቶላቸዋልም። ሂዶላቸዋልም። ሚሊዮኖች ጉርሻ ፍላጋ ለትራፊ በረድፍ ተሰልፈው ከጠኔ ጋር ተፋጠዋል። ሚሊዮኖች ከቦታ ቦታ ተራ ዜጋ ናችሁ ተብለው ይፈናቀላሉ። ሺዎች „ኢትዮጵያዊ“ እተባሉ በዬአረብ ሀገሩ እዬተነጠሉ ይታረዳሉ፤ ይደፈራሉ፤ ወንዶችም ይሰለባሉ – ይደፈራሉም፤ በፍል ይቀቀላሉ፤ በፎቅ ይፈጠፈጣሉ። በገጀሞ ይከተከታሉ —- ይታረሳሉ፤ ቄንጠኛው ደግሞ ዳንሱን እንዲህ ያስነኩታል ….

አዎን! በሺህ የሚቀጠሩ ዜጎቻችን ዜግነታቸው የትኛው ሊሆን እንደሚችልም መላ አጥተው ዛሬ ይታመሳሉ። የሱዳን ወይንስ የኢትዮጵያ? የሱዳን መንግሥትና የወያኔ የሽፍታ አስተዳደር የሚስጢሩ ድርድር „ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ ሆኗል።“ ቀንደኛው ሄሮድስ መለስ አፈር ሊያጫውቱ ቢሄዱሙም ጨፋሪው አቶ ሃይለማርያም ደግሞ በሙት መንፈስ ፈረስ እየጋለቡ ታሪክ ይቅር የማይለው አርበኝነትን፤ ታሪክን ማንነትን የዳጠ፤ የጠቀጠቀ ተግባር ፈጸሙ፤ ይንንም ሐሤት አድርገው የፍንጥሩን የልባቸውን ሞልተው የለ ምን ሲገዳቸው፤ እንዲህ ፍለቅልቅ ብለው ይደልቃሉ። በችርስ ይዘንጣሉ። ሳቅ በእናት ኢትዮጵያ ምድር ከገጠር እስከ ከተማ በፈለሰበት ዘመን ከሳቸው ቤት የበቀል ፈገግታ በገፍ እንዲህ ይመረታል – ወይ ነዶ! አሁን ዳንስስስስስ! ህም!

ሚሊዮኖች አስፓልትን ተጠልለው ነገን በሞት ይጠባበቃሉ። የኑሮ ዋስትና፤ የጤና ዋስትን፤ የመማር ዋስትና የላቸውም። የዕምነት አዛውንቶች ካለ ባህላቸውና ትውፊታቸው ስደትን የሙጡኝ ብለው እንደከሰሉ ያልፋሉ። ሀገርም ያሉት የጸሎት ቤታቸው በስጋት ተወጥሮ ከሞቱት በላይ ካሉት በታች ሆነው ተሳቀው ይኖራሉ። ዳንሰኛውም ደግሞ ዳንኪራቸውን እንዲህ መሬት አይበቃኝ ብለው መድረኩን ቀውጢ አድርገው ያስነኩታል …. ፍርሰት —

ለእለት ጥም ጠብታ ማርኪያ የሚማስኑ ዕልፎች ናቸው። እንደተቆለፈባቸው ጧሪና ጠያቂ አጥተው ትውልዱን ረግመው የሚሰናበቱንም እጅግ በርካታ ናቸው። ቄንጠኛው ዳንሰኛ አቶ ሀይለማርያም ደግሞ ሞቅ ብሏቸው፤ ጥጋቡም አላስችል ብሏቸው እንዲህ ይሉታል …. ማላጋጥ … ምልገትም —-
tedrows
ጠቀራ የለበሱ ቀናት ረሃብን እያወጁ፤ ስጋትን ነጋሪት እዬጎሰሙ፤ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ጎጆ እንደ ጉድ ይተማሉ። ቅብጠት ያመራቸውና ያልወጣላቸውም ጠቅላይ ሚኒስተር ሃይለማርያም ደሳለኝ ደግሞ ክርስትናውን ባፍ ጢሙ ብለው ይደልቁታል። ሁሉም አይቅርብኝ በማለት ከተቃራኒ ፆታ ጋርም የዐይን ፍሰቱንም ሆነ የእግር ዳንኪራውም እንዲሁም የመንፈስ ኮማውም …. በአንድነት በመደዴ ያስኬዱታል —- እርግማን!

አሁን ያን የሳውዲ ሰቆቃ ያዬ ፍጡር ዳንስ? ፈንጠዝያ?! ውቂ ደብልቂ?! እፍረት ነው። እውነት ለከፈን፤ ለመጠለያ፤ ለጉሮሮ ያልበቃች በብድር የተነከረች ሀገር እዬመሩ እንዲህ ሃላፊነት የጎደለው የአደባባይ ጥቁር ትዕይንት ማሳዬት እጅግ አንገት ያስደፋል ህሊና ላለው ሰው። „ባልወለድ“ ማለት የነበረበችው እርሳቸው ነበሩ ግን … በዬትኛው ህሊና?

ለነገሩ ምን አለባቸው እሳቸው አልጎደለባቸው። ፈሰስ ብለው ይኖራሉ። እልፎች ድምጻቸው ታፍኖ መተንፈስ ሲጀምሩ እዬተለቀሙ ለእግር ብረት ይዳረጋሉ። ልጆች ካለወላጅ፤ ጎጆም ካለ ጉልቻ፤ ትውልድም በነጠፈ ተስፋ 23ዓመት እንደዋዛ … ወገን ደም እንባ እያለቀሰ ታፍኖ፤ ተከዝኖ የሞት ቀናትን ይጠብቃል። ናፍቆት እስክንድርና መሰሎቹ ህጻናት ደግሞ ወላጆቻቸውን ተነጥቀው በሰው ሀገር ናፍቆታቸውን ሰንቀው ባልበሉት እዳ ይታሻሉ። ክልትምትም ይላሉ። አቶ ሃይለማርያም ደግሞ ከመላ ቤተሰባቸው ጋር የልጆቻቸውን ፍቅር ጠዋት ማታ እዬኮመኮሙ ጥጋቡ አላስችል ብሏቸው እንዲህ በመከራ ላይ፤ በግፍ ላይ ይጨፍራሉ ትዝብት ነው ….

ክውና — እረኛ ያጣ ህዝብ፤ ሙሴ የሌለው ትውልድ፤ ባላቤት የሌላት ኢትዮጵያ በፈላ እንባ እስከ መቼ ይሆን መቀቀሉን የሚቀጥሉት? ፈጠሪ አምላክስ መቼ ነው ፍርዱን አደላድሎ በቃችሁን የሚያውጅው!?! ….. ለግፍኞች፤ በእንባ ጨፋሪዎችስ ላይ ቅጣቱን አከታትሎ መቼ ነው የዶግ አመድ አድርጎ ብን የሚያደርጋቸው …. ? መቼስ „ተስፋ“ አያልቅ ደግሞ እንደ አመላችን „ተስፋ“ የሚባለውን እንጠብቅ ወይንስ ከእሱ ከራሱ „ተስፋ“ ከሚባለው ልብ አንጠልጣይ ጉድ ጋር ጦርነት እንግጠም ይሆን?

በሉ የኔዎቹ በዚህች ቆራጣ መጣጥፍ ትንፋሽ — የውስጤን ቁስለት በማሳዬት ተብተከትኩ። ለነበርን መልካም ጊዜ አመሰገንኩ – በፍቅር። ደህና ሰንብቱ።

እልፍ ነን። እልፍነታችን በተግባር እልፍ እናድርገው።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

“የኦነግ ጭፍጨፋ ተብለው ከሚጠቀሱ ትራጄዲዎች መካከል አብዛኛዎቹ በኦነግ የተፈጸሙ አልነበሩም”–ከአፈንዲ ሙተቂ

$
0
0

olf flag
ከአፈንዲ ሙተቂ

——
“ዳውድ ኢብሳ ሲሞት ጥሩኝ” በሚል ርዕስ በለጠፍኩት አነስተኛ ሐተታ ላይ ሁለት ዓይነት ተቃውሞዎች ቀርበውብኛል፡፡ አንደኛው “ኦነግ በአማራው ላይ የሰራውን ሴራ እና ሸፍጥ እያወቅክ ጥብቅና ቆመህለታል” የሚለው ሲሆን ሁለተኛው “የኦፒዲኦን ድርጅታዊ ህልውና አንኳሰስክ፤ አቶ አለማየሁንም ረገጥክ” የሚል ነው፡፡ ስለ ኦፒዲኦ የጻፍኩት አዲስ ነገር አይደለም፡፡ የድርጅቱ አባላት እራሳቸው በየአጋጣሚው የሚናገሩትን ነው በፌስቡክ የደገምኩት፡፡ በተለይ ደግሞ አባላቱ ከስራቸው ሲባረሩ፣ ወይ ደግሞ ከድርጅቱ ከድተው ወደ ውጪ ሀገር ሲኮበልሉ “ኦፒዲኦ የኦሮሞን ህዝብ ለማጭበርበር ሆን ተብሎ የተፈጠረ ድርጅት ነው” የሚል ጩኸት በማሰማት ነው የሚታወቁት፡፡ እነ ዮናታን ዲቢሳ፣ ዱባለ ጃሌ፣ ኢብራሂም መልካ ሲያደርጉት የነበረው ይህንኑ ነው፡፡ ነገር ግን እኔ የነርሱን ፈለግ በመከተል አይደለም እንዲያ ብዬ የጻፍኩት፡፡ ከነርሱ በፊትም እንደዚያ ስል ነበር፡፡
——
ኦነግን ለመጀመሪያ ጊዜ ካየሁበት ግንቦት 1983 ጀምሮ የድርጅቱን የፖለቲካ መስመር ስደግፍ ቆይቻለሁ፡፡ ዩኒቨርሲቲ ስገባ ግን ድርጅቱ በሚያራምደው ርዕዮተ ዓለምና በፖለቲካ ፕሮግራሙ ላይ ጥያቄዎች ማንሳት ጀመርኩ፡፡ በዋነኛነትም “የመገንጠል ፖለቲካው የኦሮሞን ጥያቄ የትም አያደርሰውም” የሚል ሀሳብ አነሳሁ፡፡ እንዲሁም የሚከተላቸው ስትራቴጂዎቹ ፍጹም ሊዋጡልኝ አልቻሉም፡፡ በዚህም ከኦሮሞ ወንድሞቼ ጋር ብዙ ጊዜ እነታረክ ነበር፡፡ በተለይም በዚያ ጊዜ ኦነግን መተቸት Taboo ተደርጎ ይቆጠር ስለነበር ከቅርብ ጓደኞቼ ጭምር እስከመጣላት ደርሰናል፡፡ እናም ከ1990 ጀምሮ የድርጅቱ ተቃራኒ እንጂ ደጋፊ አይደለሁም፡፡

እንዲህ በመሆኑ ግን ድርጅቱን በሐሰት መክሰስ ያለብኝ አይመስለኝም፡፡ ድርጅቱን በሰራው ጥፋት ብወቅሰው ማለፊያ ነው፡፡ ባልሰራው ወንጀል መክሰስ ግን ለማንም የሚበጅ አይሆንም፡፡ እንደምሳሌም ኦነግ የሚከሰስባቸውን ጭፍጨፋዎች እንመልከት፡፡ በደኖ፣ አርባ ጉጉ፣ ወተር፣ አረካ፣ አሰቦት ገዳም ወዘተ…

እነዚህ ጭፍጨፋዎች መከሰታቸው ሁላችንንም ያሳዝነናል፡፡ አንድ ቀን እውነቱን ፈልፍለን የማውጣት ግዴታም ተጥሎብናል፡፡፡ ነገር ግን በርካታ ሰዎች በሁሉም ጭፍጨፋዎች ኦነግን ተጠያቂ ሲያደርጉ በጣም እገረማለሁ፡፡ በተለይም ዛሬ በህትመት ላይ የሌሉ ሁለት የግል ጋዜጦች ይህንን ፕሮፓጋንዳ እየደጋገሙ ሲያስተጋቡት ሳይ “ስለ የትኛው ሀገር ነው የሚያወሩት” እያልኩ እደነቅባቸው ነበር፡፡ እንዲህ የምለው ጋዜጦቹ የመረጃ እጥረት የነበራቸው መሆኑን በማወቄ ብቻ አይደለም፤ የጂኦግራፊ እውቀትም ያጠራቸው ስለሚመስለኝም ጭምር ነው፡፡ ለምሳሌ “አረካ”ን እንውሰድ፡፡ ይህቺ ከተማ የት ነው ያለችው? ኦሮሚያ ውስጥ ነው? ወይስ ሌላ ቦታ?

ይገርማል! አረካ ማለት በደቡብ ክልል በወላይታ አውራጃ ከሶዶ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ ያለች ከተማ ናት፡፡ እኔ እስከማውቀው ድረስ ኦነግ እዚያ ድረስ ሄዶ ሀገር አላስተዳደረም፡፡ “አረካ የኦሮሚያ ግዛት ናት” ብሎ የሚያውቅም አይመስለኝም፡፡ እናም ጂኦግራፊን በትክክል የሚያውቅ ጋዜጠኛ የአረካውን ግጭትና ጭፍጨፋ ለኦነግ አይሰጥም ነበር፡፡ በተጨማሪም የአረካው ግጭት የደረሰው ኦነግ የሽግግር መንግሥቱን ለቆ ከወጣና በእጁ የነበሩት መሬቶች በሙሉ በኢህአዴግ ቁጥጥር ስር ከወደቁ በኋላ ነው፡፡

የአረካው ግጭት በሽግግሩ ዘመን ለነበረው የተወካዮች ምክር ቤት የውይይት አጀንዳ ሆኖ እንደቀረበ ይታወሳል፡፡ በከተማዋ ያለቁት የ31 ሰዎች ግድያ በመከላከያ ሰራዊቱ እንደተፈጸመ መንግሥቱ በይፋ አምኗል፡፡ ዳሩ ግን ለግድያው የተሰጠው ምክንያት በጣም አነጋጋሪ ነበር፡፡ መንግሥት ያቀረበው ምክንያት “ሰልፈኞቹ የተገደሉት ቦንብ በመወርወራቸው ሳቢያ የመከላከያ ሰራዊቱ ራሱን ለመከላከል በወሰደው እርምጃ ነው” የሚል ነው፡፡ ይሁንና ይህንን ምክንያት ብዙዎች አልተቀበሉትም፡፡ ብዙዎች እንደተጠራጠሩት እስከ ዛሬ ድረስ ቆይቷል፡፡ በነገራችን ላይ በአረካ የሞቱት የቀድሞ መንግሥት ወታደሮች ነበሩ፡፡ እነዚያ ወታደሮች “የጡረታ መብታችን ይከበርልን” በማለት የተቃውሞ ሰልፍ በማድረጋቸው ነው ከመከላከያ ሰራዊቱ ጋር የተጋጩት፡፡
——–
በሚያዚያ ወር 1984 በወተር ከተማ በተካሄደ ጭፍጨፋ የሞቱትም በተመሳሳይ መልኩ በመከላከያ ሰራዊቱ እንደተገደሉ የሽግግር መንግሥቱ በወቅቱ አምኗል፡፡ ይሁን እንጂ በወተር የተገደሉት 230 ሰዎች በሙሉ ኦሮሞዎች እንጂ አማራዎች አልነበሩም፡፡ እነዚያ ሰዎች የተገደሉት ኢህአዴግ ከከተማቸው ወጥቶ ኦነግ ወደ ከተማዋ እንዲመለስ በመጠየቃቸው ነው (ወተር ለአንድ ዓመት ያህል በኦነግ ቁጥጥር ስር ነበረች፤ ኦነግ ከከተማዋ ሲወጣ ኢህአዴግ ገብቶባታል፤ ነዋሪዎቹ “እንደ ቀድሞው ጊዜያችን ኦነግ ወደ ከተማዋ ይመለስ” በማለታቸው ነው ከመከላከያ ሰራዊቱ ጋር የተጋጩት)፡፡ ጋዜጦቹ ግን “ኦነግ አማራዎችን ጨፈጨፈ” እያሉ ነበር የሚዘግቡት፡፡
——-
በ1984 (ወሩን አላስታውሰውም) በአሰቦት ገዳም በተካሄደ ግድያ ሰባት መነኮሳት ሞተዋል፡፡ ይህንን ግድያ የፈጸሙትም በወቅቱ የአሰቦት ከተማን ለትንሽ ጊዜ ተቆጣጥሮ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት እስላማዊ ግንባር (IFLO) ታጣቂዎች ነበሩ፡፡ ግድያው ስር ሳይሰድ በአፋጣኝ ያስቆሙት ደግሞ ኢህአዴግና ኦነግ ነበሩ፡፡ ሁለቱ ድርጅቶች አንድ ጥምር ኮሚቴ በማቋቋም በወሰኑት ውሳኔ መሰረት IFLO ከከተማው ተባርሮ አካባቢው በኢህአዴግ ቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል፡፡
——
በአርባ ጉጉ የተፈጸመው እልቂት በሁለት ተጎራባች መንደሮች መካከል በተካሄደ ግጭት ነበር የተለኮሰው፡፡ እያደር ግን መርቲ ጀጁ እና አሰኮ የሚባሉ የአርባ ጉጉ ወረዳዎችን አዳርሷል፡፡ በግጭቱ የኦሮሞ እና የአማራ ተወላጆች በእኩል ደረጃ ተጎድተዋል፡፡

በአርባ ጉጉ ግጭት የራሳቸውን የፖለቲካ ትርፍ ለማጋበስ የፈለጉ ወገኖች እጃቸውን አስገብተውበታል ይባላል፡፡ በመሆኑም በውጤቱ ከሁሉም ግጭቶች የከፋ ሊሆን ችሏል፡፡ በዚህ ግጭት ከሁለቱም ወገን እስከ ስድስት መቶ ያህል ሰዎች መሞታቸው ይነገራል፡፡ ከመቶ ሺህ ያላነሰ ሰው ወደ ሀረርጌና ሸዋ ክፍለ ሀገሮች ተፈናቅሏል፡፡ ሆኖም ኦነግ በዚህ ግጭት ውስጥ እጁን ማስገባቱን የሚያረጋግጥ ፍንጭ እስከ አሁን ድረስ የለም፡፡ ኦነግ በወቅቱ በአርባ ጉጉ አውራጃ ምንም ይዞታ አልነበረውም፡፡ የመላው አማራ ህዝብ ድርጅትም ቢሆን በግጭቱ የከሰሰው ኦህዴድን (OPDO) እንጂ ኦነግን አልነበረም፡፡ በተለይም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የምዕራብ ሸዋ ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ የነበረው ኮሎኔል ዲማ ጉርሜሳ ከግጭቱ ጋር ተያይዞ ስሙ በሰፊው ይነሳ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ በዚያን ጊዜ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ሐሰን ዓሊ ከእፎይታ መጽሔት ጋር (ግንቦት 1985) ባደረጉት ቃለ-ምልልስ “አቶ ዲማ ጉርሜሳ ንጹሕ ነው” በማለት ከመከላከላቸውም በላይ ለግጭቱ ዋነኛ ተጠያቂ ያደረጉት መአሕድን እንጂ ኦነግን አልነበረም፡፡

የግል ጋዜጦች ግን ነገሩን አራግበው በኦነግ ላይ አላከኩት፡፡ ነገሩን ሳያውቁት ቀርተው የተደረገ አይመስለኝም፡፡ አንዳንድ ጋዜጦች -ተከፍሎአቸው እንዲህ እንደሚያደርጉ በደንብ እናውቃለን፡፡
——–
የበደኖ ጭፍጨፋ! አዎን! ኦነግ ሊጠየቅበት የሚገባው ብቸኛው ትራጄዲ ይህኛው ነው፡፡ በርግጥም እልቂቱ በተፈጸመበት ወቅት በደኖ በኦነግ ቁጥጥር ስር ነበረች፡፡ የሞቱት ሀምሳ ያህል ሰዎች ለምን እንደተገደሉ ባይታወቅም አድራጎቱ በኦነግ ወታደሮች እንደተፈጸመ ድርጅቱ ራሱ አምኗል፡፡ ኦነግ በወቅቱ በወታደሮቹና በአዛዦቹ ላይ እርምጃ ወስጃለሁ ቢልም የተወሰደውን እርምጃ ምንነት አልገለጸም፡፡ በነገራችን ላይ በዚህኛውም እልቂት ከሞቱት መካከል ግማሽ ያህሉ ኦሮሞዎች ነበሩ፡፡
—–
ከላይ በዝርዝር እንዳስረዳሁት የኦነግ ጭፍጨፋ ተብለው ከሚጠቀሱ ትራጄዲዎች መካከል አብዛኛዎቹ በኦነግ የተፈጸሙ አልነበሩም፡፡ ኦነግ ሊጠየቅበት የሚገባው ብቸኛው ድርጊት በበደኖ የተፈጸመው ነው፡፡ የእውነት ቀን ሲመጣ ያንን ፋይል ማውጣታችንም አይቀሬ ነው፡፡ ይሁንና በኦነግ ያልተፈጸመውን ከርሱ ጋር አያይዞ መጻፍ ጥቅሙ ምን እንደሆነ ሊገባኝ አይችልም፡፡ እንዲያውም የያኔዎቹ የግል ጋዜጦች የሚያራግቡት ወሬ በተወሰነ መልኩ የኦነግ ጨካኝነትን ከመግለጽ ይልቅ “ኦሮሞ ጨካኝ ነው” የሚል እድምታ ለመፍጠር የታለመ ነበር የሚመስለው፡፡

እርግጥ የኦነግ ወታደሮች በብዙ አጋጣሚዎች ልዩ ልዩ የጭካኔ ተግባራትን ሲፈጽሙ ተስተውለዋል፡፡ እርሱን አንክድም፡፡ የነርሱ ገፈት ቀማሽ ሆኖ የዘለቀው ግን በአብዛኛው ኦሮሞው ነው እንጂ የሌላ ብሄረሰብ ተወላጅ አልነበረም፡፡ በተለይ አንዳንዶቹ የኦነግ ወታደሮች “ጎበና፤ ቢተምቱ.፤ ወዘተ..” ለሚሏቸው ግለሰቦች ምህረት አልነበራቸውም፡፡ እንዲሁም ተጻራሪ ድርጅት ሊያቋቁሙ ነው በሚል ፍርሃት አባላቶቻቸውን ጭምር እስከ መግደል ይደርሱ ነበር (የኦነግ የሀረር ቢሮ ሃላፊ የነበሩትን አቶ አራርሶ ወዳይን እና በመቻራ ከተማ የተገደለውን የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ካሊድ ሃጂ ኑራን መጥቀሱ ይበቃል)፡፡ ሆኖም ጋዜጦቻችን ድርጅቱ የፈጸመውን ማውራት ይተውና ድርጅቱ ያልፈጸመውን ወንጀል ይነግሩን ነበር! ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ ማለት ይህ ነው፡፡

ለማጠቃለል ያህል እኔ ለኦነግ አልተከላከልኩለትም፡፡ አንዳች ጥብቅና አልቆምኩለትም፡፡ የጻፍኩት የማውቀውን ሐቅና የማምንበትን አቋሜን ነው፡፡ ይሁንና ይህ አባባሌ ኦነግን ከመፍራት እንዳይወሰድብኝ አደራ እላለሁ! አስፈላጊ ከሆነ በኦነግም የተፈጸሙ ስህተቶችና ጥፋቶችን አንድ በአንድ መዘርዘር እችላለሁ፡፡

ሰናይ ቀን ይሁንላችሁ!!

ያረጋገጥነው የምግብ ኢዋስትናን (ዋስትና አላልኩም) ነው።

$
0
0

ከሠሎሞን ታምሩ ዓየለ
ክፍል 4
በክፍል 3 መጣጥፌ በዋናነት የአገራችን የተፈጥሮ ሃብቶችና ዓየር ንብረቷም ለተለያዩ አዝርዕቶችና ኦንስሳቶች ልማት ምቹነቱን በመግለጽ ነበር ያቆምኩት። አሁን በሚቀጥለው ደግሞ በክፍል 2ት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያልቻልንባቸውን መሠረታዊ ተግዳርቶች ውስጥ እንደ መንስኤ የቆጠርነው የመንግስትን በተለይም የአምባ ገነንነት ቅርጽ የያዙት የሚከተሉት ያልተስተካከለ የግብርና ፖሊሲ ተወግዶ በምትኩም ትክክለኛውና ለውጥ ሊያመጣ የሚችለው የግብርና ፖሊሲና ስትራቴጂ ምንን ማዕቀፍ ማድረግ እንዳለበት የአቅሜን ያህል ለማሳዬት ነው።
እንዲህ ልጀምር። በፖሊሲ ጥየቄና ዝግጅት የተለየ ትምህርት ወይም ሥልጠና የለኝም። ፖለቲከኞች፤ የመንግስት ሹማምንቶች፤ ኢኮኖሚስቶች፤ ለሎችም የማኀበራዊ ሳይንስ ሰዎችና በስፋትም በትልልቅ ኮርፖሬሽኖችና ካምፓኒዎችም ውስጥ ቃሉ ተደጋግሞ ይደመጣል። እኔም ከጊዜ ብዛት ትንሽ የገባችኝን ያህል ላክልባት። ” መወያየት መልካም” የሚል አብዮቱ ከመፈንዳቱ በፊት በኢትዮጵያ ሬዲዮ ፕሮግራም እንደ ነበር ትዝ ይለኛልና ያንን መሰረት በማድረግ ልቀጥል። የአገሬ የፖሊሲ ማውጣት ስራዎች እንዴት እንደሚዘጋጁና እንደሚጠናቀቁ፤ ዋነኛ ተቋሞቹ የት የት እንደሚገኙ ግን ለአብዛኛው ኢትዮጵያዊ እኔንም ጨምሮ የምናውቀው አይመስለኝም ( ምን አልባት መንግስት ጓዳ ይሆን)። ለመሆኑ ፖሊሲ ምንድነው? ፖሊሲ ሃሳብ፤ መርህ፤ አቅጣጫ፤ ሥርአት፤ መንገድና መመሪያ ነው ብል ትልቅ ስህተት የሰራሁ አይመስለኝም። ባጭሩ ፖሊሲ በህግ፤ በአዋጅ፤ በደንብ ፤ በትዕዛዝ፤ በመመሪያና በአሰራር ተደግፎ ወደ ተግባር ለመለወጥ ይመነዘራል። የፖሊሲ ምንጩ ወይም መነሻው ችግር ነው ቢባልም ማጋነን አይሆንም። የችግሩ አብዛኛውን ጊዜ ሰለባ ወይም ተጠቂ ደግሞ ሕዝብ ነው። ስለዚህ እውነተኛና ሕዝባዊ ፖሊሲ የሕዝብን የልብ ትርታ (አመታት በህክምና ሰዎች ቋንቋ) አዳምጦና ተከትሎ የሚዘጋጅ ሰነድም ነው። ፖሊሲ አንዴ ከተነደፈ ችግር የለውም ማለትም አይደለም። እንደ አፈጻጸሙና አካሄዱ አመቺነት፤ እንደአስከተለው ችግር ቀላልነትና ግዝፈት ይለወጣል፤ በሌላም ይተካል፤ ይዳብራል፤ ይታደሳልም። መሠረቴና መኖሬ ለሕዝብ ነው ብሎ የተነሳ መንግሥት ደግሞ የፖሊሲውን ጥቅም ለሕዝብ አገልግሎት ቅድሚያ ይሰጣል። ፖሊሲው ሲነደፍ ከአሰራር ዝርክርክነት የጸዳና ለሚነሱ ጥያቄዎችም የጠራ መልስ የሚሰጥና ኃላፊነት፤ ተጠያቂነትና በሕዝብ ተአማኒነትና ተቀባይነት አንዲኖረው ያስፈልጋል። ለብዙሃን እንጂ መቆም ያለበት የጥቂቶችን ጥቅም ማስጠበቂያ መሳሪያ መሆን እንደሌለበት ዕሙን ነው። የአንድን አገር መሪ ቃል ብቻ ወይም የአንድን ፖለቲካ ፓርቲ የአቋም መስመር ተከትሎ እንደ መዘውር መንዳት የኋላ የኋላ ገደል ይዞ ይገባል። ባጭሩ ፖሊሲው የሕዝብ ፍላጎት መሆኑን በዚህኛው ወይም በሌላኛው ዘዴ ደህና አድርጎ ማረጋገጥ ይጠቅማል እንጂ አይጎዳም። የተዘጋጀው ፖሊሲ ሕዝባዊነት ከሌለው ደግም ተቀባይነቱና ተአማኒነቱ ይቀንሳል፤ ጭራሹንም ይጠፋል። የመንግስት ፖሊሲ ተቀባይነት የሚገመገመውም ለመንግስት ሹመኞችና ለቅርብ ባለስልጣናት በሚሰጠው ደስታና ፌሽታ ሳይሆን በሕዝብ ኑሮ ላይ በሚያመጣው አሉታው ወይም አዎንታዊ ገጹ እየታየ ነው። መንግስትም ይህንን ተገንዝቦ ያለመስማት ወይም ያለማዳመጥ ፖሊሲውን አዲዮስ ማለት አለበት። ምሁራን የሚሰጡትን ገንቢ አስተያዬት አሌ ማለት አይገባም። አንድ ወቅት ላይ በ1984 ዓም መሰለኝ ፕሮፌሰር መስፍን ኃ/ ማሪያም ከመንግስት ሰዎች ጋር እሰጥ እገባ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ለይ ጀምረው ሳለ እንዲህ እንዳሁኑ ነጻ ጋዜጦችና ድረ ገጾች ውድ በሆኑበት ጊዜ የሚከተለውን ተናግረው ነበር። “መንግስትና ምሁራን በኢትዮጵያ ሆድና ጀርባ ናቸው” ። በሃሳብም፤ በግብርም አልተገናኙም፤ አልተዋሃዱም ማለት ነው። ልጆች ሳለን ለሙሽሮች የምንዘፍነው ዘፈን ትዝ አለኝ። የሙሹሮችን መግጠምና መዋሃድ ለማብሰር እንዲህ በማለት ገጥመናል። እከሊትና እከሌ ምንና ምን ናቸው፤ የጆሮ ጉትቻ የአንገት ሃብል ናቸው። መንግሥትም ሕዝብ የኔ ነው ያላለውን ፖሊሲ ለማስፈጸም ደፋ ቀና ሲል ከሕዝብ ጋር ይጋጫል፤ ይቀያየማል፤ የተቃወሙትን በአደባባይ ይደበድባል፤ ያስራል፤ ይከሳልም፤ እስርም ይፈርዳል። ከፍ ካለ ደግም የጠመንጃ ቃታ ስቦ ደም ካፈሰሰ በኋላ በሰራው አስነዋሪ ሥራ ከተጠያቂነት ለማምለጥ በቁጥጥሩ ሥር ባደረጋቸው መገናኛ ብዙሃንን በመጠቀም “አንዳንድ የኅ/ሰቡን ሰላም ለማደፍረስ “ የሚል መግለጫ ይሰጣል፤ ይፎክራል፤ ያቅራራል ፤ ያስፈራራል። አንዳንዴም ሁኔታዎች አስጊ መሰሎ ከታየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያውጃል። ይህችን ፓራግራፍ በዚህች ጨዋታ ወይም ቀልድ ልቋጫት። አብሮኝ በአምቦ እርሻ ተቋም የተማረና በኢሉአባቦር ግብርና ተጠሪ ጽ/ ቤት በተለያዩ አውራጃዎችም ተመድበን ስንሰራ የነበረ ጉዋደኛ ነበረኝ። ጉዋደኛዬ ዕድገት በኅብረት (በእብደት ሳቅ!) የሥራና የዕውቀት ዘመቻ ከተሳተፉት ተማሪዎች አንዱ ነው። በምድብ ሸዋ በደንዲ ጣቢያ ያለኝ መሰለኝ። ታዲያ በ1968ንቱ አካባቢ በሱ መስመር ከወሎንኮሚ ጀምሮ እስከ ጌዴዎ ድረስ ያለው የጅባትና ሜጫ አርሶ አደር በሆነ ምክንያት ያምጽና በወቅቱ የሸዋው የደርጉ አንበሳ የነበሩቱ ኮሎኔል ደበላ ዲንሳን (ነፍስ ይማር) አመራር ለመከተል አስቸግሮ ኖሮ፤ ደበላ በላንድሮቨር፤ አጃቢዎቻቸው ደግሞ በፈጣኗ ከፍት ጂፕ ቢ አር መሣሪያቸው ተደቅኖባቸው ከተፍ ካሉ በኋላ፤ በየጣቢያው የሚገኘትን ዘማቾች ሰብስበው ዐመጹን ለማቆም ” ዘማቹ ተሜን “ መላ በሉኝ ብለው ስብሰባውን ለውይይት ይከፍታሉ አሉ። ተሜ ተንኮለኛዋ የምትሰጠው ሃሳቦች ሁሉ ያልተዋጠላቸው ደበላ በመጨረሻ እንዲህ አሉ ይባለል። እኔና ወታደሮቼ በምታይዋቸው ክፍት የጂፕ መኪናዎች ላይ የድምጽ ማጉያ ይዘን ከአዲስ ዓለም ጀምሮ እስከ ጌዴዎ ድረስ ባለው አውራ ጎዳና ላይ (አውራ ጎዳና ከተባለ በዛሬ መለኪያ) ” ሲ ዳጰና “ በአፋን ኦሮሚፋ እንዲሁም “ ላንተ ነው የቆምኩት “ ስለው ዓመጸኛው ሰጥ ለጥ ይላል ብለው አረፉት። አዎን! ሰላምና ሕዝባዊ ፖሊሲ ያለው አመራር ቅንና ደግ ነው። ለጊዜውም ቢሆን ጠመንጃንና ጉልበትን እንደ አማራጭ አልተጠቀሙም። በዚህ አጋጣሚ እኝህ ኢትዮጵያዊ የፖሊስ መኮንን ንግግራቸውና ምክራቸው ጣፋጭ መሆኗን በ1971 ዓም የአምቦ እርሻ ተቌም ምሩቃንን ሲመርቁ በአካል አይቻቸዋለሁኝ። አንዳንዶቹ ሰውዬውን ደህና አድርገው የሚያውቋቸው ደግሞ ቢዘገይም ቀይ ሽብር የተባለው ጸረ ወጣት፤ ጸረ ምሁርና ጸረ ተራማጅ ህይሎች እርምጃ በተለይ በሸዋ ጠ/ግዛት እንዲቆም ካደረጉት ውስጥ በዋናነት ይጠቅሷቸዋል።
በክፍል 2 መጣጥፌ የምግብ ዋስትናችንን ጉዳይ እንዳናረጋግጥ ካደረጉን ምክንያቶች አንዱ የሆነውን ተፈጥሮአዊ መንስኤ ጸባይ እንዳለው ገልጬ ነበር። አንዳንዶቹን ለመከላከልና ለመገደብ ብንሞክርም ሌላውን ግን ፈጣሪያችን ተፈጥሮን በቁጥጥሩ ሥር የሚያደርግ መሪ እስከሚሰጠን ድረስ በትዕግሥት እንጠብቅ። በሁለተኛው ምክንያት ላይ ግን የመሪዎቻችን መልካም ፍቃድ ለጊዜው ታክሎበት መስራት ይቻላል። ይሄ ነው ጥሩ ፖሊሲ ብሎም አፍን ሞልቶ ለመናገርም ሊቸግር ይችላል። ማውራት ሌላ፤ ስራ ሌላ አይደል። አዎን! መስራት እንደ ማውራት ቀላል አይዶለም። ነገር ግን በቅድሚያ የሚያሰራና የሚያንቀሳቅስ የግብርና ፖሊሲ ለማዘጋጀት ግን ያለንን የተለያየ ዕውቀት፤ ክህሎትና የስራ ልምድ ያላቸውን ባለሙያዎች በማቀናጀት በሃሳብ ነጻነት እንዲሰሩ ማድረግ የመልካም ግብርና ፖሊሲ የመጀመሪያው ምዕራፍ ፩ ሊሆን ይችላል። የዘመቻ ዓይነት አሠራር አስወግዶ በምትኩም ደህና አድርጎ በማሰብ የተዝጋጀ ፖሊሲ ያስፈልጋል። በሥራ ላይም ችግር ቢገጥመው ወዲያውኑ ሊስተካከል ይችላል። ስለዚህ በዚህ የግብርና ፖሊሲ ውስጥ እንዲካተቱ የምንፈልጋቸው ጉዳዮች በዋናነት የሚከተሉትን መሠረታው ጥያቄዎች ሊመልሱ የሚችሉ መሆን አለበት። ለምን? ማን? እንዴት? እንደምን? ምን? የት? የትኛው? መቼና ሌሎችንም ጥያቄዎች በማንሳት፤ የማይሰሩትን በማስወገድ ሃሳቡ ይጀምራል። በዚሁ ጉዳይ ብዙ አዋቂዎችና ምሁራን ተናግረዋል፤ መክረዋል፤ ዘክረዋል። መስማትና መተግበር ያቃታት ግን ይቺ መንግስት የሚሏት ተቋም ነች። እርሷ የምትፈልገው እኔን ብቻ አድምጡ፤ እኔ የምላችሁን ብቻ ደግፉ ነው። ፖሊሲው በግልጽ መሰረታዊ የሆነውን የመሬት ይዞታ ጥያቄ ካለማወላወል መልስ መስጠት የግድ ይለዋል። መሬት የግል ይዞታ ይሁን! የረዥም ጊዜ ጥያቄ መልስ ማግኘት አለበት። የደንና ዱር እንስሳትን ፤ የአፈርና የውሃ ሃብታችንን አጠቃቀም፤ አጠባባቅና አስተዳደር መፍትሄ ማበጀት አለበት። የመሬትን ዓይነት ምዘናና ምደባ በትክክለኛው፤ አግባብነትና ተቀባይነት ባለው መንገድ መዘጋጀት አለበት። የዘመናዊና ሰፋፊ ኣርሻዎችን ይዞታና የት የት ሥፍራ መሆን እንዳለባቸው በቅድሚያ ጥናት መሰረት አድርጎ መዘጋጀት ተገቢ ነው። የአካባቢ ነዋሪዎችንም ዕውቀት ከግምት ውስጥ ማስገባት ይጠቅማል እንጂ አይጎዳም። በተለይ በተለይ ደግም ከውጭ በኢንቨስትመንት ስም የሚያገኙትን የራሳቸውን ጥቅም ብቻ አስልተው የሚመጡትን ባለ ሃብቶች ክፉና በጎውን ለይተን ሳናጠና በችኮላ ፍቃድ መስጠት የኋላ የኋላ አገር ይጎዳል። ግልጽ የሆነና የትኞቹ የሰብልና የእንስሳት ዓይነቶች ቅድሚያ ትኩረትን ተችረው መልማት አለባቸው ተብሎ መጠየቅም አግባብነት አለው። የግጦሽ መሬት አጠቃቀምንና አያያዝን እንዲሻሻሉ መርሃ ድርጊት መንደፍ። የዓሳ ሃብታችንን በሳይንሳዊ ጥናት ላይ በተመረኮዘ አሰራር ማሻሻል። የምርት አያያዝን፤ አቀነባበርን፤ አዘገጃጀትንና ጥራት አጠባበቅን አዋጭውን መንገድ መከተል ። የምርት ዓይነቶች ተገቢውን የገበያ ዋጋ በጊዜና በቦታ እንዲያገኙና ሥርጭታቸውም የተስተካከለ እንዲሆን የአቅምን ያህል ካለ ማቋረጥ መጣር። ለገበያ የቀረቡ ምርቶችም የታክስ ዋጋ የማይጎዳ መሆኑን ማረጋገጥ ተገቢ ነው። የምርት ግብአቶች ሁሉ በተፈለው ጊዚና መጠን እንዲሁም ዋጋቸው የሚቻልና ተመጣጣኝ እንዲሆን መንግስት በጥናት ላይ የተመሠረት የዋጋ ድጎማ እንዲያደርግ አሠራሩን ማመቻቸትና ማስተካከል። ዋነኛ የሜካናይዝድ እርሻ አገልገሎት መስጫ ጣቢያዎች እንዲስፋፉና እንዲጎለብቱ ማበረታታት። የብድርና የባንክ አገልግሎቶችን በቅርበት እንዲገኙ አሰራሮችን ማሻሻልና ትኩረት ሰጥቶ መከታተል። የትምህርትና የሥልጠና መርሃ ፕሮግራማችንን በፍላጎትና በችግሮቻችን ዙሪያ በቅድሚያ ማዘጋጀትና መንደፍ፤ የምርምርና የሥርጸት ሥርአቱን ለስራው ምቹነት ባለው አካሄድ ማደራጀት። የልዩ ልዩ አገልግሎት መስጫ መዋቅሮችን ( መንገድ፤ ግድቦች፤ የመስኖ ቦዮች፤ ጎተራዎች፤ የሰው ሰራሽ እንስሳት ማዳቀያ ጣቢያዎችንና የእንሳሳት ህክምና መስጫ ክሊኒኮችን አርሶ አደሩ በቅርብ ርቀት የሚያገኝበትን መንገዶች ካለማቋረጥ ማሰብና መገናኛ መሳሪያዎችና ሌሎችንም ጨምሮ) በአቅም በፈቀደ መጠን ማስፋፋት። በገጠሩ የኃይል አጠቃቀም ሥርዓትን ማጎልበት። የምግብና የምግብ አዘገጃጀት ሥርአታችንን ከጤና ፕሮግራም ጋር ተስተካክሎ እንዲሄድ መላ መሻት። አዳዲስ የሚቋቋሙት የሰፋፊ እርሻ ልማት ፕሮግራሞች የሠራተኛውን ጉልበት አጠቃቀም ከግምት ውስጥ ያስገባ፤ ደህንነትና የጤና እክሎች እንዳይፈጠሩና እንዳይባባሱ ከልብ መስራት። የአዳዲስ የሠፈራና የመንደር ምሥራታ መርሃ ድርጊቶች በቅድሚያ በሕዝብ ሙሉ ፍቃድ ላይ መመስረታቸውን ማረጋገጥ። የአምራቹን ሙሉ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስጠብቁና የሚከራከሩ የተለያዩ ዓይነቶች የህብረት ሥራ ማኀበራት ማቋቋምና ማጠናከር፤ የሴት አርሶ አደሮችን ጥቅም የሚያስጠብቅ አሰራር መፍጠርና እንዲተገበሩ እገዛ ማድረግ፤ የሕዝብ ቁጥር በፍጥነት መጨመርን የሚገታ የድርጊት እንቅስቃሴዎችን ማስፋፋትና ሌሎችም በዝርዝሩ ውስጥ ያልተጠቀሱቱ በአግባቡና ከልብ ከተሰራባቸው ችግራችንን የማንቀርፍበት ምክንያት አይታየኝም።
የማንኛቸውም አገር የግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ዓይነቱ፤ ደረጃው፤ ዕድገቱና ውጤቱ በተለያዩ ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ተግባሮችና እንቅስቃሴዎች ሁሉ የተለያዩ ሊሆኑ ይችላሉ። ግብርና በዋናነት በተለይም ከማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ለየት የሚያደርገው በባህርዩ ከጸሃይ በታች በምትገኘው የተፈጥሮ ጸጋ በሆነችው በምድር ወይም በየብስ ላይ በመከናወኑ ምክንያት በርካታ አካባቢያዊና ሥነ ምህዳራዊ ተጽዕኖዎች ይፈራረቁበታል። በተጨማሪም ማኅበራዊም ሆነ ባህላዊ ተጽዕኖዎችም ለፍጥነቱም ሆነ ለውድቀቱ የማይናቁ ስፍራ አላቸው። ነገር ግን ለኢኮኖሚው መሻሻልና ለውጥ እንዲያሳይ ከተፈለገ ደግሞ ሁለት መሰረታዊ መንገዶችም እንበለው ስልቶች ወይም ሌላ በአንድነት ተጣጥመው፤ ተዋህደው፤ ተደጋግፈውና አንዱ አንዱን ተከትሎ እንዲተገበሩ ግድ ይላል። እነርሱም በዋናነት መሰረታዊና አፋጣኝ ( አቀጣጣይ / አጋዥ ሃይሎች) ተብለው ይታወቃሉ። የቀድሞው የአምቦ እርሻ ተቋም መምህሬ የሆኑትና የአሁኑ የአምቦ ዩኒቨርስቲ በረዳት ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የሚያገለግሉት በቀለ ጣሰው ናቸው ይህችን ደህና አድርገው በግብርና ኤክስቴንሺን ትምህርት ቁጥር 1 ላይ በ1971 ዓም ያስተማሩኝ። ምስጋና ለሁሉም መመህራኖቼ በዚህ አጋጣሚ።
መሰረታዊ በመባል የሚታወቁቱ የሚከተሉት ናቸው። ለግብርናው ምርት ተስማሚና በቂ የገበያ አገልግሎት መስጫ ስፍራዎች፤ ዘመናዊና በየወቅቱ እየተሻሻሉ ወደ ተግባር የሚሸጋገሩና ተመጣጣኝ የሆኑ አሠረሮች ወይም ቴክኖሎጂዎች፤ የምርት ግብዓትና የተግባር መገልገያ መሣሪያዎች አቅርቦትና በሚያስፈሉግበት ጊዜ መገኘት፤ አምራቹን የሚያበረታቱና ለበለጠ ምርትና ምርታማነት የሚያነሳሱ እርምጃዎችን ቶሎ ቶሎ መውሰድና የተለያዮ መዋቅራዊ አገልግሎቶችን ማለትም እንደ ዋናና መጋቢ መንገድ፤ ግድቦችና የመስኖ ቦዮች፤ የጎተራ አገልግሎቶች፤ ማቀናበሪያ፤ ማዘጋጃዎችና ማሸጊያዎች፤ የእንሰሳት ክሊኒኮችና የመድሃኒት ማከፋፈያዎች፤ የኃይል ምንጮችና ሌሎች በፍጥነት ማስፋፋትና ማዳረስ ዋነኞቹ ናቸው። የሚያፋጥኑ ወይም አጋዥ ሃይሎች የተባሉት ደግሞ ከዚህ ቀጥሎ የሚዘረዘሩት ናቸው። ተከታታይ ትምህርትና ሥልጠናዎች ለሁሉም በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ውስጥ በዋናነት ሆነ በአጋዥነት ለሚሰሩቱ በሞላ እንደ አስፈላጊነቱ እየተጠና፤ የብድርና የባንክ አገልግሎት በቀለጠፈና አስተማማኝ በሆነ መልኩ መቅረብ አለበት፤ አምራቾቹ የራሳችውን ዕውቀትና ክህሎት ተጠቅመው የጋራን ችግር በጋራ እንዲቀርፉ የሚያስተባብር ቡድን ወይም ማኅበር መመስረት፤ የመሬት ለምነት የሚያሻሽሉና የሚጨምሩ እርምጃዎችና ተጨማሪ መሬት ለአገልግሎት ማዘጋጀትና ከላይ የተጠቀሱትን ነጥቦች በዕቅድና በመርሃ ድርጊትና በፕሮጃክቶች መልክ መቅረጽ ናቸው።
እኔን ከሁሉ የሚገርመኝ ግን አብዛዎቻችን ተምረን ሥልጣን ላይ ቂብ ያልን ፍጡራን ሁሉ የአሁኑን ጠቅላያችንን ጨምሮ፤ የክልልና የዞን የወረዳ ባለ ሥልጣናትንም አክሎ የገዥውንም ፓርቲ አባላትን በትግራዊ ቋንቋ ለመጠቀም “ከናይ ጭቁን መደባት” እያሉ ከሚያደነቁሩን ፖለቲከኞቻችን ይዞ መነሻችንና ምንጫችን ከእዚሁ ገበሬ ቤተሰብ እንደሆን ይታወቃል። ይህም በመሆኑ የገበሬውን ኑሮ በቅርብ እርቀት የተመለከትን ይመስለኝ ነበር። በዚሁ ገበሬ ልፋት፤ ድካም፤ ጥረት፤ ጉልበት፤ ዕውቀትና ክህሎት ለአንዳንዶቻችን የተቀናጣና ለግልገሎቹ ደግሞ የተመቸ ኑሮ እንድንኖር ያደረገን ይኽው ግፉአን የተሰበሰቡበት የሕዝብ ክፍል መሆኑ ጭርሹኑ የተረሳን ይመስላል። ለእርሱ እየሰራንለት ሳይሆን እየሰራንበት ነው። እርሱ የሚያመርተውን ምርት ተገቢውን ዋጋውን ሳናጋራው እኛው አራዳውቹ በእርሱ ልፋት ሃብት በሃብት ላይ እንጨምራለን፤ በስራው ላይ ያፈሰሰውን ላቡን ሳንጠርግለት ድካሙን እንጋራዋለን፤ እንቦጠቡጠዋለን፤ እንደ ዋግምት እንመጠዋለን። እንዴት ቡናን ያመረተና ምርቱን ሁልጊዜ ገንዘብ ያላቸው እንደ ጠበል ፉት ሳይሉ ስራን መጀመር የማይሆንላቸው በዓለማችን ሞልተው ያሉ ሕዝቦች እያሉለት የአገሬ የቡና ገበሬ በባዶ እግሩ ገጀራ እየያዘ በማሳው ውስጥ ከቤተሰቡ ጋር ለትንሽ ዋጋ ይለፋል፤ ይማስናል? ልብ በሉ! ከእርሱ ምርቱን እዚህ ግባ በማይባል ዋጋ ከተረከቡት በኋላ የበለጠ ለማግኝት የሚጣደፉትን አስተውሉ፤ እንዴት ሠራተኞቻቸውን በተሻለ ኑሮ ላይ እንዳስቀመጡ። እንደምን የዓለምን “የፖለቲካ ሰብል” እየተባለ የሚጠራውን ስንዴ አምራች በድህነት ይኖራል? የስንዴ ዱቄት አምራቾቹን የማይቀመስ የፉርኖ ዱቄት ዋጋ ልብ ይበሉ! ምንጩ ይኽው መከረኛ ድሃ እየተባለ የሚጠራው ገበሬ አይደለምን? የቢራ ገብስ አምራች ገበሬን ተመልከቱና መልሳችሁ እራሳችሁን ጠይቁት? የዘይቱም ምርት፤ የዶሮውን ዋጋ፤ የከብት ስጋ ዋጋን፤ የዕንቁላል ዋጋን፤ የዓሳ ስጋን፤ የቅቤውን ዋጋ፤ የማሩን፤ የምግብ እህሉንና የጥራ ጥሬ፤ የቅመማ ቅመም ዋጋን ሌሎችንም እንደዚያው ተመልከቱት። በርግጥ ገበሬው የልፋቱና የድካሙ ተጠቃሚ ነውን ብላችሁ ታስባላችሁን? ስንቱ በዚህ ገበሬ ላብና ድካም የተሻለ ኑሮን እያጣጣመ፤ የራሱ ልጆች መልሰው ይገፉታል፤ ችግርህን አንተ አታውቅም እኛ እናውቅልሃለን ይሉታል። በቅርቡ እንኳን ግምባሩ ታንክ ይመስላል እየተባለ የሚቀለድበት በረከት ስምኦን አቅም ሳይቀር ገበሬውን እንደ ጅል ተመልክቶታል። በረከት የገበሬውን ኑሮ ከእግር ኳስ ጨዋታ ጋር ያመሳሰለው ይመስላል። የጨዋታው እንቅስቃሴ ሁሉ በዳኛው ፊሻካ ብዛትና ማነስ የሚወሰን መስሎታል። ማነው ስሙ ያ የአማራ ም/ ገዢ እንፈፍ ደግሞ በባዶ እግሩ እየሄደ ብሎ ተሳልቆበታል። ገበሬው ለልፋቱና ለድካሙ ተመጣጣኝ ዋጋ ካገኘ ለኑሮው አስፈላጊ የሆኑትን ሸቀጦች ተመልሶ መጥቶ ይገዛበታል፤ ልጆቹን ወደ ትምህርት ቤት ለመስደድ አያቅማማም፤ ጤናውን ለመጠበቅ ወደ ኋላ አይልም፤ የግብአት ብድር ካለበት ለመመለስ ወደ ኋላ አያፈገፍግም፤ በሚቀጥለው ምርት ዘመን ምን? መቼ? ስንት? ለምን? ላምርት የሚለውን መሰረታዊ የስራ ጥያቄ ጠይቆ ይዘጋጅበታል። በአገራችን ተልካሻ አሰራር ገበሬው ሁልጊዜ ተጠቃሚ ሳይሆን ተጠቂ ነው። የኔ ቢጤው ሸማቹም እንደዚያው። ተጠቃሚዎቹ የመንግስት ትልልቅ ሹመኞችና ከእነርሱ ጋር በጥቅም የተሳሰሩት ብቻ።
ለመሆኑ የግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ የሚሰጠው ጥቅም ምንድን ነው? ጠቅለል ባለ አገላለጽ እንዲህ ይጠቀሳል።
1ኛ፡ ከመሠረታዊ የሰው ልጆች ኑሮ አስፈላጊ ናቸው ተብለው በተከታታይ ከሚጠቀሱትና የክቡሩን የሰውን
ልጅ ህልውና ለመጠበቅና የምግብ ፍላጎቱን ለሟሟላት ይረዳ ዘንድ የምግብ አዝርዕቶችን ማምረት፤
ማቅረብና አዘጋጅቶ ማቅነባበር ነው። ባጭሩ የምግብ ምንጭ ነው።
2ተኛ፡ ለሌሎች ማኒፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች የሚውሉ ጥሬ ምርቶችን በማቅረብና ተጨማሪ የምርት
ውጤቶችን በማስገኘት ገደብ የሌለውን የሰው ልጆች የሸቀጥ ፍላጎት ለማሟላት።
3ተኛ፡ የኢኮኖሚ ጠቀሜታን የሚሰጡ የአዝርዕት፤ የእንስሳት ምርትና ተዋጽዎኦችን እንዲሁም ደንና ውጤቶ
ቹን ለአገርም ሆነ ለውጭ አገር ገበያ በማቅረብ የገቢ ምንጭ መሆኑና በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ላሉ
አገሮች ዋነኛ የውጭ ምንዛሪ ማስገኛና መሰብሰቢያ መሆኑ።
4ተኛ፡ ለአብዛኛው የገጠሩም ሆና የከተማ ነዋሪው ዋነኛ የስራ ምንጭ ( ጊዜያዊና ቋሚ ስራ) በመሆኑ፤ የገቢያቸ
ውን መጠን ድርሻና ዓይነት በቀጥታ ሰለሚወስን። ይቺ የሥራ ሃይል ምንጭነቷ እኛ በአገራችን
ግብርና ሲባል ከምናውቃት በላይ ነው። አብዛኛዎቻችን ግብርና ሲባል ያው ገበሬ ማረሻውን ይዞ ከአፈ
ር ጋር መታገሉና በጭቃ መለወሱና አንዳንዴም ከከብቶቹና ዶሮዎቹ ከንብ እርባታው እንቅስቃሴ ጋር
ብቻ የምናቆራኝው አለን። ነገር ግን ዕውነታው ከዚያም ባሻገር ይዘልቃል። ግብርናቸው የሜካናይዝድ
ደረጃ በደረሰባቸው አገሮች ደግሞም ሆነ በማደግ ላይ ባሉ አገሮችና የሥራቸው መሠረት ይኽው ክፍለ
ኢኮኖሚ የሆኑቱ እንደ የእርሻ መሳሪያዎችና መገልገያ ቁሶችን፤ የመሬት ማዳበሪያና የጸረ_ተባይ ኬሚካል
ማምረቻ፤ የምግብ ማቀናበሪያና ማዘጋጃ ስፍራዎቹ፤ የግብርና
ምርት ውጤቶች ማከፋፈያና መሸጭያዎች ለዓብነት ያህል የዚሁ የግብርናው የሰራ ምንጭነት ውጤት
ናቸው።
5ተኛ፡ የኅብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ የሚያስችሉ በቀጥታም ሆነ በኢቀጥታ የተዘጋጁ ፈዋሽነትን በዋናናነት የ
ሚሰጡና ለተጨማሪ አገልግሎት የሚውሉ መድሃኒቶችን ዓይነት በማምረት።
6ተኛ፡ በተለይ ከደን ልማት የምናገኘው ጥቅም በዋናነት የአካባቢን የተፈጥሮ ሚዛን በመጠበቅ፤ ለሙ አፈራች
ን በአፈር መከላት ኃይሎች ተጠርጎ እንዳያልቅና ምድረ በዳንነትን በመከላከል፤ ለብርቅዬ የዱር እንስ
ሳትም መጠለያ በመሆንና የቱሪስት መስህብ እንዲኖረው በማድረግ በዋናነት ይጠቀሳሉ። ይህንን ሁሉ ጠቀሜታውን ስገልጽም ነገ የተስተካከለና የተረጋጋ የግብርና ፖሊሲ ቢኖረንና፤ ገንዘብና ዕውቀት ኖራቸው በዚህ በምግብ ማምረት ስራ ላይ ለመሰማራት ለሚፈልጉ የአገር ሰዎች እድሉ ምን ያህል ክፍት እንደሆነና አዋጬ እንደሆነ ለመጠቆምም ጭምር ፈልጌ ነው።
በክፍል 5ትና የመጨረሻው ክፍል እስከምንገናኝ ድረስ በቸር እንሰንብት!!!
አሜን!!


ቪ ኦኤ ወይስ የኢትዮጵያ/ወያኔ ሬዲዮ ?

$
0
0

ከመስፍን ደቢ
በዚህ ባለንበት ዘመን አለማችን በሚገርም ፍጥነት ለመከታተል ፋታ በማይሰጥ ሁኔታ የፖለቲካ ለውጦች እየተካሄዱ ነው። ሶቭየት ህብረት ሲፈረካከስ ትልቁ ስባሪ ዩክሬን ነው። ዛሬ ዩክሬን እየተናጠ ነው አለምም አተኩሮበታል ። በቤንዚዌላ ቀውጢ ሆኗል ፤ አብዛኞቹ የአረብ መንግስታት ተፋጠዋል፤ በኢትዮጵያችን ደግሞ የወያኔ የመጨረሻ ምዕራፍ መድረሱ ይተነበያል። ወያኔና ደጋፊዎቹ ሽብር ላይ ናቸው። እንዲህ በምትናወጠው አለማችን የሆነውን በትክክል ማን? የት? መቼ? እንዴት? የሚለውን አንዱም ሳይቀር እንድናውቀው የሚያደርጉን ጋዜጠኞች ናቸው። ለሙያቸው ትልቅ ክብር አላቸው፣እውነተኞች ናቸው፣ ደፋር ናቸው፣ ለህሊናችው ብቻ የሚታዘዙ ናቸው፤ እውነትን ፈልገው ለኛ ሲያቀርቡና እንድናውቅ ሲያደርጉን እነሱ እስራት፣ ድብደባ፣ ስቃይ፣ ሞትም አለባቸው። እነዚህን ቁርጠኛ የእውነት አርበኛ ጋዜጠኞች እላቸዋለሁ። ስለአገራችን ብቻ ብናገር ኢትዮጵያ እንዲህ ባሉ ጋዜጠኞች ታድላለች። ተሰደውላታል፣ ታስረውላታል፣ ሞትንም ቀምሰውላታል።
ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ እና በዲያስፖራው ሁለት አይነት ጋዜጥኞች አሉ። አንዱ ክፍል የወያኔ አገልጋይ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ የሆኑ ያሉበት ነው። ሌላው ክፍል ደግሞ ለጋዜጠኝነት ሙያ ተአማኒነቱ የበረታ እውነቱን ማቅረብ ዋጋ ቢያስከፍልም ቆርጠው የሚጋተሩ ያሉበት ነው። እንዲህ ባለ አጠቃላይ ምደባ ብንጠቀም የሚቀር አንድ ክፍል አለ። የስራ ተቋማቸው በሌሎች መንግስታት የተመሰረተ ሆኖ ኢትዮጵያ ተኮር ዜና የሚያቀርቡትን ለማለት ነው። ይህም ቪኦኤ እና የጀርመን ሬዲዮ የመሳሰሉ ናቸው። በተለይ እነዚህ ተቋማት ቪኦኤ የአሜሪካን ጀርመን ሬዲዮ የጀርመን ናቸው። ኢትዮጵያ ተኮር ዜና በአማርኛ፣ በትግርኛ፣ በኦሮምኛ፣ በሱማሊኛ ያቀርባሉ። ኢትዮጵያውያን በአገር ውስጥ እና በውጭ እንደ አማራጭ የዜና ምንጭ ይጠቀሙባቸዋል። በእነዚህ የዜና አውታሮች ያሉ ጋዜጠኞች የአሜሪካን ወይም የጀርመን መንግስትን አቋም እንዲያንጸባርቁ ቢገደዱ እንረዳቸዋለን ከዚህ በተረፈ ግን ለተግባራቸው መሪ ህሊናቸው ብቻ ነው ብለን እናምናለን። ለእውነት መቆምን፣ ሚዛናዊ መሆንን ያለውን እንዳለ የሆነውን ያለተጨማሪ አስተያየት ለአድማጩ ማቅረብ ሙያው የግድ ይላል ፡የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ጋዜጠኛ የኢትዮጵያ ሬዲዮ የለቀቀውን ውሸት ቢያስተጋባው የምንታዘበው ይሆናል። ቪኦኤ የኢትዮጵያ መንግስታዊ የዜና ተቋም ያለውን ቢያስተጋባ ትዝብት ላይ ይጥለዋል:: ቪኦኤ በዲያስፖራው ካሉ የወያኔ “የዜና” የፕሮፓጋንዳ ጋዜጠኞች መለየት አለበት ። ቅዳሜና እሁድ በመጣ ቁጥር አምባሳደር ኢንተርቪው የሚያደርጉና ስለልማት የሚያወሩ ባዶ ገረወይና የሆኑ አሉ። ቪኦኤ ከነዚህ መለየት አለበት።

ቪኦኤ በሞያቸው የተከበሩ ጋዜጠኞች ያሉበት ተቋም ቢሆንም ደግሞ ደጋግሞ ስህተት የሚፈጽም ረቀቅ ባለ መንገድ የወያኔን አቋምና መልእክት የሚያቀርብ ጋዜጠኛም አለበት። ይህ መሆኑ ደግሞ ያሳዝናል ። ለምሳሌ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይሮፕላንን አቅጣጫ አስቀይሮ ጄኔቭ እንዲያርፍ አድርጎ የፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቀው ረዳት አብራሪ ሀይለመድህን አበራ ድርጊቱ በአለም የዜና አውታሮች ሁሉ ቀርቧል። ከሁሉም የዜና አውታሮች ግን ቪኦኤ እና የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቲቪ የዘገቧቸው ይመሳሰላሉ። ሁለቱም ያተኮሩት የሀይለመድህን የአእምሮ ሁኔታ ላይ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት ስለ ሀይለመድህን አእምሮ ማተኮር የፖለቲካ ብሶቱና በደሉ እንዳይሰማ እና እንዳይተኮርበት ለማድረግ ነው። የቪኦኤውም “ጋዜጠኛ ” ይህን የማድረግ ግዴታ የለበትም ሚዛናዊ በሆነ መልኩ መዘገብ በቻለ ነበር። በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲህ ያለ የተዋጣለት ወጣት ሙያተኛ ምን ምክንያቶች ላደረገው ድርጊት ጋፋፉት ብሎ ጥያቄውን ወርውሮ ማለፍ ይችል ነበር፤ ግን መልእክቱን ጋዜጠኛው ከኢትዮጵያ ሬዲዮ ጋር በረድፉ ለማሰለፍ የቆረጠ ስለሚመስል የአእምሮ ሁኔታ ላይ አተኮረ፤ ሁኔታውም ካለማወቅ አይመስልም።
ዛሬ ዘመናችን አማራጭ የዜና ተቋማትን ቴክኖሎጂ ያንበሸበሸን ዘመን ነው። እንደ ዱሮው ቪኦኤ ወይም የጀርመን ሬዲዮ ብቸኞቹ የነበሩበት ግዜ አይደለም። የኢትዮጵያ ህዝብ በሀገር ቤትና በውጭው ይህን እውነታ ያውቃል። ቪኦኤ ለራስህ ብለህ ጣፍጥ ነው መልእክቱ ። ልጅ ያቦካው ለራት አይበቃም እንዲሉ ምራቃቸውን ዋጥ ያደረጉትን ጥቅም ሊያማልላቸው የማይችሉትን የእውነት አርበኛ የሆኑትን ጋዜጠኞች ከፊት ረድፍ ቢያሰልፉ ለቪኦኤ ጠቀሜታ ይኖረዋል። ቀድሞ እንደተባለው ኢትዮጵያ የጀግኖች እና የእውነተኛ ጋዜጠኞች ባለ ጸጋ ነች፤ ገና ብዙ ታፈራለች።ብዙ ጀግና ጋዜጠኛ የሚወለድበት የለውጥ ማእበል እያስገመገመ ነው። መጥኔ ለቪኦኤ እራሱን ካላረመ፤ ሰሚ ያጣ ጋዜጠኛ ከመሆን ሰውረኝ ነው።
ቪኦኤ አንዱ ጋዜጠኛው አግባብ የሌለውን ተግባር ቢፈጽም እንደ ተቋም መጠየቁ አይቀርም። ሄኖክ ሰማእግዜር ባደረገው ነገር ትዝብት ብቻ ሳይሆን በጣም አዝነናል ቆይቶ ደግሞ ህዝባዊ ቁጣ ማስነሳቱ አይቀሬ ነው።

አሜሪካ የበለጠ ትናገር! (ከጸጋዬ ገብረመድህን አርአያ)

$
0
0

“ ነፃነቴን ካልሰጣችሁኝ ሞትን እመርጣለሁ”
ፓትሪክ ሔንሪ Give me Liberty or Give me Death

ፍሬደሪክ ዳግላስ (1818- 1895) ከባርያ እናትና ከነጭ አባት የተወለደና ራሱም ቢሆን በቦልቲሞር (ሜሪላንድ) የቤት አሽከር ሆኖ የቆየ ሰው ነበር። አንድ ማለዳ ጁላይ 4 ቀን 1852 ን ተንተርሶ (አንተርሶ) በሮቼስተር ከተማ (ኒውዮርክ) ንግግር እንዲያደርግ ጥሪ ይደርሰዋል። ደብዳቤው ሲደርሰው እንደ እብድ ከራሱ ጋር መነጋገር ያዘ። መቸም አንዳንድ ጊዜ እንዲህ ያለ ለማመን የሚከብድ አጋጣሚ ሲመጣብህ ናላህ ይበጠበጣል። ፍሬደሪክ ዳግላስም “በእርግጥ ይህ ደብዳቤ ለእኔ የተጻፈ ነው? የተቀባይ ስምና አድራሻ ስሕተት ተፈጽሞ ይሆን?” ሳይል አልቀረም። ዳግላስ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ጭንቅላቱን ሲበጠብጥ ቆይቶ ትንሽ አረፍ አለ። ሲነቃ ይኸ ዕድል እንዳያመልጠው ፈለገ። ይልቁንም የሚናገርበት ርዕስ መጣለት። “ በመሰረቱ እኔን ባርያውን በዚህ በዓል ላይ እንድገኝ- ለዚያውም ተናጋሪ መሆኔን ሳስበው ይህ ሁሉ ግብዝ- የግብዝም ግብዝ ነው አለ። ይበልጥ ደግሞ ለተሰብሳቢው ስለጁላይ 4 (ነፃነት በዓል) እንድናገር እኔን ባርያውን መጋበዛቸው ሌላው ግብዝና ነው ” አለ። ለማንኛውም ንግግሩን አዘጋጀ። በዚያ ወቅት በሮቼስተር ከተማ ያደረገው ንግግር እስከ ዛሬ ድረስ ከዓለም ታላላቅ ዲስኩሮች አንዱ ለመሆን በቅቶአል። “ጁላይ 4 ቀን ለመሆኑ ለባርያው ምኑነው? What to the Slave is the Fourth of July?

ዛሬ ከብረት በከበደ ክንድ ኢትዮጵያን እየገዙአት የሚገኙት ጌቶች- አዳዲስ መሳፍንት- አዳዲስ መኳንንት፣ አዳዲስ ዲታዎች…የንግስ በዓል ከሳምንታት በኋላ ይከበራል። (በዩጐዝላቩ ጂላስ The New Class, ወይም ከሮማውያን ዘመን አንስቶ Nouveau Riche ቀላል ድግስ አያውቁም። ስለዚህ ጉንበት 20 ቀን በታላቅና ታይቶ በማያውቅ ድምቀት ይከበር ዘንድ ዝግጅቱ እየተሟሟቀ ነው። አገር ያፈራው ትልልቁ የሐረር ሰንጋ፣ ወደል ወደል የሚያክለው የወለጋ ላታም በግ ወዘተ ተመርጦ ተመርጦ ይቀርባል። ሻምፓኙ፣ ውድ ውዱ አይሪሽ መጠጥ- ዊስኪ፣ ድራንቡዬ፣…የፈረንሳይ ኮኛኮች፣ ምርጥ ወይን ጠጆች..ያልፍላቸዋል። ምንም ማጋነን የለበትም። ጫካ ውስጥ በነበሩበት ጊዜ እንኳ ለድግስ ስንትናስንት ሚሊዮን ብር ሲያወጡ እንደነበረ ከጉያቸው የወጣው ጠንካራ ኢትዮጵያዊ…ገብረ መድኅን አርአያ ገልጦታል።
“ኑና ጉንበት 20ን አብረን እናክብር” ተብለው የተጠሩ ወይም እንጠራለን ብለው ቀኑን እንደወላድ እየቆጠሩ- የራቀባቸው ሰዎች የሉም አትሉም። እናንተም እንደኔ። ከውጭ የሚጋበዙ በርካታ ሰዎች ይኖራሉ። አዳራሾች-ሆቴሎች- በየደረጃው… ላይበቁ ነው። እሸሸ ገዳሜው፣ አስረሽ ምቺው ደግሞ የሚጠበቅ ነው። ስለገዢዎቻችን ሀብትና ንብረት ያልተባለ ነገር የለም። ይኸ ደግሞ የሞራሉን ቁልቁለት ምንኛ እንደ ተያያዙት ስም እየጠቀሰ መረጃ የሚሰጠንን ውስጥ አወቅ ኢየሩሳሌም አርአያን ማድነቅ እወድዳለሁ። በሽምግልናና ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ በሚገባቸው ዕድሜ የእኝኝ ብላ ባዝራዎች፣ አንድና ሁለት (በቀን) የማይበቃቸው የወንድ መለኮኖች አሉባቸው። ከዚህ ተራ ውስጥ ሁለት ሰዎችን ብቻ (በረከተ-መርገም ስምዖንና ስዬ አብርሃ) ነፃ ያወጣቸው ደግሞ ተስፋዬ ገብረ-አብ ነው። ስለሆነም ዳንኪራውና ስድ የሆነው በዓል የሚጠበቅ ነው። እኛም የኢትዮጵያ ጉስቁሎች የሌላ ሕዝብ በዓል በሥነ ሥርዓት መጠበቅ አለብን። የበዓሉን መንፈስ ማደፍረስ፣ ማደናቀፍና ማቃወስ በአሸባሪነትና በመሳሰለው አንቀጽ ያስቀጣል። አዎን ጉንበት 20 ቀን የድግሦች ድግሥ፣ አውራ በዓልና የድግሦችና የበዓሎች ሁሉ እናት ናት። ማን ያውቃል? ድሮ ጃንሆይ አጤ ኀይለ ሥላሴ ሐምሌ 16ን “የትዮጵያ የልደት ቀን” እንዳሉአት እነዚህ አዳዳሶቹ መሳፍንትም ጉንበት 20ን “እውነተኛው የኢትዮጵያ ናጽናት ቀን” ቢሉት አይደንቀኝም። ( ብቻ ማን ነበር- የአንዱ ሕይወት የሌላው መርዞ ነው- ያለው?)
በአገራችን የድግስ ነገር ሲነሳ ትንሽ የማስታውሳቸው ነገሮች አሉ። በአጤው ጊዜ ጃንሆይ የተወለዱበት (ሐምሌ16) እንዲሁም የነገሱበት (ጥቅምት 23) ይከበሩ ነበር። ለኢትዮጵያ ባሕልና ፖለቲካ እንግዶች የሆናችሁ ወጣቶች ምናልባት አታውቁት ይሆናል እንጂ በክብርም ቢሆን ቤተ መንግስት ስትጠሩ ግርግሩ ብዙ ስለሆነ ትንሽ ጨፈቃ ትቀምሳላችሁ። እንጀራው በእግር የተቦካ ነው ይባላል። ለማንኛውም “የንጉስ በረከት” አይናቅም ትባላላችሁ። (ይህንን የበለጠ ለማወቅ ፍቅር እስከ መቃብርን ያነብቡአል) ወደኋላ ጊዜ የሐምሌ 16 በዓል አከባበር ለአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ተሰጥቶ ነበር።
የድግስ ነገር- በመንግስት ሰፈር- ብዙ ምልኪ አለበት። ስለ ጃንሆይ መንግስት አወዳደቅ ብዙ ቢባልም ለጊዜው አንዱን አነሳለሁ። አንዳንድ ሚኒስትሮች እጅግ ከቅብጠትም ባሻገር ስለሄዱ ክራር ይዘው ወደ መሸታ ቤት መሄድ አብዝተው ነበር። የዛሬዎቹ ከእነዚያ ጋር ባይወዳደሩም ትንሽ ትንሽ ሕዝብንና አኗኗሩን ወደ መርሳቱ ደርሰው ነበርና ሌላው ቀርቶ ከመሳፍንቱ አንዱ የነበሩት ጄኔራል ዐቢይ- “አውቀን እንታረም” የሚል መጽሐፍ ደርሰው ነበር። ጠንቃቃው ጄኔራል “አውቀን ካልታረምን ሌላው ቀርቶ ሬሳችን እንኳ የወደቀበት አይታወቅም” ብለው ነበር። አዎን አርማጌዶን በዓለም ፍጻሜ ላይ የሚከሰት ሳይሆን ያልታሰበ የእልቂት መውረድም አርማጌዶን ሊባል ይችላል። ያ ወቅት የሞራል ድቀት ሥጋና ደም ገዝቶ የሚታይበት፣ ሕዝብ ሲያልቅ አንዳንድ ሹማምንት መንደላቀቅ ያበዙበት ነበር። ደርግ ጃንሆይን ከሥልጣን ሲያወርድ “ሕዝብ በሺህ ቤት ሲረግፍ እነሱ በእሸሸ ገዳሜ ተጠምደው…” እያለና የቀለጠ ድግስ በቴሌቪዥን እያቀረበ ነበር። ድግስ….
ደርግ ራስዋ በራስዋ ያመጣችው ጣጣም አለ። ወደ ሥልጣን የመጣበትን ቀን ለማክበር ብልጭልጩንም ማናምኑንም ሰልፉንም…ሲያበዛ የእንግሊዝ ጋዜጠኞች በሁለት መቶ ሺህ ዶላር ውስኪ ሸጥን አሉና…የደርግ መሰላል ወደታች ብቻ የሚያወርድ ሆነ። ድግስ እየተኮነነ መጣ። ድግስ እየተጠቀሰበት ወረደ። ሁለት መቶ ሺህ ሕዝብ በረሃብ አለቀ ብሎ ተሳለቀ ተባለ። በራሱ ጊዜ ዘጠኝ ሚሊዮን ሕዝብ ተርቦ ውስኪ ተራጩ ተብሎ ለወያኔ ፕሮፖጋንዳ ተመቸ። እዚህ ላይ ያነሳሁት የጉንበት 20 አከባበር ያንኑ እድል ይከተል ይሆናል- ይከተላልም- ቁልቁለቱን ጀምሮአል በሚል ነው። ድግሶች በሦስቱ መንግስታት- የሥልጣን መልቀቂያ ጊዜ ምልክቶች- ብልሽትሽቱ የወጣ መንግስት ማክተሚያ ወቅቶች ሆነው አይተናቸዋል። ( ሁሉም የእጁን ያገኛል- ብድሩን ወይም ብድራቱን ተከፈለ- በሰፈሩት ቁና መሰፈር አይቀርም የሚባል አነጋገር ያለ ይመስለኛል። የእንግሊዝኛው ፈሊጥ ግን Poetic Justice ይለዋል) “ያርግላቸው!” አሜን ያድርግላቸው!!
ደርግ የተወነጀለበት 200ሺህ ዶላር ዛሬ አንድ ባለ ጊዜ ወያኔ ለልጁ ልደት ከሚደግሰው በታች ነው። በ1997ዓ.ም አባዱላ ገመዳ ለልጃቸው ዘኪያስ አባዱላ 24ኛ ልደት በዓል የ100ሺህ ዶላር ኮብራ ዘመናዊ መኪና በስጦታ መልክ አበርክተዋል። በ1994ዓ.ም በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ 14ሚሊዮን ሕዝብ ለረሃብ ተጋልጦ ነበር። መለስ ዜናዊ ከ10 ዓመት በኋላ “በቀን ሶስት ጊዜ ትበላላችሁ” ባሉበት ዓመት መሆኑ ነው። የመለስ ዜናዊ መንግሥት ለተራቡት ወገኖች ደንታ አልነበራቸውም። በድርጅታቸው የተፈጠረው ቀውስ ላይ በማተኮርና ለእርሳቸው የሥልጣን ዕድሜ ማራዘሚያ ሲሉ “ተሃድሶ” ብለው ለሰየሙት ቱማታ 280ሚሊዮን ብር ባጀት መድበው ካድሬዎቻቸውንና ተከታዮቻቸውን በድግስና በውስኪ ያምነሸንሹ ነበር። በዛው ዓመት ልጃቸው ሠማሃል መለስ የልደት በዓልዋን በግዮን ሆቴል ዳስ ተጥሎ አክብራለች። ለኬክ ብቻ ግማሽ ሚሊዮን ብር ነበር ወጪ የተደረገው። የመለስ ልጅ ልደትዋን በምታከብር እለት በግዮን ሆቴል ደጃፍ በርካታ በረሃብ የገረጡ ወገኖች የሚላስ የሚቀመስ አጥተው ወድቀው ነበር።
ስለ ድግስ ዝርዝር ለመጻፍ ፍላጐቱ የለኝም። ደግሼም አላውቅም። መንግስት ሲቀናጣ፣ እሸሸ ገዳሜው ልክ ሲያጣ፣ የሞራል ድጡ መጠነ ቢስ ሲሆን፣ ሰብአትካትን- ሰዶምና ገሞራን ወይም የጥፋት ውሃን ዘመን ሊያመለክተን ይችላል። ራስ ተፈሪዎች “ባቢሎን” ይሉታል። እንዲያውም በቀድሞው መንግስት በጠቅላይ ሚኒስቴር ሚኒስትር የነበሩት ዶክተር ሥዩም ሐረጐት The Bureaucratic Empire, Serving Emperor Haile Selassie በሚለው መጽሐፋቸው ያነሱት አንድ ነጥብ ስለድግስና ስለመሳሰሉት ጉዳዮች ነበር። ኮረኮረኝ። ሥዩም ሐረጐት እንደጻፉት የቀ.ኀ.ሥላሴ ባለስልጣኖች የታሰሩት ጠጅ ለመጣል ምቹ ቅዝቃዜ በነበረው ሥፍራ ነበር። ከላይ የደርግ አባላት ስብሰባ ሲካሄድ፤ ሑካታ ሲፈጠር፣ ጭብጨባ ሲበዛ ወዘተ በእሥረኞቹ ላይ ይፈጠር የነበረውን የመንፈስ ጭንቀት ይነግሩናል። አሳሪዎች የእሥረኞች ሥቃይ ሊታያቸው ከቻለ በእርግጥ “ሰው” የመባል ሙሉ ባሕርይ አላቸው ለማለት ይቻላል። (የደርጉን ዘመን ግፍ ለማውራት የምደፍርበት ወኔ የለኝም። ራሳቸውን እየቀደሱ በሌሎች ግለሰቦች ላይ ከሚደነፋፉም ጋር ጠበል የምጠጣ አይደለሁም። አንድ ነገር ላይ ከተስማማችሁልኝ ደርግ በውሃ አጥምቆ ቢሆን ወያኔ ይኸውና በእሳት እያጠመቀ ይገኛል። የጥምቀቱ ተቀባይ ደግሞ መላው ወገኔ ነው።)
የአሜሪካ መንግሥት ባለፉት ቀናት የኢትዮጵያን ድንኳን ገለጥለጥ አድርጐ የአገሪቱን የሰብአዊ መብት አጠባበቅ፣ የፖለቲካ እሥረኞች አያያዝ፣ በገጠር ያለውን ብሔረሰቦችን የመከፋፈል መንግስታዊ ጫናና ወንጀል አሳውቆናል። አሳውቆልናልም። በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ሰማንያ ሺህ የፖለቲካ እሥረኞች አሉ። ከእነዚህም መካከል ስድሳ ከመቶው አእምሮ እስከ መሳት መድረሳቸውን በምስክርነት አቅርቦልናል። ዝርዝሩ ብዙ ነው። ታላቅ ወንድም (የተጠጋኸው ትልቅ መንግሥት በፖለቲካው ቋንቋ ቢግ ብራዘር ይባላልና) ምናልባትም የእሥረኛውን ቁጥር ቀንሶት ይሆናል እንጂ በኢትዮጵያ እየኖረ ወያኔንና ትውልደ ወያኔ ያልሆነ ለመሆኑ ያልታሰረ – አለዚያም እሥራት የማያስጨንቀው ማነው? ብለው የሚጠይቁ የትየለሌ ናቸው። ያልታሰሩ የሚመስላቸው ሰዎች ደግሞ የጥርስ ችግር እያለው ሕመም ሳይሰማው በመጨረሻ ላይ አምስትና ስድስት ጥርሶቹ ሲረግፉለት ለቃቅሞ ወደ ሐኪም ቤት እንደሚሮጥ ሰው ናቸው።
እንደሁም ልጆቻቸው ወይም የአገር ወጣቶች በነቂስ እየታረዱ ኅዘኑ ከቤታቸው የማይገባ፣ የቤተሰብ አውራ በባለቤቱ ፊት ታስሮ ሚስት ስትነወር፣ ንብረቱ ሲድፋፋ፣ ጐታው ሲደፋ ልቅሶውና ዋይታው ከጆሮአቸው የማይደርስ ጐረቤት ወገናችን አለ። የድንጋይ ልብ የገባለት። አንዳንድ የማውቃቸው ሰዎች – ጐይትኦም ብቻ ሳይሆን- ደባልቄና አምበርብርም ጭምር – ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ ሄደው ሲመለሱ ተመሣሣይ ትዝታ ይዘው ይመጡላቸዋል። አዲስ አበባ ውስጥ የሚሠራው የእድገት ምልክት የሚገለጥ አይደለም። የአለቃ ደስታና የተሰማ ግጽው መዝገበ ቃላት በቂ ቃላት የላቸውም። “እንዲያውም በእንግሊዙ ንገረኝ” ትለዋለህ። አንተም አሿፊ እሱም አሹዋፊ ትባላላችሁ። ጓድ መንግሥቱ ኅይለማርያምን ብጠቅስ እንደማትቀየሙኝ ተስፋ አደርጋለሁ። በኢትዮጵያ ራዲዮ በሠራሁባቸው ዓመታት አንድ ቀን ስለ ራዲዮ አሠራር ስንገልጽላቸው ምርር ትክን ብለው “ ዘፈኑና ጭፈራው አልበዛም ወይ? ለመሆኑ ወገኖቻችን በጠላቶቻችን ሰይፍ እየተመቱ፣ አብዮታዊ ሠራዊታችን በግራም በቀኝም – በሰሜንም በምሥራቅም፣ በመሐል አገር ደግሞ በአምስተኛ ረድፈኞች ጓዶቻችን ሁሉ እተየረሸኑ..እያለቅን አይደለም ወይ? ኢትዮጵያ ራስዋ እንደ አንድ ልቅሶ ቤት መታየት የለባትም ወይ? እንዴት ነው በዚህ ሁሉ ልቅሶኛ ላይ እሸሸ ገዳሜ ዘፈን ለማሰማት ፈቃድ የምትፈልጉት? ፈቃድ የሚጠየቅበት አይደለም። እንደየስሜታችሁ ነው። ደስ ካላችሁ ዝፈኑ። አስዘፍኑ። አለዚያም ዳኝነቱ የእናንተ ነው” ብለው ነበር። አንዱ ሲደሰት ሌላው ያዝናል። ዓለም ጉራማይሌ!
ሕይወት ከዚህ መሠረታዊ አመለካከት ይጀምራል። ግን ከአለቃችን ንግግር ውስጥ ማንንም ሊነካ የሚገባው ለአገራቸው ባበረከቱት ቅንና ሕጋዊ አገልግሎት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥረው ወደ ወህኒ ዓለም የተወረወሩትን ሰማንያ ሺህ ኢትዮጵያውያን በዓይነ ሕሊናችሁ ጐብኙልን። አሜሪካ የምትነግረን- የማናውቅወን አይመስለኝም። ራስዋን በምስክርነት አቅርባለች። ከተጠቀምንበት። ወይም ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ አንድ ሰሞን ይሉ እንደነበረው “በደርግ ጊዜ አሜሪካ በክምር ሳር ውስጥ የወደቀች መርፌ ይታያት ነበር። አሁን ግን በእልፍኝ ውስጥ የቆመው ዝሆን እንዳይታያቸው አንድ ዓይነት ግርዶሽ (ማዮፕያ) ተፈጥሮባቸዋል” አይደለም? ጉዳዩ የኢትዮጵያውን ጉዳይ ነው ተባብለናል። የኢትዮጵያን ዋና ዋና ትግሎች (ጦርነቶች) በቅጥረኛና ካልሆነም በአሜሪካ አማካይነት የምንዋጋቸው አይደሉም። ይልቁንም ዛሬ አሜሪካ የነገረችን ሁላችንም እሥረኝነት እንዲሰማን ይመስላል። ጐበዞቻችን በወህኒ እየማቀቁ ነው።
ስለ እስክንድር፣ ስለ በቀለ፣ ስለ አንዱዓለም፣ ስለ ርእዮት….ሰምተን ነበር? ከእነሱ ሌላ ሰማንያ ሺህ ማን ያውቃል 180ሺህ ሰዎች በወህኒ ዓለም ይማቅቃሉ። ሌሎች ያልታሰሩ ግን “በመተካካት መልክ” ሊገቡ ወረፋ እየጠበቁ ናቸው። አፍጥጦ የመጣብን- እስካሁንም ያልተመለሰው ከባድ ጥያቄ- ለመሆኑ እኛስ አልሞትንም ወይ? መቸም ወደፊት እንደምንተሳሰበው ከሞቱት አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ አምሳ ሺህ ውስጥ አይደለንም ወይ? የመኖር ያለመኖር ማረጋገጫ (ምናልባት ሰርተፊኬት ወይም ሊቸንሳ) አግኝተናልን? ራስ ቢተወደድ መኮንን እንዳልካቸው “አልሞትሁም ብዬ አልዋሽም” ነበር ያሉት? ሙኩሼዬ ጸጋዬ ገብረ መድኅን ቀዌሳ ደግሞ ልዑል ሐምሌት የሚያንበለብለውን ዘላለማዊ ስንኝ እንዲህ ብሎ በከፊል ወደ አማርኛ መልሶታል።
መኖር አለመኖር እዚህ ላይ ነው ምሥጢሩ
የዕድል ፈተና አለንጋ ሲወናጨፍ ወስፈንጥሩ
ይህ ዕድል ያልደረሰውና የፈተናውም አለንጋ ያልገረፈው አለ ወይ? ይለናል። ኦስካር ዋይልድ ይመስለኛል በሶሻሊዝም ሥር የሰው ነፍስ (The Soul of Man under Socialism) ድርሰቱ “መኖር እጅግ ብርቅ ከሆኑ ባሕርያት ዋነኛው ነው። ብዙ ሰዎች እንዲሁ አሉ። ግን አይኖሩም ” ያለው (To live is the rarest thing in the World. Most people exit, that is all ) ይለናል በአንክሮ። የእኔው የትግል አድባር (አያውቀኝም) ፕሮፌሰር ሐጐስ ገብረ ኢየሱስ እናቱን ለመጠየቅ ጓድ መንግሥቱ ሔሊኮፕተር አዘዙለትና ወደ አድዋ ሔዶ ነበር። ሲመለስ A Requiem of History በሚል ያቀረበውን መጣጥፍ አልረሳውም። በዚያው ሰፊ ጽሑፉ ውስጥ እንደ ፈርጥ ያየሁለት “እናቴ በእርግጥ በሕይወት አለች። እየኖረች ግን አይደለም። She was alive, but Not living.” ይላል።
በ1980ዎቹ ካነበብኋቸው መጻሕፍት መካከል በሔንሪ ኪየምባና በዴቪድ ማርቲን የተገለጡ አስደንጋጭ አጋጣሚዎች በአእምሮዬ ውስጥ የተከሉት ክፉ ትዝታ አለ። በኢዲአሚን ኡጋንዳ ጊዜ የተፈጸመ ነው። እንዲያውም የ“State of Blood” የሚለው ጸሐፊ የኡጋንዳ የጤና ጥበቃ ሚኒስተር የነበረው ሔንሪ ኪየምባ ነው። ወደ ወጉ እንመለስና ኢዲአሚን በየቀኑ ሥፍር ቁጥር የሌለው ኡጋንዳዊ የሚገድልበትና የጭፍጨፋው ወፍጮ እንበለ እረፍት የሚሠራበት ሥፍራ ነበር። በዚህ “ሥራ” ላይ የተሰማሩት ባለሙያ ነፍሰ- ገዳዮች ትንሽ ፋታ ካገኙ ወደ ሰፈር መሸታ ቤት ይሄዱና ካቲካላና ቡቅር ከሚመስለው “ነፍስን ጭምር” ከሚያስረሳው መጠጥ ይጨልጣሉ። ግድያው እንደ ጫት ሐራራ ስለሆነባቸው በማይገድሉበት ሰዓት ሁሉ ሲያፋሽጉ ይውላሉ።
አንድ ቀን ያለወትሮው ግድያው በምሽት ሰዓት ሊጠናቀቅ ስላልቻለ ዋናው ገዳይ እስረኞቹን ይሰበስብና “ዛሬ ስለመሸ ሄዳችሁ ከቤተሰቦቻችሁ ጋር እደሩና ነገ በጠዋት መጥታችሁ መቃብራችሁን ቆፍራችሁ ትገደላላችሁ። አሁን ሂዱ። መልካም ዕድል” ይላቸዋል። በማግስቱ እስረኞቹ ተሽቀዳድመው በመሰለፍ መቃብራቸውን ቆፍረው በተሰጣቸው ትልልቅ መዶሻ አንዱ ሌላውን ገደለ ይባላል። ተረት ወይም የፈጠራ ድርሳን አይደለም። ዴቪድ ማርቲን በኦብዘርቨር ጋዜጣ ላይ በተከታታይ ያቀርብ የነበረውን ሐተታና ከላይ በርእሱ ያመለከትሁትን የሔንሪ ኪየምባ መጽሐፍ ያነብቡአል።
ገዥዎቻች፣ አንዱን ጠባብ፣ ሌላውን ነፍጠኛ በማለት የሰየፉት ወገን ቁጥር ይታወቃል? ከምዕራብ ወደ ደቡብ፣ ከደቡብ ወደ ምዕራብ እያንከራተቱ በየኪሎ ሜትሩ የረገፈው ወገናችን ቁጥር ይታወቃል? በአኅዝ የማይገለጠው መከራውና ሰቆቃው በምን ይተመን? እዚህስ ደረጃ አልደረስንም የሚያሰኝ ምን ምልክት አለ? አሁንም ለእርድ የተዘጋጀን ነን- ሁላችንም ባንሆን አብዛኞቻችን። ንጹሐን ዜጐችን ግደሉ ብንባል ዓይናችንን የማንጨፍን አለን። አሁንም ቢሆን እኛን በእኛ እየጨረሱንም እያጫረሱንም ነው። አይደለምን? የኢዲአሚኑ ሪፖርት ይዘገንናልን?
ያንን የምታውቁትን ለፍቶ ያስተማረኝ የኢትዮጵያ ገበሬ ሲባልለት የቆየውን “ናስቲለው”…አልፎ አልፎ ታስታውሱታላችሁ? ትዝ ሲላችሁ ዓይናችሁ እንባ ይቋጥር ይሆን? (ናስቲለው በሰሜን ኢትዮጵያ ገበሬ ማለት ነው።) አሜሪካ ስለ ኢትዮጵያ ገበሬ በመንግስት መሰቃየት ያርዳን? አቦ! አቦ! እንደ ብዕርና ወረቀት ያስጠላኝ ነገር የለም። ካሣ ተሰማ ትዝ አለኝ። ድንቀኛው ጸሐፊ ጓደኛዬ ብርሃኑ ዘሪሁን ካሣ ተሰማን አንድ ቀን አነጋግሮት ነበር። ለመነን መጽሔት ነበር። ብርሃኑ ወርቅ የሆነውን የካሣን ፕሮፋይል ሲያቀርበው “ቧንቧ ሠራተኛው ካሣ” በማለት ነበር። ካሣ ክራር መደርደር የለመደው በስሜት ነው። ከተቃጠለ አንጀቱ የሚያወጣውን ትንፋሽ በዘፈን ለማብረድ ነው። ካሣ ይዘፍናል። ስሜቱ ወደ ጽርሐ-አርያል ይከንፋል። እሱም ራሱ እንደ ማኰብኰብ ሲለው ክራሩን ሰባብሮ ሲጃራ መግዣ ፍለጋ ይሄዳል።
ይኸ ሁኔታ ዛሬ ይገባኝ ጀምሮአል። ከክራሩ ባሻገር የሚሰማው ድምፅ ያለ ይመስለኛል። ከመላእክት ጋር ሲነጋገር ቆይቶስ ቢሆን? ከአድማስ ባሻገር ከታላላቆቹ ተራሮች ላይ ሆኖ ስለዚች አገር ዕድል- ስለሚደርስባት አደጋ፣ ስለ ትንንሽ ልጆችዋ መቀጨት፣ እንደ ዛሬ ስላለው የመከራ ሌሊት ያጫወቱት እንደሆነ ማን ያውቃል? እንዲያ ሆኖ ሆኖ ካሣ ወደ ቧንቧ ሥራው ይመለሳል። እሱም ዘመንን ቆጥሮ ወደ መሬቲቱ ተመለሰ። ወደ ማኅፀናዋ።
እኛንም ደካሞች ልጆችዋንም እነሱንም ባሊጊዜና ቅምጥል አዳዲስ መኳንንትና መሳፍንት የኢትዮጵያ መሬት እኩል ትበላናለች ወይ? ስለ ጄኔራል ደጐል ያነበብሁት አንድ ታሪክ አለ። ጄኔራል ደጐል ሽባ ሆና የተወለደች ልጅ ነበረቻቸው። ወላጆች እጅግ እያዘኑ ልጅቱ በመንፈስ እንድትጠነክር የማያደርጉት አልነበረም። የሚችሉትን ጥረት ሁሉ ካሙዋጠጡ በኋላ ልጅቱ ትሞታለች። እናት መሆን አይቀርምና ማዳም ደጐል ምርር ብለው ያለቅሳሉ። ያዝናሉ። እሳቸውን ማጽናናትም ከባድ ሆነ። በዚህ ጊዜ ጄኔራል ደጐል ባለቤታቸውን “እስካሁን ድረስ ምኞታችንና ጸሎታችን ሁሉ እግዚአብሔር ከሰው እኩል እንዲያደርጋት ነበር። ይኸውና በሕይወት ባይሆን በሞት ከሁሉ ጋር እኩል ሆናለችና ልቅሶሽን ተይ…” በማለት ባለቤታቸውን አጽናኑአቸው።
ኢትዮጵያውያን ሽባ ሆነን አልተፈጠርንም። ወይም አዳዲሶቹ ዲታዎች (ኖቮሪሽ) በአፋቸው ላይ የወርቅ ፍልቃቂ እየነከሱ ከማኅፀን አልወጡም። ሕዝብ የሚገዛው እንዲህ ነው ተብለው ጊንጥ የሚመስል አለንጋ የሰጣቸው አንዳች ኅይል የለም። ለምን ገዥና ተገዥ፣ ገራፊና ተገራፊ ሆነን ቀረን? አንመራመር። አስፈላጊ ወዳልሆነ እሽኰለሌም አንግባ። ይልቁን ከሞት በፊት ስላለው እኩልነት እናንሳ። በሞት ሕይወትን ስለማምጣት፣ በደምና በአጥንት ነፃነትንና እኩልነትን ስለመቀዳጀት።- ውይይይይ ለአፍ አይገድም። ትግሉን፣ መስዋዕትነቱን በወረቀት ላይ ጨረስነው አይደል? በሃያኛው ክፍለ ዘመን መነሻ የተጫነው የእኩልነት ትግል እነ W.E.B Du Bois የጀመሩት የጥቁር አሜሪካውያን ተጋድሎ ስትራተጂ የሚነደፍበትና ፕሮግራሙ በሥራ ላይ የሚውልበት ስልት የሚወጣበት ነበር። ታላቁ ዱብዋ ተፈጥሮ ለሰው ልጆች እኩል የሰጠችውን መብት ከሰው ልጆች መለመንን የመሰለ ውርደት እንደሌለ ይገልጣል። የመብትና የነፃነት ልመናን የመሰለ ወራዳ አቋም የለም። W.E.B Du Bois The Souls of Black Folk በሚል ድሮ ባሳተመው መጽሐፍ “ተነሥ! የምታጣው ሰንሰለትህን ነው” ወደሚለው የተራማጆች ፍልስፍና ያመራል። እንዲያውም ሎወልን በመጥቀስ-
“Twixt old systems and the word
Truth forever on the scaffold
Wrong forever on the throne
yet that scaffold sways the future
And behind the dim Unknown
Standeth God within the shadow Keeping watch above His own”
ይላል። እውነት ዘወትር በመሰቀያው ሥፍራ፣ ውሸትና የማይገባው ሁሉ ዘወትር በዙፋኑ (በአልጋው) ላይ የመገኘቱ ነገር- ያ የመሰቀያው ጣውላ የወደፊቱን ሁሉ እየነቀነቀ መገኘቱ፣ እነሆ በጭላንጭሉ መሐል ደግሞ እግዚአብሔር ከፍ ብሎ ቆሞ የራሱን ወገኖች የማበረታታቱ ጉዳይ ዘላለማዊ ነው።
ልመለስ ወደ አሜሪካ ዓመታዊ የሰብአዊ መብት መግለጫ። ከላይ ያነሳሁአቸው የዱብዋ (አሜሪካኖች ዱባይስ ይላሉ ፈረንሳዮችን ለማብሸቅ) ወይም የፍሬደሪክ ዳግላስ ታሪኮች ለእነሱ ብዙ ይጥማቸው እንደሆነ አላውቅም። በተለይ ለሪፐብሊካኖቹ። እንደዚያም ሆኖ ይህ በእነሱ ድጋፍና ርዳታ ሞልቃቃ ሆኖ የተወለደውና የሚጨፍርብን ሥርዓት (መንግሥት) ፀረ ሕዝብ፤ ፀረ አገር፣ ፀረ እንጨት፣ ፀረ ሳር፣ ፀረ ሕዝብ፣ ለመሆኑ- እደግመዋለሁ- የእነሱ እማኝነት አለን። ጊዜው- የመለያያው- ደረሰና ነው ምሥጢሩን ሁሉ ያፈነዱት? ሊሆንም ላይሆንም ይችላል። እዚያ ላይ ያለውን ነጥብ የምንመለስበት ይመስለኛል። ለአሁኑ ግን አሜሪካ በአንድ በኩል ልትረዳን የምትችላቸውን ጉዳዮች ባነሳ- ከአንባብያን ድጋፍ ካገኘሁ።
አንደኛ- እስካሁን ድረስ አሜሪካ እንዲህ ያለ በሰብአዊ መብት አከባበር ረገድ የተበላሸ አቋም፣ በፖለቲካና በአገር አንድነት ጥበቃው ረገድ አሳፋሪ ሪኮርድ፣ በሕዝብ ሰላም ጥበቃና የፍትሕ መስተንግዶ መላሸቅ ረገድ ያልሆነላቸውን መንግሥታት ወይ Evil ኤምፓየር- ወይ Rogue State አለዚያም አሸባሪ (Terrorist) ሲሉ ባጅተዋል። ወያኔ ምንድነው? በእኛ ምደባ Terrorist Regime ሊባል ይገባዋልና ስያሜው በዚሁ እንዲሆን እንጠይቃለን።
ሁለተኛ፥ ይኸ ሁሉ ከተወሳና የወያኔዎች መንግሥትም ከሕዝብ የብድርና የርጥባን ገንዘብ 20 ቢሊዮን ዶላርስ ጠልፎ ወደግል ሂሳብ ያዋለ እንደመሆኑ- የዋና ዋና ሌቦችን የስም ዝርዝር እናቅርብና ወደየምዕራቡ መዲና ሲገቡ እንዲያዙና እንድንፋረዳቸው።- ገንዘባቸው እንዳይንቀሳቀስ እንዲደረግ- ከምዕራባውያን የሚሰጣቸው ማናቸውም ርዳታ ያለ ቅድመ ሁኔታ እንዲቋረጥ- ኢኮኖሚው ራሱ የተጠለፈና ወደ ግል ኩባንያነት የተዛወረ ስለሆነ የትኛውም አገር ከወያኔዎች ጋር የንግድ ልውውጥ እንዳያደርግ ዘመቻችንን እንዲቀበለን ትብብር እንጠይቃለን።- ከናይን ኢለቨን ጋር በተያያዘ አሜሪካ እንዳይደርሱ እግድ የነበረባቸው አንዳንድ ዘራፊና አቀባባይ ሌቦች እንደገና ወደ አሜሪካ ብቅ እያሉ የለመዱትን የሞራል ድቀት ትርኢታቸውን እያሳዩ ናቸው። ከእነዚህ መካከል አንዱን አረብ ግለሰብ የኢትዮጵያ ትውልድ ሁሉ የሚፋረደው ስለሆነ ተይዞ እንዲመረመር እንጠይቃለን። ወርቃችን፣ ሌሎች የማዕድን ሀብቶቻችን ወዘተ በዚሁ ሰው እንደ ትንሽ ዕቃ በየቀኑ እየተጫነ እንደሚወሰድ እናውቃለን። እናስረዳለንም። …………

በ1980ዎቹ Republic of Fear በሚል ርእስ ስለ ሳዳም ሑሴን ጨለማ አገዛዝ የሚያወሳው መጽሐፍ በእጅጉ ያሸማቅቃል። ጸሐፊው ኬናን ሜኪያ ይባላል። የኢትዮጵያ የዛሬ ሁኔታ ደግሞ ሌላ ባሕርይ ያለበት ይመስለኛል። ስለ ዋናዎቹ አምባገነኖች ሲነሣ አብዛኛዎቹ ነጠላ ናቸው። በቺሊ ፒኖቼ- በሩማንያ ቻይቼስኮ፣ በኢራቅ ሳዳም ሑሴን፣ በሊቢያ ጋዳፊ…ናቸው። ለወርቅ ጥጃቸው የማይንበረከክ፣ ለምስላቸው የማይሰግድ ከሁለት ስፍራ ይከፈላል። ያማቸው፣ ስማቸውን ያጐደፈ…የሚሰቃይበት አዳዲስ መሣሪያ አስፈልፍለዋል። ዝርዝር የማሰቃያውን ስልትና ድርጅት ከማእከላዊ ምርመራ ሠራተኛነት አምልጠው የወጡ ሰዎችን ማነጋገር ይቻላል። ባይሆን አንድ ጥያቄ በአእምሮአችሁ የሚመላለስ ወገኖቼ አትታጡም። መለስ ከሞተ በኋላም ይኸ አገር በአምባገነን የሚመራ ነው ለማለት ይቻላል ወይ? በእኔ በኩል ከሰዎች ጋር ስወያይ “አምባገነኑ የማይታወቅ አምባገነን መንግሥት” A Dictatorship without a Dictator ግን አገዛዙ መንጋ ጨካኖች፣ ነፍሰ- ገዳዮችና በዝባዦች ቢኖሩትስ? የፈረንሳዩ ታላቅ ምሁር ዣን ፍራንስዋ ሬቨል Without Marx or Jesus በሚለው መጽሐፉ እንዲህ ያሉትን አምባገነኖች ባሕርይ Collective Mediocrity and Collective bestiality ይለዋል። ነገሩ እንዲህ ነው። መለስ ሲሞት የእሱ እጓለማውታ (Orphans) መፈላለግ ያዙ። ሰብሳቢ አጣን ብለው ወደ ትካዜው ዓለም ተሰደዱና መጠራራቱን አንድ መፍትሔ አደረጉት። ምንጣፉን ቶሎ ብለው የረገጡት እነ እንቶኔ ደግሞ አራት ኪሎን የተጫጫነውና አሁንም የሚገዛውን መንፈስ በፍጥነት በማናቸውም አስማት ለማስወጣት አልቻሉም። ትንሽ ፋታ ሳያስፈልጋቸው አልቀረም። ጥቂት ጊዜ ከገዙ በኋላ የፕሮፓጋንዳውም መሣሪያ ትንሽ ትንሽ ይደፍረዋል። “መለስኮ ሰው ነው” ማለት ይጀምራል። ሰው መሆኑን ዛሬ ነው ያወቁት አትበሉአቸው። እኛ መለስን ከመቃብር አውጥተን አንፋረደውም። እነሱ ራሳቸው ከሳሽም ፈራጅም ይሆናሉ። ጠብቁ ብቻ።
በደርግ ጊዜ ስለአባካኝነትና አሻጥር ትልቅ ጉባኤ ተዘርግቶ ነበር። በንቁዝ (ኮራፕት) ባለሥልጣኖችና በመሳሰሉት ላይ ጥብቅና ወሳኝ የሆነ ርምጃ ስለሚወሰድበት ሁኔታ ውይይት ሲካሄድ በየቦታው ኮሚቴዎች እንዲቋቋሙ አሳብ ይቀርባል። በዚያ መድረክ ላይ የአገር አስተዳደር ሚኒስትር የነበሩት ጄኔራል ታዬ ጥላሁን የተናገሩት ትዝ ይለኛል። በአጤ ምኒልክ ዘመን እቴጌ ጣይቱ “ለአገሬ ለየጁ ያለው አንድ አፈንጉሥ ብቻ ስለሆነ ሌላ እንዲጨመርለት እጠይቃለሁ” ሲሉ እቴጌይቱን በአደባባይ ተቃውመው የማያውቁት ንጉሠ ነገሥት “እንኳን ሌላ ተጨምሮበት አንዱም ቢሆን አልተቻለም” አሉ ይባላል።
በዛሬዪቱ ኢትዮጵያ ከመለስ ሞት በኋላ አንድ ታዋቂና በአደባባይ ስሙና ሹመቱ የተገለጠ አምባገነን ባይኖርም ሟቹ በመጠኑ ራቅ ያደረጋቸው ሰዎች አልጋው ላይ የተረባረቡ ይመስለኛል። አቦይ ስብሐት፣ ጌታቸው አሰፋ፣ ዐባይ ወልዱ፣ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ወዘተ ወዘተ…በአንድ አገር የስለላው መረብ እንዳለ ወደ ፍጹማዊ ኅይል ሲለወጥ ደግሞ የዜጐች ሁሉ (መካከለኛ ደረጃ ያሉት ወያኔዎች ሳይቀሩ) መብት ወደ ኢምንትነት ይለወጣል። የሥነ መንግሥት ምሁራን በመንግሥት ውስጥ መንግሥት (ኤስቴት ዊዝን ኤ ስቴት) የሆነውን እንዲህ ያለውን ሥርዓት “መሪ” የሚባለውን ግለሰብ ጭምር ሽባ አድርጐ የሚቀፈድደው ያደርጉታል። በአሁኑ ሁኔታ ቀስ በቀስ የመለስ የቅርብ ሕዝብ አጫራሾች ዕጓለማውታ (ኦርፋንስ) ቢመስሉም ሌሎች በርካታ አምባገነኖች ጡንቻቸውን እያፈረጠሙ ናቸው። ወትሮ አንድ አምባገነን ያልቻለው የኢትዮጵያ ሕዝብ የብዙ አምባገነኖች ተሸካሚ ሆኖዋል። ሁሉም ነፍሰ ገዳዮች! ነፍሰ ገዳይ የማይፈራስ ማነው?
ለጊዜው በመንጋ ተንኮለኞች- ነፍሰ ገዳዮችና የዝርፊያ ሠራዊት እየተገዛን እንገኛለን። ስለእነሱ ድግስ፣ ስለ እነሱ ጥቅም፣ እነሱ የትኛዋን ጋለሞታ እንደሚጐበኙ፣ የትኛዋን መለኮን ዛሬ እንደወሰዱ እንወያያለን። በጥቃቅን ጉዳዮች አእምሮአችንን አስጨንቀናል። ወጣጥረነዋል። ይልቁን በሌላው ዓለም እየተቀጠቀጠ ማረፊያ ያጣው መንግሥታዊ አሸባሪነት የሙጥኝ ብሎ የሚገኘው በኢትዮጵያ መሆኑን እንተባበር። ይህን የሽብር መንግሥት ሌላው ቀርቶ በብረት መሞከርን ካህናቱና መነኮሳቱም መደገፍ አለባቸው። ከቶውንም ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በፋሺስቶች ጥይት ሊደበደቡ ጥቂት ሰከንዶች ሲቀራቸው “ልጆቼ ኢትዮጵያውያን ለፋሺስቶች እንዳትገዙ አውግዤአለሁ” ማለታቸው ይጠቀሳል። አዳዲስ ካሕናትና የዚህ ትውልድ ቀሳውስት ነገሩን ቸል እንኳ ቢሉ የአቡነ ጴጥሮስ ግዝትና ውግዘት አለብን። ቋሚ ነው- እስከማዕዜኑ።
ትግልና ታጋይ የሚጠይቁት አንድ ነገር ብቻ ነው። በደረትህ ውስጥ ጤነኛ ልብ፣ በጭንቅላትህ ውስጥ ጤናማ አእምሮ ካለህ ማናቸውም ችግር አይፈታህም። ጥይት አይመታህም። ድንፋታ ትርጉም አይሰጥህም። ቅጥፈትና ማስፈራራት ትጥቅህን አያስፈታህም። ልጆቼ ልላቸው የምችለው እነ እስክንድር፣ በቀለ፣ አንዱአለምና ርእዮት ይህን ወኔ በሰፊው የተቀዳጁ ናቸውና እንኮራባቸዋለን። እነሱ ወኅኒ ዓለም ሲገቡ የከዳናቸውና የቆሙለትን ዓላማ ጭምር የረሳንባቸው ከመሰላቸው ደግሞ አደራ በላነት ሊሰማን ይገባል።
ይህን ጽሑፍ የጀመርሁት በወያኔ የልደት በዓል ምክንያት ትንሽ የምለውን ለማቃመስ ነበር። ምናልባትም እንደ ፍሬደሪክ ዳግላስ ለእነዚህ ሰዎች “ጉንበት 20- ጉንበት ሃያ ትሉናላችሁ ጉንበት ሃያ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሥቃይ ሁሉ እናት የሆነችው ስቃይ የመጣችበት ቀን። ጉንበት 20 የባርነትና ወደር የሌለው ውርደት መታሰቢያ ቀናችን ናት። ጉንበት 20 ለእሥራታችን መታሰቢያችን ናት።” ልንላቸው እንችላለን። ይኸ የደፋሮቹ ጋዜጠኞች – የጀግኖቹ የፖለቲካ መሪዎችና ገበሬዎች የተባበረ ድምጽ ነው። በሬሳችን ላይ የሚጨፍሩበት፣ በመቃብራችን ላይ የሚያሽካኩበት፣ ቤትና ንብረት አሳጥተው ለስደት ያበቁንና በዚህ ደስታ የሚሰክሩበት በዓላቸው- የእኛ የልቅሶ ዕለት፣ የእኛ የመከራ ቀን መታሰቢያ ነው።
በመጨረሻም እንደገና ለአሜሪካ በማቀርበው ጥያቄ ላይ ይህችን ነጥብ እደግማለሁ። ይህ መንግስት ኢቭል የምትሉት አይነት ነው? ወይስ አሸባሪ? የወያኔ ኦሮሞዎች በኢትዮጵያውያን ኦሮሞዎች ላይ የሚፈጽሙትን እልቂት፣ የወያኔ አማራዎች (እነበረከት አምሮች ከተባሉ) በኢትዮጵያውያን አማሮች ላይ የሚያካሄዱትን መጠነ ሰፊ ድምሰሳ፣ የወያኔ ሙስሊሞች በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ እያደረሱ የሚገኙትን ወከባና ወደር የሌለው ጥቃት፣ ሟቹ የመለስ የሃይማኖት የይስሙላ ፓትርያርክና እንደ ሩሲያዊው ራስፑቲን የሚቆጠረው አባ ጳውሎስ በኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ያካሄደውን ሥቃይ አሜሪካ ከእኛ በላይ እንደማያውቀው ለዴሞክራሲ፣ ለሰብአዊ መብትና ነፃነት ስትል ርምጃ ለመውሰድ አቅዳለች? አጤ ኅይለሥላሴ በቀድሞው የመንግሥታት ማኅበር ጉባኤ ላይ ያደረጉትን ንግግር ለመጥቀስ እገደዳለሁ – “ታሪክና ትውልድ ፍርዳችሁን ይጠባበቃሉ!”
እነሆ ዛሬ በኢትዮጵያ የሰው ዘር ጠላት የሆነ ሥርዓት አለ። የሒትለርን ፀረ ሕዝብነት ለመረዳት የፖላንድ መወረር፣ የሃምሳ ሚሊዮን ሕዝብ ማለቅ፣ የስድስት ሚሊዮን አይሁድ መጨፍጨፍ መጠበቅ ይገባል? ታሪክ አላስተማራችሁምን? በአሜሪካ ላይ ስንት ክህደትና ቸልታ እንቁጠር? በፋሺስት ወረራ ዘመን ሩዝቬልትና ሴክሬተሪ ሐል ያሳዩን ክሕደትና ቸልታ አይረሳንም። አሜሪካ የበለጠ ትናገር! እግዚአብሔር ሁላችሁንም ይጠብቃችሁ!!

ህወሓት “ስሜን ልታጠፋ”ነው! (ከአብርሃ ደስታ)

$
0
0

ህወሓቶች ስሜን ለማጥፋት ዝግጅት መጀመራቸው የዉስጥ ምንጮች ገልፀውልኛል። ታድያ ቀጣዩ የመንግስት ሚድያዎች አጀንዳ ለመሆን ስለበቃሁ ህወሓትን የፈጠረ … ( ማነው የፈጠረው ደሞ?) የተመሰገነ ይሁን። እንዳዉም ሳስበው ለዓቅመ ትችት ደርሻለሁ ማለት ነው። ለማጥፋት ሚድያ የሚያስፈልገው ስም አግኝቻለሁ ማለት ነው። ስሜን ለማጥፋት ከተዘጋጁ ስም አለኝ ማለት ነው። ዕድሜ ለህወሓቶች! ለነገሩ ህወሓቶች ስም ያለውና የሌለው መለየት አይችሉም። እስቲ የሓሰት ውንጀላዎቻቸውን ለመስማት ያብቃን (ለነገሩ በቂሊንጦ ማረምያቤት ጀምረውታል አሉ)።

አብርሃ ደስታ

አብርሃ ደስታ

መስከረም አከባቢ ነው (ከዓረና ጠቅላላ ጉባኤ በኋላ)። አቶ አባይ ወልዱ ካቢኔያቸውን ሰብስበው “አብርሃ ደስታን መከላከል አንዱ የፖለቲካ አቅጣጫችን ነው” ማለታቸው ሰማሁ። በሚልዮን የሚቆጠር በጀትም መመደቡ ሰማሁ። ግን አላመንኩም። ምክንያቱም በጀት በመመደብ አብርሃን እንዴት መከላከል ይቻላል? ሰለማዊ ታጋይ ነኝ። ጠመንጃ የለኝም።

የሰማሁት ግን ብዙ ታማኝ የህወሓት ካድሬዎች ተመልምለው የፌስቡክ አጠቃቀም ሰልጥነው የአብርሃን ሐሳብ ማፍረስ እንዲችሉ ማብቃት ነበር። ግን የፌስቡክን አጠቃቀም መሰልጠን ሐሳብ ማመንጨት ማለት እንዳልሆነ ግልፅ ነው። እነዚህ የፌስቡክ ስልጠና የተሰጣቸው ታማኝ ካድሬዎች ሲጨንቃቸው በሓሳብ ከመከራከር ይልቅ መሳደብን መረጡ። በስድብ ሐሳብን ማሸነፍ ግን አይቻልም። እናም አልቻሉም።

እናም የተመደበው ገንዘብ ለታማኝ ካድሬዎቹ (የባለስልጣናቱ ቤተሰቦች) ተሰጠ። ሐሳብን ሊያመነጩ የሚችሉ ካድሬዎች በዝምድና ተመርጠው እንደየ አስፈላጊነታቸው በሑመራና ሌሎች ከተሞች መሬት በነፃ ተሰጣቸው (አርሶአደሮችን በማፈናቀል፣ ደግሞ አርሶአደር የት ይደርሳል? በረከተ ስምዖን ትዝ አለኝ)። ኢንቨስተሮች ሆኑ። ኢንቨስተሮች በመሆናቸው ህወሓትን አይተቹም እንጂ እኔም ለመንቀፍም ግዜና ፍላጎት አልነበራቸውም።

ከነዚህ መሬት የተሰጣቸው ካድሬ ኢንቨስተሮች አንዱ የግል ጋዜጠኛ ነኝ የሚል ሲሆን ባለፈው ሦስት ወራት በህወሓት መሬት እንዳልተሰጠው ሲምል ቆይቶ ዛሬ ግን በሑመራ መሬት እንዳለው አረጋግጦልኛል። እንዲህ ነው። ሰውየው ጋዜጠኛ ነው። በሑመራ አከባቢ የሚገኝ የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን በምስጢር መሰጠቱ ፅፌ ነበረ። ዛሬ አገኘኝና “የፃፍከው ስህተት ነው” አለኝ። “ስህተት ስለመሆኑ ምን ማስረጃ አለህ?” ስለው “እኔ ራሴ በሑመራ መሬት አለኝ። የኔ መሬት አልተወሰደም”አለ። ይገርማል። አንደኛ ከወራት በፊት በህወሓት መሬት ከተሰጣቸው ወጣቶች አንዱ እንደሆነ ነግሬው “ስህተት ነው። መሬት አልተሰጠኝም” ብሎኛል። ዛሬ የተበላሸበት ረስቶት ነው። ሁለተኛ በሑመራ ያለው የሱ መሬት ስላልተወሰደ ለሱዳን የተሰጠ የኢትዮጵያ መሬት የለም ማለት አይቻልም። ምክንያቱም መላው ሑመራ ለሱዳን ተላልፏል አልተባለም።

የህወሓት ፖለቲካ ስም የማጥፋት ፕሮፓጋንዳ ነው። ህወሓቶች የሰው ስም ብቻ አይደለም የሚያጠፉ፤ የሰው ህይወትም ያጠፋሉ። ይህን ሁሉ ተግባራቸው እናውቀዋለን። እናም በስም ማጥፋት ዘመቻ የሚሸበር የለም። ህወሓትን የምቃወመው መጥፎ ስለሆነ ነው። እናም በስም ማጥፋት ዘመቻ ተሰማርቶ መጥፎነቱን ቢያጋልጥ ህወሓትን የምቃወምበት ምክንያት ትክክለኛነት የሚያረጋግጥ በመሆኑ አይደንቀኝም።

አንድ አምባገነናዊ ስርዓት የሚፈፅማቸው ተግባራት ስም ማጥፋት፣ ማሰቃየት፣ ማሳሰር፣ መግደል ናቸው። ከዚህ ዉጭ ምንም ማድረግ አይችልም። ፍቅርን የማስፈን፣ ፍትሕን የማንገስ፣ እኩልነትን የማረጋገጥ፣ ስልጣንን ለህዝብ የማስረከብ፣ ነፃነትን የመስጠት ብቃት የለውም። ነፃነት ለመስጠት ብቃት ይጠይቃል። ሰው ለመግደል ግን ጠመንጃ መያዝ ብቻ በቂ ነው። ስለዚህ አምባገነናዊ ስርዓት የሚችለው ነገር መጥፎነት ነው። መጥፎ ስለሆነም ነው የምንቃወመው። ምክንያቱም የምንፈልገው መጥፎነንት ሳይሆን መልካምነት ነው። መጥፎ ተግባር በሌላ መጥፎ ተግባር ስለማይሸነፍ የህወሓት መጥፎነት በመልካምነት ለማሸነፍ እንሞክራለን። ምክንያቱም የምንታገለው ህወሓትን ለመተካት (ህወሓት የሚሰራውን መጥፎ ተግባር ለመድገም) ሳይሆን የህወሓትን የመጥፎነት ስርዓት በመልካም ህዝባዊ ስርዓት ለመቀየር ነው። የምንቃወመው ስርዓቱን ነው።

ምክር አለኝ! አሁን የታሰበው ስም የማጥፋት ዘመቻ በ2007 ምርጫ ወቅት ቢሆንላቹ ይሻላል። ምክንያቱም ዓላማቹና ሀይማኖታቹ ስልጣን ነው። ስለዚህ በምርጫ ወቅት ቢሆን መልካም ነው። ለማንኛውም ህወሓቶች መልካም ዕድል ብያለሁ (ለዘመቻው)። እንደ አኬልዳማና ሐረካት ለትዝብት የሚዳርጋቹና የሚያከስራቹ መሆን የለበትም።

ስሜ አይጠፋም። ምክንያቱም ስም የሌለው ስሙ አይጠፋም። ስም ለማጥፋት መጀመርያ ስሙ መኖር አለበት። አሁን ግን ስሙ የለም። ስም ለሌለው ሰው ስም ለማጥፋት የሚደረግ ዘመቻ ስም መፍጠር ነው የሚሆነው። ስለዚህ ስም ለማጥፋት ሲሉ ስም ይፈጥሩልኛል። እናም ይተውታል የሚል ግምት አለኝ። አጀንዳው የተነሳው እኔን ለማደናገጥ ታስቦ ሊሆን ይችላል።

It is so!!!

[ዴሞክራሲያ ቅጽ 39 ቁ. 4 የካቲት 2006 ዓ.ም] –ለዳግማዊ የካቲት ሕዝባዊ አመፅ እንነሳ

$
0
0

eprp rt
የየካቲት 66 አብዮታዊ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ጉልህና ደማቅ ሚና ያለው ክስተት ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዝንተ ዓለም የሚያስበው የሚዘክረው ኹነት ነው። የአገዛዞች ጭቆናና ብዝበዛ መጠን እጅግ አድጎ ዜጎች መኖር የማይችሉበት ሁኔታ ሲከሰት የሕዝብን ቁጣና ብሶት ያዘለ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ሊፈነዳ እንደሚችል የሕብረተሰብ ሕግ ይደነግጋል። በዓለም ላይ አስከፊ አገዛዞችን ያርበደበዱና ከሥልጣን ያስወገዱ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች በጣም በርካታ በመሆናቸው ዝርዝሩን ማቅርብ አስቸጋሪ ቢሆንም በ19ኛውና በሃያኛው ክፍለ ዘመን የተከሰቱትን የፈረንሳዩንና የሩሲያ አብዮቶች፤ በ1989-90 ዓም በምስራቅ አውሮፓ አምባገነን አገዛዞች ያስወገዱትን ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንዲሁም በ2010-12 የአረብ የጸደይ እንቃስቃሴ የሚል ስያሜ የተሰጣቸውና በተለያዩ የአረብ አገሮች ተቀጣጥለው አምባገነን አገዛዞችን ያስወገዱትን ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች ለአብነት መጥቀስ ይቻላል። በአገራችን በየካቲት 66 የተከሰተው አብዮታዊ እንቅስቃሴ በዓለም ውስጥ ከነበሩት አብዮቶች የተለየ ባይሆንም በወቅቱ ለ50 ዓመታት ያህል ስር ሰዶ የነበረውንና ማንም ሊያነቃንቀው የማይችልና መለኮታዊ ኃይል ነው ተብሎ ሲፈራ የነበረውን የአጼውን ሥርዓት ገዝግዞና አዳክሞ ከሥልጣን እንዲወገድ በማድረጉ በኢትዮጵያ
ታሪክ ውስጥ አቢይ ምዕራፍ ይዞ ይኖራል።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

[የለንደኗ ጽዮን ማርያም ቤ/ክ ጉዳይ] –ትግላችን ከሕወአትና ከግብረ-ዐበሮቹ ጋር ነው!

$
0
0

New Picture (15)
ፍርድ የእግዚአብሔር ነው! ወገን ተባበረን!
መጋቢት ፪ ፦ ፪ሺህ ፮ ዓም ከኮማንደር አሰፋ ሰይፉ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ።
ጻ! መንፈስ ርኩስ!!!
አሜን!!!
የቤተ ክርስቲያናችን ችግር ከጀመረ ረጅም ጊዜ ነው። አበው “ቁጭ ብለን የሰቀልነውን ቆመን ማውረድ አቃተን!” እንዳሉት ኾኖ ተካርሮ ለመዘጋት ከበቃች መጋቢት ፩ አንድ ዓመቱ ነው። ብዙዎቻችሁ ችግራችንን ችግራችሁ አድርጋችሁ ስትከታተሉ ስለነበር ሃተታ አላበዛባችሁም።
ባጭሩ፦ የመተዳደሪያ ደንባችን እንዲሻሻል ይወሰናል፦ከካህናትና ከምእመናን
አርቃቂዎች ይመረጣሉ፦በኅብረት ሥራቸውን ያኪያሂዳሉ
የልዩነታቸው መነሻ፦
መሠረቱ- የምእመናን ወኪሎች ቤተክርስቲያኗ ሕጋዊ ሰውነት እንዲኖራት
ያስፈልጋል ይላሉ።እስከዛሬ የተዳደርንበት ተንቀሳቃሽና የማይንቀሳቀስ
ሃብትና ንብረትዋን በሚገባ አያስከብርላትምና። ይህም ማለት ባለዐደራዎቹን
በድምጽ ብልጫ ሕንፃ ቤ.ክርስቲያኗን ሳይቀር ለሌላ ሊያሳልፉ ያስችላቸዋል (አኹን በተጨበረበረ ሕጋዊነት፦ ምልአት እንኳን ሳይኖራቸው እንዳደረጉት) “ሊሚትድ ካምፓኒ ባይ ጋራንቲ” የሚባለው ግን ያለ ጠቅላላው ጉባኤ
ስምምነት በሃብቷና በንብረትዋ እንዳሻ ማዘዝ አይቻልም። ሲባል የካህናት ወገኖች ቀንዳቸው ቆመ። አለቃው ግን- ተስማምተው፦
- የሰበካ ጉባኤው ሊ. መንበር መነኩሴ እንዲኾን ፦
- አለቃውም፦- ደሞዝ ለመጨመር ፦
– ጉርሻ ለመስጠት
- የየንዑስ ኮሚቴዎች ሊ. መንበር እንዲኾን
ረቂቁ ውስጥ እንዲካተትላቸው ሲጠይቁ፦

ምእመናን አርቃቂዎች
ሊ. መንበሩ መነኩሴ ይኹን ማለቱ ቃለ- ዓዋዲውን “ከካህናት ውስጥ ይመረጣል” ስለሚል ያፈርሰውዋል። ያገሪቱንም ሕግ ይጻረራል፦ እንዲሁም የዴሞክራሲን መንፈስ፦ የተመዘገብንበትም የግብረሠናይ ድርጅት መመሪያ ስለሚንድ ልንስማማ አንችልም።
- ደሞዝ መጨመሩም የጠቅላላ የሰበካ አመራሩ ሥልጣን ስለኾነ፡
- ጉርሻ የተለመደ ስላልኾነና፡ ካስፈለገ ጉባኤው ሊወስነው ስለሚገባ
- የአለቃው የየንኡስ ኮሚቲዎችም ሊ. መ. መኾን፦ የየኮሚቴዎችን ሥልጣንና መብት ስለሚጋፋና ሥራ ስለሚበደል ፦
- አለቃው፦ በሊ.መንበርነት ሰበካ ጉባኤው ላይ የኹሉንም ከአባላቱ ጋር ኾነው ስለሚያዩት በገለልተኛ ዳኝነት ጉዳዩን ሊመረመሩት ይችላሉ። አለዚያ ግን ማንኛውንም በንኡስ ኮሚቴዎች የሚቀርበውን ኹሉ በፈለጉት መርተው ሰበካ ጉባኤው ስብሰባ ላይ ዳኛ በመኾን ፈንታ ጠበቃ በመኾን ሥራ ይበደላል፤፡ ስለዚህ
ንኡስ ኮሚቴዎችን ማጨናነቅና ሥራን መበደል ስለሚኾን
አንስማማም፦ በመባላቸው ካህናት ዐውደ-ምሕረቱ ላይ አሳዛኝና
አሳፋሪ ስብከታቸውን ቀጠሉ። ለአብነት አንድ ላቅርብ፦ “እኛ
ካህናት የምንለውን የማይቀበል በመንግሥተ-ሰማያት ቦታ የለውም።”

ይህ አባባል የቫቲካኖቹ የቅ. ጳውሎስን ርዕሰ አድባራት ሲሠሩና ገንዘብ ሲያጥራቸው ማይምኑን አማኝ፡”የሞተብህን ዘመድ እያሰብህ(ሽ) ገንዘብ ብትሰጠን የሞተብህ ዘመድ ከሲኦልም ቢኾን መንገሥተ-ሰማያት በቀጥታ ይገባል።” እንዳሉት አይደለም??!የኛዎቹ ግን ይባስ ብለው ወደራስ አዞሩት!!! አንዳንድ የታሪክ ጸሐፊዎች ስለዚህ ጉዳይ ሲጽፉ “ለማርቲን ሉተር የመጨረሻዋ ገለባ ይኽች ነበረች።”* ይላሉ። ጠንቁም ካቶሊክ ቤ.ክርስቲያንን አፍርሶ ፕሮቴስታንትን ወለደ። እኛ ጋ ምን በመፈለግ ነው??
የምእመናን አርቃቂዎች ጥያቄ አንድ ብቻ ነበር ነውም። ይኸውም ያረቀቅነውን የተማስማንበትንና ያልተማማንበትን ይዘን ወደ ሰየመን አካል (ጠ. ጉባኤ.) አቅርበን ጉባኤው ይወስን ቢሉ አሻፈረኝ ከማለት አልፈው – “የግል ኩባንያ ሊያደርጓት ነው..ለግላቸው ሊበደሩባት ነው… ምሥጢራት እንዲደፈሩ ሊያደርጉ ነው… ቀኖናን ያፋልሳሉ — ቃለ-ዓዋዲን ያፈርሳሉ ወዘተ” የወሬ ዘመቻ ባርቃቂ ጓደኞቻቸው፡ በቤ/ክርስቲያ ነባርና ቅን አገልጋዮች ላይ ከፈቱባቸው።

ይህ የወሬ ዘመቻ ያሳዘናቸው ሽማግሌዎች በገዛ ራሳቸው ተነሳሽነት ሊያደራድሩ ቢፈልጉ መለሷቸው። ምእመናን በዚህ ተስፋ ሳይቆርጡ ኹለት ጊዜ የተለያዩ ሽማግሌዎች የቀድሞው አለቃ “እኔን ካልደገፋችሁ በማለት አሳዝነውና አሳፍረው መርጠው ላኩ። የነእርሱም ልፋት ከመጀመሪያው አልተለየም። አሉባልታው ግን ነፈሰ።
እኔም፦ ‘እንዴት እንዲህ ይኾናል?’ በማለት ነበር ከምእመናን ዐርቃቂዎች አንዱን ስጠይቅ፦ በ ’እንዴት ጠረጠሩን’ ድምጸት የካህናቱ መግለጫ ባለፈው ሳምንት ነበር የኛ የሚቀጥለው ስለኾነ ሰምተው ይፍረዱ’ አለኝና ሄድሁ። ቀኖናውንና ቃለ-ዓዋዲውን ከካህናት በበለጠ አጥንተው፦ የፈረሰው በካህናት እንጂ በነርሱ አለመኾኑ ገልጸው “ እስቲ ቀኖና ፈረሰ ፦ ቃለ-ዓዋዲ ፈረሰ የምትሉትን በአንቀጽ ጠቅሳችሁ አቅርቡ ቢባል። ከየት??
ምእመናን አርቃቂዎች ለምእመኑ አንዲት የቀኖና አንቀጽ እንዳላፈረሱ፤- እንዲሁም ቃለ-ዓውዲውን ለሥራቸው እንደተመሩበት አስረዱ፤- ካህናት ግን ያወረዱባቸውን ሕዝቡን በሀሰት ሊያሳስቱ የሞከሩባቸውን በማስረጃ ሊያቀርቡ እንደማይችሉ ሲያረጋግጡባቸው፦
“ጌታዋን የተማመነች በግ ላቷን ከአጥር ወጪ ታሳድራለች።” እንዲሉ ‘መነኩሴ ናቸው፦ አደራ ያከብራሉ፦ ቤተክርስቲያናንን አክብረው ያስከብራሉ፦ እኛንም ያስተምራሉ፦ ብንጣላም ያስታርቁናል። ባህልን ጠብቀው ያስጠብቁናል፦’ ብሎ የመረጣቸውን ምእመን በአሳፋሪና በአሳዛኝ ኹናቴ ከድተው አገራችንንም ሃይማኖታችንንም ለታዛቢ ጣሏቸው።

እኔንና መሰል አዛውንትን የሚያሳዝነን ቅዱስ መጽሕፍና እምነታችን እጅግ ያልዘለቀላቸውን ወገኖቻችንን ስላሳሳቱብን ነው። ለሥልጣንና ሹመት ብሎም ለጥቅም መፈጽም ላይ ያሉትን ወንጀል፦ “ለሃይማኖቴ ነው ብሞትም ግድ የለኝ|!” ሲሉ በውኑ ለሃይማኖት መሞትን የሚፈልጉ ከኾነ፦ ከአንድ አምስት ስድስት ዓመት በፊት ሲኖዶስ ውስጥ ብዙ ካህናት በአክራሪ እስላሞች እንደሚገደሉ አቤቱታ ሲያቀርቡ፦ ሟቹ የሲኖዶስ ሊ.መንበር፦ እንደ መቼውም ልባቸው ሥራቸው ላይ ስላልነበረ ፡” ማሕበረ-ቅዱሳን ይላኩ፡” ቢሉ አንድ ልባቸው የተነካ የቤተክርስቲያኗ ልጅ በንዴት ተነስተው፦” አላሁ አክበር!” እያለ እጸድቃለሁ ብሎ ወደሚገድለው ማሕበረ-ቅዱሳን ይሂዱ ማለት ምንድር ነው?” ያሉትን በማስታወስ በዕውኑ ለሃይማኖታቸው ስማእትነትን ማግኘት ከፈለጉ የኛ የቀድሞው አለቃና ግብረ-ዐበር ካህናት ወዳሉበት ሠፈር ለምን አይሄዱም?” እዚህ ወጣቱንና ያልዘለቀውን ከማሳሳት? ማተባችሁን በጥሱ ያላችሁ አለ? ከኛ ወገንስ ማተቡን የበጠሰ አለ?
ሊ. ጳጳስ አባ እንጦስ እንዳሉት፤ ‘ቤትክርስቲያን መዝጋት መንፈሳዊ አይደለም።’ በኢመንፈሳዊነት አቢይ ጾም በተያዘበት ዕለት፡ ዘጓት!! ይህም ያለንበእትንም አገር የተመዘገብንበትንም ሕግ ይጥሳል። በማግሥቱ አንድ-ኹለት ካህናት ይዘው ወደ ኤምባሲ ዘለቁ። በሦሰትኛው ቀን ወደ ሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሊ.ጳጳስ ቢሄዱ፦ “ አንተ… ቀድሞውንስ እኛ እዚህ እያለን ኤምባሴ ምን ወሰደህ?” ተብለው ከተዘለፉ በኋላ በኹለቱ የገዥዎች ወኪሎች፦ በኤምባሲውና በጳጳሱ መካከል መመላለሱ ጦፈ።
እነሆ! ስደተኛ ነኝ፦ የአ.አበባውን ሲኖዶስ ለ.መንበር ስም በጸሎት አላነሳም፦ አቡነ እንጦስ የተባሉት የወያኔ ካድሬ እኔ ካልሞትሁ የማርያምን ቤ/ክን በር አይረግጧትም! ብለው የደነፉት ጠቅልለው ከገዥዎቹ ጉያ ገቡ። ገዥዎቹም፦ ምናቸው ሞኝ?! ‘እንዲህ ብለኸን/አርገኸን አልነበረም ሳይሉ እጃቸው እስቲገባላቸው ድረስ ያሽሞነሙኗቸዋል። ከቅ.ማርያም ወደ እነ ጳጳሱ የሄዱትን ኹሉ አግደዋል፤፡ በኋላም በዚህ ዓይነት ያባረሯቸውን ካህናት ጫማቸው ላይ ወድቀው ማሩኝ አሉ። በኛ ላይ ወገን ለማብዛት።
አዲስ አበባንም አዘወትሩ። ቶሎ ቶሎ እየተመላለሱ በሄዱ ቁጥር ደግሞ ሻንጣዎቻቸው እየተወጠሩ ነው። ‘በምን?’ ውስጥ የማንገባው ሳናውቀው ቀርተን ሳይኾን በትዝብት ማለፍን መርጠን ነው። አኹን ይህችን ጽሑፍ እንዳቀርብ ያስገደደኝ፦ በጥቅምትና ኅዳር በውጣው “ ዜና ቤተክርስቲያን ዘ ኢትዮጵያ ” ላይ የሰጡትን ቃለ-ምልልስ አይቼ ነው።
ለመመለስ ይህን ያህል ጊዜ የፈጀብኝ፦ለጽሑፌ ርዕስ ተቸግሬ ነው። እንኳንስ የመነኩሴ ቆብ የደፋውን ማንንም ‘ ዋሾ ‘ ማለት ይከብዳል። የባህል ተፅዕኖም ቀላል አይደለም። መተዉ ደሞ ሊላውን የማሳሳት ተባባሪ መኾን ነው። በዚህ ውስጥ እያለሁ መጀመሪያ የመጣልኝ ርዕስ

“ከእውነት ጋር የሚያስተዋውቅልን/ የሚያስታርቅልን ያለህ!” ነበር፦
“ከታማኝነትስ?”
የሚለው ደግሞ ይጠዘጥዘኝ ጀመር።
እያመነታሁ ሳለሁ ‘በፍኖተ ዴሞክራሲ’ የኢሓፓ ሬዲዮን ላይ በአንድ ወቅት
(ለኔ ጥሩ የዜና ምንጭ ያለው ኾኖ አግኝቼዋለሁ።

“ ለምን ይዋሻል? – እስከ መቼስ ይዋሻል?”

የሚለው ትዝ አለኝ። ይህን ወደ መምረጡ ላይ ሳለሁ በቅርቡ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ደግሞ፦

“ የምዋሸው ዕውነቴን ለመቆጠብ ብዬ ነው።”

የሚል ርዕስ አየሁ። አይጣጣ ! ምን እዳ ገባሁ? እያልሁ መጽሐፍ ቅዱሴን ለመግለጥ ሳስብ፦ ‘ በደረጃ ሂድ እንጂ! ‘ የሚል ስሜት አደረብኝ። ስለዚህ ስለ ‘ ውሸት ‘ ምድራውያን ዐዋቂዎች ምን ብለው ይኾን? በማለት ማገለባበጥ ጀመርሁ። እዚያም ላይ ወደ እምነት ተመሳሳዮቻን ሄድ ብዬ መቃኘትን ሳስብ፦ የሩሲያን ደራስያንን መረጥሁ። በዚያው ባነበብሁት ቋንቋ፦
london
Simply put by Leo Tolestoy,

“ Anything is better than lies & deceits.” ብሎአል

The writer of “ The Brothers Karamazov “ Fyrdor Dostoyevsky

“ Above all, don’t lie to yourself. The man who lies to himself and listens to his own lies comes to a point that he cannot distinguish the truth within him, or around him and so loses all respect for himself and for others and having no repsect he ceases to lose love.” (አጽንዖቱ የኔ)
ይህን የቀድሞው አለቃ በየሄዱበት ስብሰባም ኾነ ቀብር ወይም ድግስ ቀምሰውታል። (ለተመልካች እስከሚከብድ ድረስ) እኔም አልጠቅስም!

ታዲያ ምእመናን ወገኖቼ፦ የዶስቶየቪስኪው ምክር ቅዱስ ጳውሎስ በመጀመሪያው የቆሮንቶስ መልእክቱ ም. ፲፫ ላይ ልብ በሚሠብር ዓይነት ያሠፈረልንን አያስታውሳችሁም? በትንሹ እነሆ፦ አጭር ናትና ምዕራፏን ዝለቋት።አደራ !! አኹን ግን ከ ቁ ፩-፫ ያሉትን ላስነብባችሁ፤፡
“በሰዎችና በመላእክት ቋንቋ ብናገር ፍቅር ግን ከሊለኝ እንደሚጮህ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ኾኛለሁ።ትንቢት ቢኖረኝ፦ምስጢርንም ኹሉና ዕውቀትን ኹሉ ባውቅ፦ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ኹሉ ቢኖረኝ፦ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። ድሆችንም ልመግብ ያለኝን ኹሉ ባካፍል ፦ ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ፦ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም።”
ታዲያ በኛ ላይ የሚመጻደቁትና ልጆቻችንን ያሳቱብን ካህናት ምን ለማግኘት ነው? ከአካባቢያቸው ውርደትን፦ ንቀትን.. ለምን? በገዥዎች ለመሾም!?!?

ለሦስት ከፍለውን፦ አንዱ ወገን በሀዘን እቤቱ ሲቀር ፦ ሌሎቻችን በዚህ አገር መራር ብርድ በአቢይ ጾም ከገረገራው ስንጸልይ የኛ ካህን መላከ ብርሃን ብርሃኑ ወደዚያኛው ወገን በመሄድ “ እባክችሁ አብረን እንጸልይ። ተለያይተን የምንጸልየው አያርግም።” ብለው ቢማጸኑ ከነሱ መዘምራን አንድ-ኹለቱ “እኛ ከአሕዛብ ጋር አንጸልይም!” ሲሉ፦ ጥቂቶች ተጨመሩላቸው። እውን እነዚህ ልጆች የ”አሕዛብን” ስንኳንስ ትርጉሙን ቃሉን ዐውቀውት ነው?
ወንድም እህቶቼ ሆይ፦ ያስረዘምሁባችሁ ግንዛቤያችሁ የተሟላ እንዲኾን ነውና ይቅርታ። እንደምንም ብላችህ የመጨረሻዋን ገጽ ተመልከቱልኝ አደራ!

ጌታ በወንጌሉ ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ኹሉ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባህር መስጠም ይሻለው ነበር።” ማለቱ ተዘንግቶ ነው? ተንቆ!!
እዚህ ላይ ታናናሾቹ ሲል የእድሜ ጨቅላዎችን ብቻ አለመኾኑንእንደማይዘነጉት ተስፋ አለኝ።
በዜና ቤተክርስቲያን ላይ ለወጣው (የልብ-ወለድ) መግለጫ በብዛት ከላይ በተገለጸው የተሸፈነ ይመስለኛል፡፤ በተለይም ለችግሩ መነሻ የነበረውና አኹንም ድረስ ከቤተክርስቲያኗ ልጆች ጋር በጠቅላላ ጉባኤ ቀርቦ ከመነጋገር ብሎም ከመነጻጸር በየቦታው… የሚነዛው …ነው። አማርኛችን ሰፊ ሲኾን ለኹናቴው መግለጫ በሚኾኑት ለመጠቀም ትውፊትና ባህል ስለሚከለክሉ ልለፈው። የዜና ቤ/ክንን ለማጠቃለል፦ ከታሪክ መዝገብ
“ እባብ ሆነ ውቤ ሰውነቱን ትቶ
ሊነክ(ግ)ስ ነው አሉ ካቡን ተጠግቶ።”
የተባለውን “ያብዬን ለእምዬ!” ስለኾነ እዚያው ተቻቻሉበት። ከአቡኖች ብሎም ከሲኖዶስ የተጠጋው ማንነው? ያውም “ የፓትሪአርኩን ስም አልጠራም!” ካለ በኋላ!

አኹን በግለ ሰቦች ላይ በድፍንም ኾነ በነጠላ ሊያጎድፉ ስለሞከሩት ልመለስ።ከዜና ቤተ ክርስቲያን ሳልወጣ፦

“ ማንም ሳይወክላቸው ቤ/ክንን(ባልተጠቀሰ ቃለ-ዓዋዲ ተደግፈው)ኃላፊነቱ በተወሰነ የግል ኩባንያ ኹለት ግለሰቦች ባለንብረትነት በግል ስማቸውና በግል ባለ ንብረትነት በመኖሪያ ቤታቸው አድራሻቸው
በማስመዝገብ ቤ.ክንን በንግድ ተቋምነት ለመቆጣጠር እንዲያመች በሕገ ወጥ መንገድ በስውር አስመዝግበው፡ ተገኝተዋል።” ብለዋል። እግዜር ይቅር ይበልዎ።ድሮ የመስኮቡ ክሩሾቭ ሲናገሩ የሰማሁትን አስታወሱኝ። የቃል-በቃል ጥቅስ ሳይኾን መልእክቱ ‘ውሸትህ እንዲታመን ከፈለግህ እውነት ቀላቅልበት’ ነው። እዚች እጠቅስኋት ውስጥ እውነቱ ኹለት ጽኑ ስደተኞች ኢትዮጵያውያንና ለቤተክርስቲያንዋ በገንዘብም በጉልበትም የለፉ የተባለውን መፈጸማቸው ነው። ሌላው እውነት በግል ስማቸውና አድራሻቸው ማድረጋቸው ነው። ያደረጉበትም ምክንያት የቀድሞው አለቃ ለሌላ አሳልፈው ሊሰጡ ቢሞክሩ ባለቤት እንዳለው በማስመዝገብ በድብቅ ስም እንዳይዘዋወር ነው። ይህም ሠርቷል። የቀድሞው አለቃ ይህን ሊያውቁ የቻሉት የተፈራውን እኩይ ተግባር ሊፈጽሙ ሄደው ‘ ይህማ ባለቤት አለው!’ በመባላቸው አይደለም? እንግዲያውስ በባለቤትነት መመዝገባቸው እንዳለ ኾኖ ርሳቸውም በአለቃነቴ እንዳለሁ ነኝ እያሉ እያስቸገሩ ሳሉ፦ ታዲያ እነዚህ በባለቤትነት የተመዘገቡትን ግለ-ሰቦች በሕገ-ወጥነት ባለቤትነቱን ከወሰዱ ለምን አልከሰሱም? አለመክሰሳቸው ትልቅ የእምነት ጉድለትን አያሳይም? ሕጋዊ ተግባር መፈጸማቸውን ካወቁ ለምን ለአሉባልታ አበቁት? በሃሰት ለመወንጀል? ሊላው ሃተታ ኹሉ ክሩሾቭ እንዳሉት ነው።
-“ …ካህናት በሥርዐተ ጥምቀት ላይ በጸሎት እንዳሉ መስቀል በመቀማት…” እግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ! የማን መስቀል ተቀማ? ግቢውን በፖሊስችና በውድ ዋጋ (በኤምባሲ) በቀጠሯቸው በግል ጠባቂዎች ሞልተውት ነበር፦ ታዲያ እውነት ከነበረ የቢተክርስቲያኗ ንብረት ሲቀማ ለምን አላስመለሱም? ይህም
በሕግ የሚያስጠይቅ ነው።
የአንዳንድ ሰው ለልበ-ወለድ ነገር ያለው ስጦታ ይደንቃል።

“ …በሕገ-ወጥ መንገድ የመረጧቸውን ግለ-ሰቦች ስም ለባንክ በማስተላለፍ የቤተ ክርስቲያኑን የባንክ ሂሳብ በግለ ሰብ አድራሻ በማዞር …” እንዴ እስካሁን ድረስ እንዳሉት የቤተ ክርስቲያን ገንዘብ ሲዘረፍ እያወቁ ሕግ ባለበት አገር ዝም ካሉ ተጠያቂው ርስዎ መኽንዎን በራስዎ መሠከሩ። በችሎታ ማጣት ነው ይባል? ኃላፊነትን አለማክበር? ወይስ በግድ-የለሽነት?
- በተሰለጠነበት የልብ-ወለድ ዝባዝንኬ በኋላ “…ቤተ ክን ውስጥ በጫማቸው ዘልቀው በመግባት…” ፈሪሃ እግዚአብሔርን ፈጽማችሁ ከልባችሁ አውጥታችሁታል ማለት ነው? ይህ ኹሉ አገር ውስጥ ይህንን …የሚያነብቡትን የእምነት ወገኖቻችንን ለማሳዘን? ምን አጠፉ? እነርሱማ ሃዘን ምን ገድዶአቸው? በሽ-በሽ አይደለም እንዴ? ብሎም በኛ ለማስፈረድ? እንደተጫማ እንደ ኹል ጊዜም የሚገባ በእግዚአብሒር እጅ የተያዘና የአገሪቱም የጤና ተቅዋምተገቢውን ድጋፍ የሚያደርግለት አንድ ወንድማችን መኾኑን እያወቁ? አገር ውስጥ ያለውን ሕዝበ ክርስቲያንን ማሳሳት ይገባል? የውጪው አነሰና ነው?
እኛን ስደተኞችን ለማስጠላት? ይህ ወንድማችን ደግሞ የቤተ ክርስቲያኗ ጽኑ አገልጋይ መኾኑን የማያውቅ የለም።

ዜና ቤ/ክን አንድ ወገን ሰምቶ ሳያጣራ በዚህ ወገን ያለነውን ክብር በመንካትና ሌላውንም ሕዝብ በኛ ላይ በማሳሳቱ ይህን መልስ ለማስተካከያ ካላተመው በጸሐፊውና ባታሚው እንዲሁም በባለቤቱ ላይ ሕጋዊ ርምጃ የመውሰድ መብታችን የተጠበቀ መኾኑን እናስታውቃለን
“የጋዜጣው መለክት” ብሎ ውሸት ተቀብሎ ውሸትን ያባዛው በውሸትም አንባቢያን ወገኖቻችንን ያሳሳተው ሳይውል ሳያድር የሚገባውን ነገር መፈጸሙ ይጠቅመዋል። ይህ፦”ጌታዋን የተማመነች..” ሂደት ውሎ አድሮ ያስከፍላል።

ግለ-ሰቦችን በሚነካ ጉዳይ!

በገዜጣው ለወጣው የግለ-ሰቦችን ለማጠቃለል፦

“ ከካህናቱም መካከል እነ ቄስ ብርሃኑ ብሥራት የመሰሉት…” ተብሎ
የተጻፈው መላከ ብርሃን ብርሃኑ ናቸው? ሳይመነኩሱ የመነኩሴ
ባህርይ ያላቸው፦ የተማሩ፦የተከበሩና የተወደዱ፦ ጽኑ አገልጋይ
ጥሩ መምህር፦አርአያነታቸው የሚፈለግ፡ ናቸው ከሚኖሩበት ከለንደን
ከምስጋናና ፍቅር በስተቀር ስንኳን የጸያፍ ነቀፌታ ቅሬታ እንኳን ሰማሁ
ያለኝ አላጋጠመኝም። እስቲ ዘርዘር አድርጌ ግልጋሎታቸውን ለንባቢያን
ላቅርብ፦

ሀ- በአሜሪካ-
-ሜሪላንድ – ቦልቲሞር፦ ደብረ-ብርሃን ቅ. ሥላሴን መሥራች
-ላስቬጋስ – የኃመረ ኖኅ ኪዳነ-ምሕረት ወሚካኤል አቋቋሚ
ለ- በአውሮፓ፦
– ስዊድን፦ ደብረ-ሰላም ቅድስት ማርያም መሥራች
– ስዊትዘርላንድ፦በርን የደብረ-አሚን ተክለሃይማኖት “
– ሆላንድ፦ ዴንሃግ፦ የዉሉደ-ብርሃን የወጣቶች የሰንበት ት/ቤት መሥራች

ስለርሳቸው የሚሰማው ፍቅር፦ ውዳሴና አክብሮት ነው። ይበልጥ ደግሞ
ቀድሰው ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ፈትተው አቀብለው በመጨረሻ
በእጃቸው በሚያሳልሙበት ጊዜ ትንፋሻቸው ‘ቁርጥ-ቁርጥ’ እያለ፡ ወደ ሴቶች
ወተት ማውጫ ይወርዳል ተብሎ ተነግሮባቸው አይታወቅም።

ታዲያ እኒህን በስም ሳይመነኩሱ በግብር የመነኮሱትን በብቁ
ችሎታና በመልካም ግልጋሎታቸው ከቀድሞው አለቃ ቢያንስ
ከአራት ዓመታት በፊት
የ ‘ መልአከ ብርሃን ‘ ማእረግ የተሰጣቸውን በርስዎ የተነፈጋቸው በምን ሥልጣን ነው? ወይስ ማእረጉ የተሰጣቸው በብቸኛነት በአሜሪካ፦በዌስት ኢንዲስና በደቡባዊ አፍሪካ ለቤተ ክርስቲያናችን ከአርባ ሺህ
ልጆች በላይ ልጆች ባፈሩላት የምራባዊው ዓለም ሊቀ ጳጳስ በነበሩት መሾማቸው? ወይስ እኚህ የተቀደሱና የተባረኩ እውነተኛ የኢትዮጵያና የቤተክርስቲያኗ ልጅ ቆራጥ ልጅ በቀውጢው ጊዜ ልጅነታቸውን እንደ ብዙሐን ተብረክርከው ያልካዱ በስደተኝነት ለብዙሐን አርአያ መኾናቸው ተብረክራኪዎችን አስቀንቶ የርሳቸውን ሹመት ላለመቀበል የተደረገ ሴራ ነው? ጌታዬ ይግባኝ በሌለብት ቃሉ “ማንንም አባት አትበሉ!” ባይል እኒህን ሊ.ጳጳስ አቡነ ይስሐቅን ‘አባት!’ ብላቸው ክብር ይሰማኝ ነስበር። መሬት ይቅለላቸው።
ይህም ቢኾን፦ በቆሙበት አለመርጋት ነው። በአራተኛው ፓትሪአርክ የሚመራው የውጪው ሲኖዶስ የሾማቸውን እንቀበላለን ተብሎ የለ? አሳዛኝና አሳፋሪ! ይህ ኹሉ ልፋት ምድራዊ ጌቶቻችሁን ለማስደሰት? ታዲያ ጌታችን

’ለኹለት ጌታ…” ያለው ተፈጸመባችሁ አይደለም? ማንን ለማስደሰት?
ትርፉ ትዝብት ነው።
ወገኖቼ
“የገብርኤልን መገበሪያ የሰረቀ ሲለፈልፍ ያድራል!” ሲባል ሰምታችሁ የለ!?

“ይሁን እንጂ በለንደን ያለውየኢትዮጵያ ኤምባሲ በታቻለው መጠን እየረዳን ስለሆነ…”
ብለው አፍረጠረጡት፦ ይህ ተሰውሮን ሳይኾን… ሕገ-መንግሥታቸው
“መንግሥት በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ አይገባም።” ያለውን በማፍረጥረጥ ማስረጃ መስጠታቸውን ነው የወደድነው።

የኤምባሲው ርዳታ ምን ምንን እንደሚያጠቃልል በክፍል ኹለት እገልጻለሁ

እነዚህ በደርግ የጦር ሹማምንትነት የሚብጠለጠሉት የቀድሞው አለቃ “ከሸፈቱ ይቅርታ፦ እውነተኛ አቅዋማቸው ከተገለጸ በኋላ፦” የመጡ አይደሉም።ኹሉም፦ ማለት ይቻላል፦ከርሳቸው በፊት በተለያዩ የቤተክስቲያኗ ኮሚቴዎች ውስጥ ያገለገሉ ናቸው።ቤተክርስቲያኗም ከዕዳ ነጻ እስክትደርስም ኾነ በኋላ በተፈለጉበት ተግባራት ተሠማርተው አገልግለዋል አኹንም ያገለግላሉ። አንዳንዶቹማ መነኩሴ አገኘን ብለው እንደግል መኪና ነጅነት ድረስ ያገለገሉበት ወቅት ነበር። ዋጋቸው መወረፍ ኾነ እንጂ- በቀድሞው አለቃ በኩል!
ደግሞ ፖለቲከኞች – ፖለቲከኞች የሚባለው ባገር ላይ የተጫኑትን ተቃዋሚዎች ለማለት ነው እንጂ ሊላ ምክንያት ምንም የለ። ይህም ገዥዎቹ የሚቃወማቸውን ኹሉ “አሸባሪ!” እንዲሉ የገዥዎቹ ደጋፊነታቸውን ለማረጋገጥ የገዥዎቹን ተቃዋሚ ስደተኞችን “ፖለቲከኛ!” በማለት ለመቅረብ መኾኑን የሚያረጋግጥ ነው።
አንዱ ‘ፖለቲከኛ – ፖለቲከኛ’ ሲባል የመለሰው ለጥቅስ የሚገባ ነው። “እኔ እኮ ክርስቲያን የኾንኩት እንኳን ፖለቲከኛ ልባል ፖለቲካ የሚባል ነገር ሳልሰማ ነው።” አለ። የቀድሞውም አለቃ ፖሊስ ጠርተውና በዐውደ-ምህረቱ ላይ ከነጫማው እጁን ይዘው መጥተው ፖለቲከኛ የተባለው ወንድማችን ሲናገር፦ “ዚስ ዚስ ፖሊቲካ! “ ቢሉት ፖሊሱ ገርሞትና ታዝቦ “ እዚህ አገር ማንም ባመነበት የመናገር መብት አለው። ፀጥታ ያደፈረሰበት ኹናቴ የለም።” ብሎ እጁን አስለቅቆ እንደ ወጣ ተነግሮኛል። እዚህ ላይ በሰበባ-ሰበቡ ፖሊሶች ሲጠሩና ዐውደ ምሕረቱም ላይ ሲያንጓጓቸው ሳይጫሙ ኖሯል? ይህ ማነብነብ ከወጣትነት ትምሕርቴ አንድ ነገር አስታወሰኝ። “ብዙ ሲዋሹ ለአንዳንዱ ዕውነት ይመስላል”
የሚባለውን። ማንን ለማሳመንና ከማንስ ወገን ለመኾን የተደረገ ስልትና ጥረት እንደኾነ “ዶሮ ጭራ የምታወጣው ነው።”
በተረቀቀው ውስጥ አርቃቂዎቹ ‘ለፖለቲካ መነገገሪያ ትኾናለች’ የሚል እንኳን ተነባቢ ዐረፍተ-ነገር በአንድምታ የሚደረስበት ዐረፍተ-ነገር ቀርቶ መንፈሱ አለ??
ወደ ትውስታዬ ስመለስ ዝነኛው ሼክስፒር በጻፈው ጁሊየስ ሲዘር ላይ
“ ከንቱ ስባሄን አልወድድም!” ይላል ጁሊየስ ሲዘር፦ ጸሐፊውም
“እንዲህም በማለቱ ሲዘር ራሱን በከፍተኛ ደረጃ በከንቱ አወደሰ!” ይለዋል።(ከንቱ ስባሄ ለራሱ አደረገ ሲል ነው) የቀድሞውም አለቃ ፖለቲከኛነታቸውን በዚህ መልክ ያለማቋረጥ ያነበንቡታል።
አኹንም ወገኖቼ ሕወአትንና ግብረ-ዐበሮቻቸውን ለማስደሰት በተናገሩ ቁጥር የደርግ ከፍተኛ መኮንኖችንና በተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት ውስጥ ተሳታፊዎችን በመወረፍ ጌቶቻቸውን ሲያስደስቱ፦ሼክስፒር እንዳለው የራሳቸውን ፖለቲከኛነት በነጋሪት ያስተዋውቃሉ። ለማያውቃቸው!!!

ይባስ ብለው “ ንጉሡን ያወረዱ፦ ፓትሪአርኩን ያስገደሉ” ማለታቸው ተወርቶአል። እዚህ ላይ፤
“አንተ ግብዝ፦ ሌባ ጣትህን በሰው ላይ ስትቀስር ሦስቱ ጣቶችህ ወዳንተ ማመልከታቸውን አትርሳ” ያለውን ማስታስወስ ይጠቅማል። በ ፷፮ ዓም ወሬው ኹሉ ስለ ሶሺያሊዝም በነበረበት ጊዜና ሕዝቡም ስለሶሻሊዝም የሚያውቀው ፀር-ሃይማኖትነቱን ስለነበር ቆዝሞና አጉሞተሞቶ ነበር። ይሄን ጊዜ ያኹኑ ሊ.ጳጳስ መልከጼዴቅ፦ ሊ/ሥልጣናት ሃብተማርያም ለቤተክርስቲያናችን እሁድ እሁድ ጠዋት የሬዲዮ ፕሮግራም አስፈቅደውላት ስለነበር በዚች ፕሮግራም አንድ ጎረምሳ “ቀሲስ” ‘የሶሺያሊዝምና የወንጌል ትምሕርት አንድ ናቸው። ኹለቱም ኹለት ያለው አንዱን ለሌለው ይስጥ ይላሉ’ ብሎ ሕቡን ያስተኛ በማን ፈቃድ ነበር? ካለስ በኋላ ከቤ/ክን ሃላፊዎች “ወንጌልንና ሶሻሊዝምን በአንድ ዓይነት አታቀርብም!” ብሎ እንኳን ቅጣት ግሳጼስ አድርሶበታል? ሲኾንስ ጠንካራ ማስተባበያ መስጠት አይገባትም ነበር?? አኹን ታዲያ ‘የእምዬን ለአብዬ’ መስጠቱ ሕወ አትንና ግብረ-ዐበሮቹን በማስደሰት ለመሾም ነው?? ይበልጥ ደግሞ የስደተኛን ንብረት በማስረከብ!!! ማን ይኾን በነገ ሊያዝዝ የሚችል?

በጉዳያችን ገብተው ስለነበሩ ወይም ስለገቡ ሊ.ጳጳሳትና ስለ ሲኖዶስ በክፍል ኹለት እገልጻለሁ፡
አንዳንድ የቤት ክርስቲያኗ ልጆች፦በብዙ ልፋት አርቃቂዎች የሠሩትን ለባለ ጉዳዮች እንዲያቀርቡ ኾኖ፤- ካህናት የረቂቁን መግለጫ ተራቸውን ጨርሰው፦ የምእመናንም ወኪሎች ተወጥተውት በስምምነቱ መሠረት የጠቅላላ የምእመናኑ ተራ ላይ ካህናት “እኛ በቀረበው ላይ መናገር አለብን።” ሲሉ ምእመናን በውስጣቸው ታምቆ የነበረው ፈንድቶ “የኛ ተራ ነው!” ባሉ ጊዜ ኹኔታው ለቁጥጥር የማያመች ነበር። ከዚህ ቀደምም እንደገለጽሁት፦ በዚህ ጊዜ የቀድሞው አለቃ ከዓውደ ምሕረቱ መድረክ ወደ ምእመኑ ሲመጡ ሳይ፦ በነበረብት ኹኔታ ቢወርዱ የሚከተለውን በመፍራት ለመከላከል ስሄድ፦ አንድ በጣም ትሁት፦ ሰላምተኛና ታዛዤ የነበረ ወጣት፡ ፊቱን አጨማድዶ “ርስዎ ደግሞ ምን ሊያደርጉ መጡ?” ያለኝ አይረሳኝም። እንዲሁም ከህቶቻችን “ኮማንደር -ኮማንደር- አይሂዱ! አይሂዱ!” ከሚሉት ውስጥ አንዷ ልብሴን በመጎተት የተማጸነችኝን አስታውሳለሁ። ይህን ያነሳሁበት፦ የቀድሞውን አለቃ ከአፋፉ ላይ ሳገኛቸው “ይህን ኹሉ ያቀነባበሩ ርስዎ ነዎት!” በማለት ወደ ተረበሸው ሕዝብ በጃቸው አመለከቱ። ለካስ ‘ እባክዎ አይሂዱ!’ እያሉ የሚከላከሉኝ በቀድሞው አለቃ እኔን የነገሩ አንቀሳቃሽና የኋላ መሪ አድርገው ያሳድሙብኝ ስለነበር ነው።
ይህ ክብር ለኔ በምንም ምን አይገባኝም። “ከብት ያልዋለበት ኩበት ለቀማ !” ነው። ከዚህ ቀደም በዚቹ ቤ/ክን የተነሳ ስሜ ተጥርቶ ስለነበር አኹንም ለማያያዝ ነው፤፡ ከእውነት የራቀ ኾነባቸው እንጂ።የመጣሁት ከቦካ በኋላ ነው እውነቱን አግኝቼ ለማግባባት ልሞክርም ነውይኸውም ካህናት ‘በተነገረው ላይ መልስ አለን!” ሲሉና ምእመናን በአጽንኦት ሲቃወሙ አበራርጄ ካህናት የጠይቁት እንዲፈቀድላቸው ማድረጌ በቂ ማስረጃ ነበር። የቀድሞው አለቃ ግን ሰውን አሳሳሱት!! በተለይ መዘምራንና አንዳንድ እህቶችን። ይቅር ይበላቸው! ይበለን።

ይህን ክፍል ሳጠናቅቅ በልዩ ማሳሰቢያ ነው፦
 በመጀመሪያ የመጨረሻውን ስብሰባ የመራኸው ለእኩል ሰዓት
ቆሜ ስለሥርዐት! ስለ ስምምነት! ስለ ኅሊና፦ ስለእግዚአብሔር
ብዬ ስማጸን ፍጆታ የከለከልኸኝ ካህን አንዲት ግሩም እህታችንን
ለመጨረሻ ጊዜ ለመሸኘት ደቡብ ለንደን መካነ መቃብር
ስንጠብቅና አስከሬኑን የያዘ መኪና ሲቃረብ ከመኪና ልወርድ
ስከፍት ጉልበቴ ላይ ተደፍትህረጅም ለመሰለኝ ጊዜ የቆየኸው፦
ከኹለታችንም አንድ ትንፋሽ ሳይወጣ የተለያየነውን በተለያዩ ስሜቶች አስተውሳለሁ። ዋናው የኢትዮጵያዊነት መሠረተ ጨዋነት እንዳለህ ነው። ለዚህም አመሰግንሀለሁ።
የሚበልጠው ግን መሠረተ ክርስቲያንነትህ ስለኾነ
ኹለተኛው፡ አንድ በጣም ሰላምተኛና ጨዋ የቅዳሴ ጠበልም ታመጣልኝ የነበርህ ከአሥር ቀናት በፊት መውጫው ላይ ተገኛኝተን “ለምን ርስዎ ደግሞ መጡ?” ብለህ በጠቆረ ፊት ለምን አነጋገርኸኝ ስልህ የመለስክልኝን የመቆርቆር መልስ በምስጋና ተቀብያለሁ። ግን..
ሦስተኛ፡ አንዲት ወጣት መዘምር ችግራችንን በፍጥነት ለመፍታት
“ ከቅዳሴዎቹም አጭሩን፦ ትምሕርቱም ከተነበበው ወንጌል ባጭሩ፦ከሓውርያት አባቶቻችን የወረስነውንከቅዳሴ በኋላ ምእመናን አምጥተው ኹሉም የሚቋደሰውውን ከግሪክኛ “አጋጴ!” (ፍቅር) የተባለውን ካህናት ምእመናንን ትተው በመኮምኮም ብዙ ጊዜ የሚያጠፉትን ሲኾን አቆይተው አልያም ፈጠን ብለው ችግራችንን እንፍታው በማለቴ አንዳንድ ነገር ልታስምሪኝ መጥተሽ “ ኮማንደር-ኮማንደር የሚባሉት ርስዎነዎት? ያልሽኝና ትንሽ የተነጋገርነው
-እንዲሁም አሕዛብ ያላችሁን ሊሎችም የጋራ ችግራችን ግልጽ ያልኾነላችሁ እባካችሁ ሐሙስ የካቲት ፲፩ ቀን (20/03) እምሽቱ ፲፪ ሰዓት (6ፒ ኤም) ኢትዮጵያውያን ተራድኦ ማሕበር ተገናኝተን በአገርና በአንዲት ቤ/ክን ልጅነት እንወያይ። እናንተም የእኛን ዐቅዋምና ምክንያት ትረዱልናላችሁ፦ እኛም የናንትን ከዚያ በኋላ በየዐቅዋማችን በወንማችነት/እህትማማችነት/አባትና – እናት ልጅነት የሰደት ኑሮአችንን እንቀጥላለን። የምን ጠብ፦ የምን ኩርፊያ? ማንን ለማስደሰትና ለመጥቀም?!!?

ተንኮልና፦ ክፋት የተመላባቸው የጠላት መሣሪያዎች እንዳንገናኝ የማይሞክሩት የለም። እናንተ ግን በነፃ አገር በነፃነት የምትኖሩ እንደመኾናችሁ በዐእምሮአችሁ ለኅሊናችሁና ለሃይማኖታአችሁ ታዘዙና ወስኑ።እኔና የእኛን ዐቅዋም ሊያስረዱ የሚችሉ በሰዓቱ ተገኝተን እንጠብቃችኋለን።
አድራሻው 3A, Lithos Rd. (off Finchley Rd) Stations Fichley Rd & Finchley Rd & Busses 13, 82, 113, 187, 268
ፈቃዳችሁ ቢኾን በስልክ ቁትር 0207 794 4265 እንደምትገኙ ብታስታውቁን ይጠቅምውናል።

እሁድ የካቲት ፳፫ ቀን ጠ.ጉ. ተጠርቶ ካስተላለፋቸው ውሳኔዎች ውስጥ
- ጉዳያችን ባስቸኳይ ፍ/ቤት እንዲቀርብና
- ጉዳያችንን አለ አግባብ ሲያሽ ያከረመብንን ያገሪቱን የግብረ ሠናያት ድርጅት (ቻሪቲ ኮሚሽንን) በጥምር ተከሳሽነት እንዲቀርብ ተውስኖአል።

ይህ ማለት ወጪው የትዬ ኤለሌ መኾኑን አጥተነው አይደለም። ተስድደን ካለንበትም መጥተው ትግራይን እንገነጥላለን ባዮችና ግብረ-ዐበሮቻቸው በገንዘባችን የገዛነውን አናስነጥቅም በማለት ነው፤፡ ያገራችን አይበቃም!!?? ሊተባበረን ሊረዳን አብሮን ሊቆም ለሚፈልግ ወገን በ

NatWest Bank, Account name Save St. Mary of London—Sort Code: 60-19-26, Account no. 29112052
ለምትተባበሩን ኹሉ ልባዊ ምስጋናችንን እያስቀደምን ሂደታንን ለማሳወቅ ይመች ዘንድ ማድረጋችሁን በ commanderassefa@yahoo.co.uk
ብትገልጹልኝ አስታውቃችኋለu።

በክፍል ፪ ፦
— በጉዳያችን በገቡት ሊቃነ ጳጳሳት ኮራንባቸው
ወይስ?
— እንደሚሉት የሲኖዶስ ልዑካን ነበሩ ወይስ?
— ሲኖዶስ ዐውቆም ኾነ ሳያውቅ / ፈልጎም ኾነ
ተገድዶ ‘…እንዳያንሠራራ አድርገን
አሽመድምደነዋል..’ ብሎ ከሚፎክርበት ጋር የሚ..?
—ያገራችን ገዥዎች ባለንባት አገር መንግሥት ላይ
ተጽዕኖ እያረጉ ነው ወይስ?
የሚሉትን ዓበይት ጉዳዮች ስለምዳስስ እነምትከታተሉን ተስፋዬ ጽኑ ነው

ወስብሀት ለእግዚአብሔር!

Viewing all 1664 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>