Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » Opinion & Analysis
Viewing all 1664 articles
Browse latest View live

በመንግስት ሞኖፖሊ የተያዘው የኢትዩጵያ የባንክ አገልግሎት ዘርፍና የኢትዩጵያ ብር የገንዘብ የመግዛት አቅም ቅነሳ (devaluation) ክፍል አንድ – (ከሚሊዬን ዘ አማኑኤል)

$
0
0

ከሚሊዩን ዘ አማኑኤል

 

dd Banking sector and currency devaluation in Ethiopia በ1967 ዓም የIትዬጵያ ወታደራዊ መንግስት (ደርግ) በአዋጅ በሃገሪቱ ውስጥ የሚገኙ በግል ዘርፍየሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን በአዋጅ ቁጥር 20/1974 ወደ መንግስት ሃብትነት በማዘዋወርና በመውረስ ፋብ ሪካዎች፣ባንኮችና ኢንሹራንሰ ኩባንያዋችን፣የከተማ ትርፍ ቤቶችን፣ የገጠር መሬትን፣ ኢርሻዎችን ወዘተ በመንግስት ተወረሱ፡፡  የኢትዬጵያ ወታደራዊ መንግስት (ደርግ) አፍቃሪ ሶሻሊስት መንግሥት የፖለቲካና ኢኮኖሚ ፖሊሲዎች በማማከርና በማርቀቅ አገሪቷን ወደ ሶሻሊስት የእቅድ ኢኮኖሚ እንድትከተል አደረጉ፡፡–—[ሙሉውንለማንበብእዚህላይይጫኑ]—–


በመንግስት ሞኖፖሊ የተያዘው የኢትዩጵያ የባንክ አገልግሎት ዘርፍና የኢትዩጵያ ብር የገንዘብ የመግዛት አቅም ቅነሳ (devaluation) ክፍል ሁለት (ከሚሊዬን ዘ አማኑኤል)

$
0
0

dd4ኛ) የኢትዩጵያ ብሄራዊ ባንክ በባንክ አገልግሎት ዘርፍ የህዝቡን ታማኝነት ኢንዲያገኝና የፋይናንስ ዘርፉን ኢንዲያስተዳድርና ኢንዲቆጣጠር ተጨማሪ መመሪያና ደንብ ማውጣት ያስፈልጋል፡፡ የኢትዩጵያ ንግድ ባንክ በሃገሪቱ ውስጥ ስንት ቅርንጫፍ ባንኮች ኢንዳሉትና በክልላዊ መንግስቶች ውስጥ ያለው ስርጭት፣ማለትም የኢትዩጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ቁጥር ለሚሊዩን ህዝብ፣የአነስተኛና ጠቃቅን የብድርና ቁጠባ ኢንስቲቲውሽን (MFI) አገልግሎት ተጠቃሚ ህዝብ በመቶ፣የቁጠባና ብድር ኮዖፕሬቲቨ አገልግሎት ተጠቃሚ ህዝብ በመቶ (SACCO)፣በመደበኛ የባንክ አገልግሎት የተመቻቸላቸውና ተጠቃሚ ህዝብ በመቶ ቀጥሎ ባለው ሠንጠረዥ ይታያል፡፡ —[ሙሉውንለማንበብእዚህላይይጫኑ]—–

“ስለእኔ አታልቅሱ!” –ተመስገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)

$
0
0

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

“ዋይ ዋይ ከሚሉና ሙሾ ከሚያወጡ ሴቶችና ከሕዝቡ እጅግ ብዙዎች ተከተሉት፡፡ ኢየሱስ ግን ወደ እነርሱ ዘወር ብሎ እንዲህ አለ፡- እናንተ የኢየሩሳሌም ልጆች ለእኔስ አታልቅሱልኝ፤ ዳሩ ግን፡-

መካኖችና ያልወለዱ ማኀፀኖች፣ ያላጠቡ ጡቶችም ብፁአን ናቸው የሚሉበት ጊዜ እነሆ ይመጣልና ለራሳችሁና ለልጆቻችሁ አልቅሱ፡፡” (የሉቃስ ወንጌል ም. 23 ቁ. 27-30) ከቅዱስ መጽሐፉ ይህን የመሲሁ የመጨረሻ ምክር የመረጥኩት (ምንም እንኳ ረቢው የተናገረው ስለመለኮታዊው ትምህርት ቢሆንም) ዓለማዊው ፍች የኢትዮጵያችንን የወቅቱን መንፈስ ለመረዳት ከማስቻሉም በዘለለ፤ በየጊዜው እያየን፣ እየሰማን ያለነውን የፖለቲካ ተቃውሞው የጥምዝምዞሽ መንገድ በአርምሞ ለመመርመር መልካም ምሳሌ ይሆናል በሚል እሳቤም ነው፡፡

የሠላማዊ ትግሉ መቀልበሻ ስልቶች

እፍኝ በማይሞሉ ፋኖዎች ከአርባ ዓመታት በፊት “ደደቢት” በተሰኘ የሰሜን በርሃ የተመሰረተው ህወሓት ከተራዘመ የትግል ጉዙ በኋላ፤ ታጋይ ሕላዊ ዮሴፍ “እልፍ ሆነናል” እንዲል፤ ራሱን አጠናክሮ “እልፍ” በመሆን ሥልጣን ይዞ፣ የሀገሪቷን አንጡራ-ሀብት አመራሩ መምነሽነሺያው ካደረገ፣ እነሆ ሃያ ሶስት ዓመታት እንደዘበት ነጎዱ፡፡ ርግጥ ነው ይህች የዳንኪራ እና ፌሽታ ዘመን እውን ትሆን ዘንድ፣ የቡድኑ ዋና ዋና መሪዎችም ሆኑ መላው ታጋይ (የበረከቱ ተቋዳሽ ባይሆንም) በቃላት ሊገለፅ የማይችል የመከራ ዓመታትን በቆራጥነት ማሳለፋቸው የሚስተባበል ታሪክ አይደለም፡፡ ሥልጣን እጃቸው ከገባ በኋላም የአገር ጥቅም መገበርን ጨምሮ እየገደሉ፣ እያሰሩና እያሰደዱ… በሕዝብ ላይ ወደር የለሽ ጭካኔን በመፈፀም ዘላቂነቱን እንዲህ ስለማስረገጣቸውም ተወርቶ የተዘጋ አጀንዳ ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ይሁንና ከዕለት ዕለት እየመረረና እየከፋ የመጣው ይህ ኩነት፣ ምድሪቷ የአንድ እውነት መዝጊያና የአዲስ ዓመት ምዕራፍ መክፈቻ ላይ መድረሷን ስለማመላከቱ ለመመስከር ጠቢብነትን አይጠይቅም፤ የዘመኑ መንፈስ እያሰማን ያለው “ፋኖ ተሰማራ”ም የሶስተኛው አብዮት ደውል ስለመሆኑ ለመረዳት የቀደሙ ነብያቶችን ትንበያ መጠበቅ አያሻም፡፡
ገዥዎቻችን፣ መግደልና ማሰርን ሱፍ ለብሶ፣ ከረባት አስሮ፤ ጠዋት ወደ ቢሮ ተገብቶ፣ ማታ የሚወጣበት መደበኛ ሥራ ከማድረጋቸውም ባለፈ፣ የሥልጣን ግዛታቸውን እንዲህ ነቅተው (ታጥበውና ታጥነው) ባይጠብቁት ኖሮ፣ ለሃያ ሶስት ዓመት ቀርቶ፣ ለሃያ ሶስት ሰዓት እንኳን በቤተ-መንግስቱ መቆየት እንደማይችሉ አብጠርጥረው ያውቁታል፡፡ የዚህ ጽሑፍ ፍሬ-ሃሳብም በዚህ መልኩ የሥልጣን ዕድሜውን ገና የማቱሳላን ያህል ማራዘም የሚፈልገው ኢህአዴግ፣ ተቃዋሚ ድርጅቶች የሚያቀነቅኑት የሠላማዊ ትግል አቅጣጫን የሚቀይስበትን እና የሚወስንበትን የሴራ ፖለቲካ፣ ለውጥ ፈላጊው ኢትዮጵያዊ ነቅቶ እንዲያከሽፈው መቀስቀስ ነው፡፡

ዛሬ በርካቶች በቁጭት እንደሚብሰለሰሉት ኢህአዴግ በመንበሩ ላይ ከሁለት አስርታት በላይ ተደላድሎ የመቆየቱ ምስጢር በውስጣዊ ጥንካሬው፣ አሊያም ሲቪል ጀግኖች በመጥፋታቸው ሳቢያ አይደለም (ወላድ በድባብ ትሂድና፤ ሀገሪቱ የሚሞትላት ጀግና ትውልድ ከመፍጠር መክና አታውቅም)፡፡ የግንባሩ ዋነኛ የጥንካሬ ምንጭ የተቃዋሚውንም ወገን የቤት ሥራ ጠቅልሎ እየሰራ በመሆኑ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ወደኋላ ሄደን በአደረጃጀትም ሆነ በድጋፍ መሰረታቸው ‹‹የተሻሉ›› ሊባሉ የሚችሉ ተቀናቃኝ ፓርቲዎችን ሂደት ብንመረምር፣ መራራውን እውነታ እየጎመዘዘንም ቢሆን መጋታችን አያጠራጥርም፡፡ ለማሳያ ያህልም በአገዛዙ የማስቀየሻ እርምጃ ተጠልፈው ከከሸፉ ሕዝባዊ ንቅናቄዎች መካከል ጥቂቶቹን በአዲስ መስመር እንመልከት፡፡

ኦነግ

Et_olfየኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር፣ መለስ ዜናዊና ጓዶቹ ቆንጥረው ከሰጡት የሽግግር መንግስት ሥልጣኑ ተገፍቶ ከወጣ በኋላ ወደለመደው በርሃ በገባበት ወቅት፣ በአንፃራዊነት ቀድሞ መገንባት ከቻለው ጥንካሬ ባሻገር፣ በኦሮምኛ ተናጋሪው ማሕበረሰብ ዘንድ የሚሊዮኖችን ልብ ይበልጥ ማማለል ችሎ እንደነበረ የአደባባይ ሐቅ ነው፡፡ ወቅታዊውን የኃይል አሰላለፍ ጠንቅቆ የተረዳው “አባ መላ”ው ኢህአዴግም የጠብ-መንጃ ግብግቡ ከመጀመሩ አስቀድሞ፣ ከተማውን ለቆ ያልወጣውን የአመራር አባሉን ኢብሳ ጉተማን ወደ እስር ቤት ወረወረ፤ ይህንን ተከትሎም ኦነግ ከመቼውም ጊዜ በላይ በእልህና በቁጭት ተነሳስቶ አርሲና ሐረርን አስተባብሮ፣ ወለጋን በታንክ አቋርጦ፣ ባቱ ተራራን በመድፍ ጩኸት አንቀጥቅጦ፣ በባሌ ተሻግሮ ፊንፊኔ ላይ በድል ሊንጎማለል ነው ተብሎ ሲጠበቅ፤ በግልባጩ ዋና ፀሀፊው ሌንጮ ለታ እና የተወሰኑ መሪዎቹ በቦሌ በኩል በመመለስ “ወይ እኛንም አብራችሁ እሰሩን፤ አሊያም ጓደኛችንን መልሱልን?” በማለት ከመረጡት የኃይል ትግል ጋር የማይጣጣም ስልት ተግብረው አረፉት፤ በዚህም የልብ ልብ የተሰማው ኢህአዴግ፣ የድርጅቱን አባላትም ሆነ ኦሮምኛ ተናጋሪውን በጅምላ በ “ስመ-ኦነግ” እየወነጀለ ለአስከፊ እስር መዳረጉ፣ በክልሉ ላይ ከባድ ፍርሃት አነበረ፡፡ ይህ ፖለቲካዊ ስህተትም ለዛሬው ሽንፈቱ ዋነኛ ተጠቃሽ ሲሆን፤ የተቃውሞ ጎራ ትግሉንም ከሥርዓት ለውጥ ወደ እስረኛ ማስፈታት ያወረደ ቀዳሚ ኩነት ሆኖ በታሪክ ተከትቧል፡፡

መአሕድ

asrat weldeyesየፕ/ር አስራት ወልደየስ የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት (መአሕድ) ውድቀትም ከኦነግ ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ መአሕድ በምስረታው ማግስት ያገኘው መጠነ-ሰፊ የሕዝብ ድጋፍ፣ ህወሓት/ኢህአዴግ በ17 ዓመታት ከሰበሰበው ሁሉ ይልቅ እንደነበረ አይዘነጋም፡፡ ይህ አይነቱ ፈጣን ግስጋሴም ሊያስከትለው የሚችለውን የቁጣ ናዳ አስቀድሞ የተረዳው ‹‹ብልጣ-ብልጡ›› ኢህአዴግ፣ ሊቀ-መንበሩን ጉምቱ የሕክምና ሊቅ ጨምሮ ጥቂት የአመራር አባላቱን እስር ቤት ወረወረ፡፡ ከዚያማ ድርጅቱ ‹‹እታገልለታለሁ›› የሚለውን የፖለቲካ ሥልጣን የመቆጣጠር ዓላማውን ‹‹መሪዎቻችን ይፈቱ!›› ወደሚል አኮስሶ ባለበት ሲረግጥና ሲዳክር ለ13 ዓመታት ከቆየ በኋላ፣ በስተመጨረሻ ህላዊነቱ አክትሞ ወደ ሕብረ-ብሔር (መኢአድ) ድርጅትነት መሸጋገሩ ታወጀ፡፡ ክስተቱም አብዮታዊው ግንባሩ የተቃውሞ ጎራውን እንቅስቃሴ ወደፈለገው አቅጣጫ መዘወሩን በሚገባ እንደተካነበት ያስረገጠ ሆኖ አልፏል፡፡

ቅንጅት

Birtukan-Midekssa-_Tadias-Magazine-coverዛሬ ዛሬ እንደ ንግስት ሳባ ዘመን የሩቅ ጊዜ ታሪክ ያህል ይሰማኝ የጀመረው ምርጫ 97ም ሌላኛው የነገረ-አውዱ አስረጂ ነው፡፡ በጥቂት ወራት ውስጥ ከጫፍ ጫፍ ሀገራዊ ንቅናቄ መፍጠር የቻለው ግዙፉ ቅንጅት በአብዛኞቹ የምርጫ ጣቢያዎች በይበልጥ ደግሞ በገጠር አካባቢዎች አሸናፊ መሆኑ በተለያዩ አጣሪ አካላት በመረጋገጡ፤ የኢህአዴግን‹‹መንግስት ለመመስረት የሚያስችለኝ ድምፅ አግኝቻለሁ›› ጨዋታን ከውስጥም ከውጭም አምኖ የተቀበለ አንድም እንኳ አልነበረም፡፡ በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ይህንንዓይን ያወጣ ስርቆት በሠላማዊ መንገድ ለመቃወም በሞከሩ ዜጎች ላይ በተወሰደው ርህራሄ አልባ የኃይል እርምጃ በርካታ ንፁሀን ለህልፈት እና ለአካል ጉዳት ሲዳረጉ፣ በተወሰኑየክልል ከተሞች ደግሞ ከፍተኛ ሕዝባዊ ማጉረምረም ተፈጥሮ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ ግና፣ ‹‹ብልሆቹ›› የኢህአዴግ ኤጲስ ቆጶሳት በተካኑት ስልት የቅንጅቱን መሪዎች ከያሉበትሰብስበው እስር ቤት ከተቱ፤ ትግሉም ከተነሳበት ‹‹የገጠሩ ወገኖቻችን ድምፅ ይመለስ!›› ወደ ‹‹መሪዎቻችን ይፈቱ!›› ቀኝ ኋላ ዞሮ፣ የሥርዓቱ ዕድሜ እንዲቀጥል ስለመፍቀዱ የእኔ ትውልድ የአይን ምስክር መሆኑ ርግጥ ነው፡፡

ሕዝበ-ሙስሊሙ

Ethiopian_muslims-260x190ለሶስት ዓመት ተመንፈቅ (ከ‹‹እፎይታ ጊዜ››ው በቀር) ካለማቋረጥ በተቀጣጠለው የሙስሊሙ ኃይማኖታዊ ነፃነትን የማስከበር ትግልም፣ የንቅናቄው አስተባባሪዎች ‹ቃሊቲ የታጎሩትን መሪዎች የማስፈታት ዓላማ በአራተኛነት የተያዘ ነው› ቢሉም (‹‹አህባሽን በግዴታ ማጥመቅ ይቁም››፣ ‹‹መጅሊሱ ወደ ሕዝቡ ይመለስ›› እና ‹‹ነፃ ሕዝባዊ ምርጫ ይካሄድ›› የሚሉት ሶስቱ መሪ ጥያቄዎች የተቃውሞ መነሾ እንደሆኑ ልብ ይሏል)፤ የሕዝበ-ሙስሊሙ በተለይም የቅርብ ጊዜዎቹ የመስጂዶቹ እምቢ-ባይነቶች፣ ሥርዓቱ ለማደነቃቀፍ (ዓላማውን ለማስቀየስ) ባዘጋጀው የ‹‹ይፈቱ›› ማዕቀፍ ስር የተገደበ የመምሰል አዝማሚያው ነው በዚህ አውድ እንድጠቅሰው ያስገደደኝ፡፡ በርግጥ የሁለት አስርታቱን የተቃውሞ ልምድ በቅጡ የመረመሩ የሚመስሉት የ‹‹ድምፃችን ይሰማ›› ወጣቶች፣ በዚህ የተለመደ የትግል ቅልበሳ ላለመጠለፍ የሚያደርጉት ብርቱ ሙከራ እንዳለ ብገነዘብም፣ ከቀደመው ‹‹ጥቁር ሽብር›› ወዲህ በቀጣይ በሚኖሩት የትግል ወቅቶች ዋነኛ የትግል ጥያቄያቸውን ነፃነታቸውን በማስከበር ማዕቀፍ ስር እንደሚያደራጁት አምናለሁ፡፡

ማልቀስስ ለማን?

eth cryበ1983ቱ የመንግስት ለውጥ ዓለም አቀፋዊው አውድ፣ ለሽፍቶቹ ስብስብ እርግማንም በረከትም ይዞ ነበር፡፡ እርግማኑ፣ በቀደመ-ፖለቲካዊ ዝማሜያቸው ዝግ ሶሻሊስት ሥርዓት መመስረት አለመቻላቸው ሲሆን፤ በረከቱ ደግሞ በረዥሙ የእርስ በእርስ ጦርነት ክፉኛ የተመታችውን አገር በተለይም ተቋሞቿን ለመገንባት ከሚያስፈልገው ጊዜ አኳያ የምዕራባውያኑን ‹‹ዕድል እንስጣቸው›› የድጋፍ ልብ ማግኘታቸው ነው፡፡ በእነ ሳሙኤል ሀንቲንግተን ‹‹መድበለ-ፓርቲ ሥርዓትን እርሱት፤ አውራ ፓርቲነት ያዋጣችኋል›› ምክረ- ሐሳብ አማካኝነት የወቅቱ ምዕራባውያን አለቆቻቸውን መንፈስ መረዳታቸውን ወደኋላ ስንገነዘብ፤ ቢያንስ እስከ 97 ድህረ-ምርጫ ውጥንቅጥ ድረስ በተጓዙበት የአምባ-ገነንነት መንገድ በጥብቅ አለመወገዛቸውን እንረዳለን፡፡ በአናቱም በህወሓትና መሰል ነፍጥ አንጋቢ የድህረ-ቀዝቃዛው ጦርነት ቡድኖች ላይ ተስፋ የነበራቸው ዓለም አቀፍ ተቋማት እና ምሁራንም ዘግይተውም ቢሆን ቡድኖቹ ወደ ቋሚ ሽፍትነት መቀየራቸውን ከመመልከት አልዳኑም፡፡ የዚህ አይነት ስብስብ ቋሚ መለዮ፣ በመሰረተ ልማት ግንባታዎች ላይ ሙሉ ሀገራዊ ሀብት ማፍሰስ ነው፤ መግፍኤውም ግልፅ ነው፤ የሕብረተሰቡ የአምራችነት ማሕበረ-ኢኮኖሚያዊ አቅም ሲጎለብት፣ እነርሱም የሚያግበሰብሱት ሀብት እየሰፋና እየበዛ እንዲሄድ የማስቻሉ ሀቅ ነው፤ እንደ ህወሓት ያሉ የነፃ-አውጪነት የኋላ ታሪክ ያላቸው ገዢ ቡድኖች፣ በምርጫ ፖለቲካ የማይነቀነቁባቸው ምክንያቶችም ከዚሁ ጋር ይተሳሰራል፤ ከሰላማዊ ሕዝባዊ ዓመፅ ውጪ ይህን ነውረኛ ቡድን ማስቆም እንደማይቻል በ‹‹ሕዳሴ አብዮት›› ርዕሰ-ጉዳይ ለመከራከር የሞከርኩትም ለዚሁ ነው፡፡ እንግዲህ ከእስክንድር ነጋ እስከ ርዕዮት አለሙ፤ ከውብሸት ታዬ እስከ የሱፍ ጌታቸው፤ ከአንዱአለም አራጌ እስከ በቀለ ገርባ፤ ከጦማሪያኑ እስከ እነ ሐብታሙ አያሌው… ድረስ ዘርዝረን የማንጨርሳቸው የእልፍ አእላፍ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያውያን መታሰር አሳዛኝ ቢሆንም፤ ለእነርሱም ሆነ ለሀገር የሚበጀው ‹‹ታጋይ እንጂ ትግል አይሞትም!›› የሚለውን የጊዜውን አስገዳጅ ሕዝባዊ ጥሪ በመቀበል አደባባዩን በቁጣ ማጥለቅለቅ ብቻ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ዛሬ እያየነው እንዳለው የግፉአኑን መፈክር አንግቦ መነሳትን ገሸሽ አድርጎ፣ የ‹‹ይፈቱ›› ጥያቄ የትግሉን መንፈስ ይመራው ዘንድ መፍቀድ ሂደቱን ለሥርዓቱ ሴራ አሳልፎ እንደመስጠት የሚቆጠር ይመስለኛል፡፡

መግቢያዬ ላይ የጠቀስኩት የመምህሩ ቃል የሚነግረንም ለእነሱ ከማልቀስ ይልቅ፣ የአምባ-ገነኑን ሥርዓት ቀንበር ተሸክመን በአሳረ-ፍዳ ኑሮአችንን ስለምንገፋው ስለራሳችን ብናለቅስ የተሻለ መሆኑን ነው፡፡ ከዚህ ጎን ለጎንም አብዝተን ነፃነታቸውን የምንሻላቸው ጀግኖቻችን እንደምኞታችን ቢፈቱና መፃኢ ዕድላቸው ምን ሊሆን እንደሚችል ራሳችንን ብንጠይቅ፣ የምንፋጠጠው ‹ተመልሰው በኢህአዴግ የብረት ጫማ ስር ለጥ-ሰጥ ብሎ ማደር› ከሚል እውነታ ጋር ብቻ ነው፡፡የተለመደውን ‹‹የይቅርታ ቃጭል›› አጥልቀው፣ በተሰበረ መንፈስ ከትግሉ ርቀው አንደበታቸውን ሸብበው አሊያም ከሀገር ወጥተው ቀሪውን ህይወታቸውን በስደት እንዲያሳልፉ ከማድረግ ያለፈ የምንፈጥርላቸው ወይም የምናመቻችላቸው ምንም ነገር አለመኖሩ ርግጥ ነውና፡፡ ያውም ብርቱካን ሜደቅሳን ለቅቆ፤ ርእዮት ዓለሙን የሚያስርበትን የቆየ የፖለቲካ ጨዋታውን ሳንዘነጋ፡፡ ይህም ነው ሕዝብን የማዳመጥ አንዳችም ልምድ ለሌለው ሥርዓት ‹‹ይፈቱ!››፣ ‹‹ይለቀቁ!›› እያልን ከመጮኽ በመቆጠብ፣ ታሳሪዎቹ ስለተዋደቁባቸው የነፃነት እሴቶች መተግበር መታገልን ግድ ያደርገው፡፡

በጥቅሉ በመከራው ዳገት ላይ ያሉት ወገኖቻችን የገጠማቸውን ሁነት ያስነሳው፣ ማናችንም በነፃነትና በእኩልነት ልንኖርባት የምትገባዋን አገር የመናፈቅ እንደሆነ ከተስማማን ዘንዳ፣ በየእስር እርምጃው የተፈጠሩትን ክፍተቶች እየደፈንን፣ የነፃነቱን ቀን ለማቅረብ መታተር የወቅቱ አስገዳጅ ጉዳይ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ በቀድሞው የቅንጅት አመራሮች የገፍ እስር ማግስት፣ የከተሞቹን ንቅናቄዎች ከ‹‹ይፈቱልን›› ይልቅ፣ ‹‹ድምፃችን ይመለስልን!›› በሚለው መሠረታዊ ጥያቄ አጥብቀን ይዘን ትግላችንን ብናራዝመው ኖሮ፣ ፖለቲካዊ ለውጦችን መጨበጥ እንችል እንደነበር ማናችንም ብንሆን የምንጠራጠር አይመስለኝም፡፡ ከዚህ አኳያም የሚያስማማን ዋነኛ ጭብጥ፣ ቢያንስ የ2002ቱ ምርጫ በተካሄደበት አስቂኝ ድራማ ልክ ተከናውኖ እና ተቀልዶብን የማለፉ ዕድል እጅጉን ያነሰ የመሆኑ ጉዳይ ነበር፡፡

ባለፉት ጥቂት ወራት ውስጥ ያየናቸው የጦማሪያኑና የሶስቱ ፓርቲዎች ወጣት አመራሮች እስር፣ በተለመደው የ‹‹ይፈቱ›› ደካማ የትግል ስልት የመሄድ ዳርዳርታውን ገርተን፣ ከአደባባዩ መራቃቸውን ተከትሎ እየተፈጠረ ያለ የሚመስለውን (ከማሕበራዊ ድረ-ገፆች እስከ የዕለት ተዕለት የፓርቲዎቹ እንቅስቃሴ ድረስ) ክፍተት መሻገሩ፣ የተሻለ ብቻም ሳይሆን ገዢዎቻችን እንድንሰምጥበት ከሚሹት የሽንፈት ማጥ ውስጥ ከመነከርም የሚገታ አማራጭ ነው፡፡

እነሆም ለማንስ ማልቀስ ይገባል? የሚለውን ጥያቄ መመለስ የሚያስፈልገን እንግዲህ በዚህ ከባድ ወቅት ላይ ነው፡፡ …እንደየተነሱበት አውድ ለሚያምኑባቸው ክቡድ ዕሴቶች ዘብጥያ ለተጣሉት ዜጎች መብሰልሰልን በመምረጥ ከጎናቸው መሰለፍን ላንገራገርነው ለኛ ማዘን የበለጠ የተገባ ነውና፣ እነርሱ ድርሻቸውን ስለመወጣታቸው እያመሰገንን፣ ፍትሃዊ አቋሞቻቸውን በገዘፈ ጉልበት ወደፊት መውሰድ ብቸኛው ምርጫችን መሆን ይኖርበታል፡፡ የ‹‹ሕዳሴው አብዮት›› ተግባሮትም አስፈላጊው ሥነ-ልቦና ይኸው ነው ብዬ አምናለሁ፡፡
ድል ለግፉአን ኢትዮጵያውያን

የመለስ “ትሩፋቶች”–መጽሃፍ ቅኝት (ከጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋ)

$
0
0

meles book
ደራሲ፣ ኤርምያስ ለገሰ
ብዛት፣ 406 ገጾች
አሳታሚ፣ ነጻነት አሳታሚ ድርጅት

እንደ መንደርደርያ
በስፋት ሲወራለት የነበረውን ይህን መጽሃፍ ሙኒክ-ጀርመን ላይ ገዝቼ ለማንበብ እያፈላለግኩ ሳለሁ፤ አንድ ወዳጄ ይዞት አየሁ። የደበዘዘ የመለስ ፎቶ ያለበትን ይህንን መጽሃፍ የኦስሎው አበበ እጅ ላይ ነበር። ገና ሰላምታ ሳንለዋወጥ ነበር መጽሃፉን ከእጁ ላይ የነጠቅኩት። ታማኝ በየነም እዚያው አብሮን ስለነበር አስተያየቱን ጣል አደረገ። “መነበብ ያለበት መጽሃፍ” እንደሆነ አበክሮ ነገረኝ። ታማኝ ኢትዮጵያን የሚመለከቱ መጻህፍት በሙሉ እንደማያመልጡት አውቃለሁ። በዚህ አዲስ መጽሃፍ ላይ አንዳች አዲስ ነገር እንደሚኖር ከንግግሩ ለመረዳት አያዳግትም።
የመጽሃፉ መታተም ወሬ እንደተሰማ በደራሲው በአቶ ኤርምያስ ለገሰ ላይ የድጋፍና የተቀውሞ ድምጾች ከሁለት ጫፎች ይሰሙ እንደነበር አስተውያለሁ። ሁለቱም ጫፎች ለክርክራቸው የየራሳቸው መከራከርያ ነጥቦች ቢኖራቸውም መደምደሚያቸው አንዱ-ካንዱ ሚዛን የሚደፉ ሆነው አላገኘኋቸሁም። ማየት የሚገባን የጫነውን ሳይሆን ጭነቱን ነው እንዲሉ፣ መልዕክተኛውን ሳይሆን ይልቁንም መልዕክቱን አንብቦ የራስ ፍርድ መስጠቱ የሚመረጥ ይሆናል። ማንበብ ከጉዳቱ ጥቅሙ ነው የሚያመዝን። መረጃ ሁሉ አይናቅም። የብዙዎቻችን ችግር ከታማኞቻቸን የምናገኘውን መረጃ ብቻ ይዘን በዚያ ቁንጽል መረጃ ተንተርሰን ውሳኔ ለመስጠት መሞከራችን ይመስለኛል። ያ ስውዬ እንዳለው ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል። የኮ/ል መንግስቱን፣ የሻምበል ፍቅረስላሴን እንዲሁም የበረከት ስማዖንን መጽሃፍትስ ገዝተን አንብበን የለ? እንደዚህ አይነቶቹ መጻህፍቶች ሙሉ ሰው እንኳ ባያደርጉን ሚዛናዊ እንድንሆን ይረዱናል።
***
መጽሃፉ ሲገለጥ
በንዑስ ርዕስ “ባለቤት አልባ ከተማ” ተብሎ የተሰየመውን “የመለስ ‘ትሮፋቶች’” እነሆ አነበብኩት..
ደራሲው፣ ኤርምያስ ለገሰ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሂሳብ ትምህርት የባችለር ዲግሪውን እንደያዘ መከላከያ ሚ/ር ውስጥ ተቀጥሮ ዝዋይ በሚገኘው የመከላከያ ኮሌጅ ከፍተኛ መኮንኖችን ለማሰልጠን ተጓዘ። በካምፑ ያሉ አብዛኞቹ መኮንኖች ከአምስትኛ ክፍል ያልዘለሉ እንደሆኑም በገጽ 209 ያስነብበናል። ወጣቱ ካድሬ እነዚያን መሃይም መኮንኖች የተፈጥሮ ሳይንስ ሊያስተምራቸው እንዳልሄደ ግልጽ ነው። ከጳጳሱ በላይ ካቶሊክ… እንዲሉ ከበረሃ የመጡ ነባር ታጋዮችን የድል አጥቢያው ካድሬ የራሳቸውን ርዕዮተ-አለም ሊለቅባቸው መሄዱ ደግሞ የበለጠ ግርታ ይፈጥራል።
ደራሲው የአብዮታዊ ዲሞክራሲን ወንጌል የተቀበለው የአራት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ነበር። እዚያ በተማሪ ስም ተመድቦ የሚሰራ ሰላይ ካድሬ ይህንን የቅጥፈት ፍልስፍና ሰብኮ እንዳጠመቀው በገጽ 192 ላይ አስፍሯል። በአራት ኪሎ ቆይታው ከሂሳብ ትምህርቱ ጎን ለጎን ቀዩዋን መጽሃፍ ሲበላት ከርሞ ኖሮ፤ የህወሃት ሃዋርያ ሆኖ እነሆ ወንጌሉን ሊሰብክ ተሰማርቷል።
ይህንን ለማድረግ ታድያ አብዮታዊ ዲሞክራሲን በስሱ ሳይሆን እስከ አንገቱ ድረስ መጋት ይኖርበታል። የድርጅቱ አይነተኛ ርእዮተ-አለም የሆነውን የባንቱስታን የክልል አገዛዝ እና የዘር ፖለቲካን አቡክቶ ማብሰል ይጠበቅበታል። ከፍ ሲል ደግሞ ኢህአዴግኛ ቋንቋ መናገር የግድ ይሆንበታል – መስፈርቱን ለሟሟላት። በገጽ 327 ላይ አብዮታዊ ዲሞክራሲን ቀጥ አድርጎ ሰላቆመው ምሰሶ ሲገልጽ፤ “በራስ ያላመኑበትን ነገር መናገር – ለህሊና የሚከብድ” ብሎታል። አለፍ በሎም እንደ ሂትለሩ ጎብልስ ውሸትን እየደጋገሙ ህዝብን ለማሳመን መሞከር (ገጽ 389) እንደሆነ ይነግረናል።
ወትሮውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ወደ ኢህአዴግ ጎራ የሚገባ ተማሪ በማህበራዊ ኑሮው ላይ ምን ያህል አደጋ እንደሚጋረጥበት በውስጡ ያለፍነው የምናውቀው ጉዳይ ነው። አንድ ተማሪ ኢህአዴግ አባል ከሆነ መጀመርያ ከህብረተሰቡ ጋር ይራራቃል። ከዚያ ከመርህ ጋር ይጋጫል። በመጨረሻም ከራሱ ጋር ይጣላል።
ኤርምያስ ያውም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሆኖ ለኢህአዴግ በካድሬነት የመጠመቁ ስሜት ከምን ሊመጣ እንደቻለ ለማወቅ ያጓጓል። በመጽሃፉ ውስጥ ይህቺን ጉዳይ እንደዋዛ ሳይጠቅሳት አልፏል። በአብዮታዊ ዲሞክራሲ፣ አንድ እና አንድ ሶስት ነው የሚሆነው። እንደሁኔታው አራትም አምስትም ሊሆን ይችላል።
ወጣቱ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ካድሬ መሆን ደግሞ በሂሳብ ትምህርት አንድ ሲደመር አንድ ሁለት ነው የሚለውን ስሌት ለድርድር ማቅረብ ግድ ይለዋል። እዚያ መርህ እና እውነት የሚባል ነገር አይሰራም። ይህንን ደግሞ ኤርምያስ ራሱ በመጽሃፉ ውስጥ ባነሳቸው ርዕሶች ሁሉ ያረጋግጥልናል። “ከኢህአዴግ ጋር ያቆራረጠኝ ከራሴም ጋር ቅራኔ ውስጥ የዘፈቀኝ ሕግ ይህ ነበር።” (ገጽ 1) ሲል “እውነት የተደጋገመ ኩሸት ነው” የሚለውን የድርጅቱን የመጀመርያ ህግ ያነሳል። ህጉን በትክክል ገልጾታል።
ልዩነቱ ኤርምያስ የባነነው ከ12 አዓመታት በኋላ መሆኑ ነው። በነዚያ አመታት ከተራ ካድሬነት አልፎ ልዩ-ልዩ ሃላፊነትን ተሸክሞ በሰባራው ሃዲድ ረጅም ተጉዟል። ከአዲስ አበባ የምክር ቤት አባልነት እስከ መንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዴኤታ የሚደርስ የስልጣን ተሸክሟል። በመጽሃፉ የዘረዘራቸው ዘግናኝ ዝርፊያዎች ሲካሄዱ አይንና ጆሮውን ከልሎት የነበረው ይህ ሸክም ይሆን? በገጽ 303 ላይ “እኔ ኢሕአዴግ ነበርኩ። ያውም እውነቱ እስኪገለጥልኝ በእምነት የምተጋ ካድሬ። ….10ሺ የሚጠጉ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በአብዮታዊ ዲሞክራሲ እያጠመቅኩ ኢሕአዴግ አርገያለሁ።” ብሎናላ!
***
መጽሃፉ በስምንት ክፍሎች ተመድቦ በሃያ አምስት ምዕራፎች ተሸንሽኗል። በዋናነት ግን በሶስት ጉዳዮች ላይ እያጠነጠነ በዚህ ዙርያ ተዛማች የሆኑ መረጃዎችን ያስነብበናል። በአንዲት ጀምበር ቢሊየነር የሚያደርገው የባለቤት አልባዋ አዲስ አበባ የመሬት ዘረፋና የምርጫ 92/97/2000 እንድምታዎችን በግንባር ቀደምትነት ይተነትናል። እንዲሁም የባድመ ጦርነት አስከትሎ ያመጣቸውን መዘዞችን በስሱ ለመዳሰስ ሞክሯል።
የጨለማውን አሊ አብዶ ዘመን በግርድፉ ይዳስሳል። የካዛንችሱ ስውር መንግስት አሊ አብዶን በርቀት እንዴት ይነዳው እንደነበር ያወሳል። የበለጠ ትኩረቱ ግን በአርከበ እቁባይ አስተዳድር ችግሮች ላይ ነው። በነዚህ ዘመናት ዘረፋው ግዙፍ፣ ችግሮቹም ውስብስብ ነበሩ። በእውነት ለመናገር በመጽሃፉ የተነሱት በደሎች እና ዘረፋዎች የአደባባይ ምስጢሮች ናቸው። አብዛኞቹ ከግሉ መገናኛ ብዙሃን የተደበቁ አልነበሩም። ይህ መጽሃፍ ዝርፍያዎቹ መቼ፣ እንዴት እና በማን ተፈጸሙ ለሚሉት ጥያቄዎች ምላሽ እየሰጠ የቀድሞዎቹን መረጃዎች የተሟላ ያደርጋቸዋል። ጉዳዮቹን በስፋት እና በጥልቀት ለማወቅ የሚያስችል ግንዛቤም ይሰጠናል። ከንቲባ አሊ አብዶ ዘመን ሁላቱን ታላላቅ እምነቶች ለማጋጨት እሳቤ ሆኖ፣ በታቦት ማረፍያዎች ሳይቀር መስጊድ እንዲሰሩበት ይደረግ እንደነበር ቀደም ብሎ ተዘግቧል። አርከበ እቁባይ ከንቲባ ሆኖ ሲሾም የካቢኔ አባለቱን ከትግራይ ጭኖ ባመጠቸው መሃይማን ካድሬዎች መሙላቱም አዲስ መረጃ አይደለም። የጠገበው ጅብ ሲሄድ የራበው መተካቱን የማያውቅ የለም። የኤርምያስ መጽሃፍ ግን መረጃውን በማስረጃ እየደገፈ ይተርክልናል። ለተራው አንባቢ ትርጉም ባይሰጥም፤ የበርካታ ሹማምንት ስሞችን በመጽሃፉ ተደርድረው እናገኛለን።
የመለስ “ትሮፋቶች” ደረቅ የፖለቲካ ትንተና ላይ የሚያተኩር ያለመሆኑ መጽሃፉን ያለትንፋሽ እንዲነበብ ያደርገዋል። በአንድ ጎኑ ጥርስ የማያስከድኑ፤ በሌላ በኩል ደግሞ አንጀት የሚያቃጥሉ እውነታዎችን ይዟል።

ተወርቶ የማያልቀው የአርከበ እቁባይ ታሪክ ውስጥ የካድሬ ተስፋ ብርሃን ጉዳይ ሰፍሯል። ተስፋ ብርሃን መስማት የተሳነው ህመምተኛ ነው። አርከበ ከመቀሌ አስጭኖ ያስመጣው ካድሬ። ሲቪል ሰርቪሱን፤ ትምህርት ቢሮን እና አጠቃላይ አቅም ግንባታውን እንዲመራ ሃላፊነት ተሰጥቶታል። ገብረተንሳይ የሚባለው ሌላኛው ካድሬ በአንድ ግምገማ ላይ “አንተ ደንቆሮ ነህ። ካንተ ጋር እንዴት እንደምሰራ አይገባኝም?” ይለዋል። መስማት የተሳነው ተስፋብርሃን መልሶ “ገብረተንሳይ ልክ ነው የመምህራን ስልጠና መስጠት አለብን።” አለው (የመለስ “ትሮፋቶች” ገጽ 132)። ደራሲው በየግምገማዎቹ ይከሰቱ የነበሩ እንደነዚህ አይነት ጥርስ የማያስከድኑ ትውስታዎችን በመጽሃፉ ውስጥ አስፍሯቸዋል። በተላይ የካድሬ ጨነቀ ታሪክ (ገጽ 150-155) ‘ጧ ‘ አድርጎ ከማሳቁ ባሻገር ስርዓቱ በሕዝብ ላይ ምን ያህል እየቀለደ እንደሆነ ያሳየናል።
በገጽ 224-225 የሰፈረው የአቦይ ስብሃት ጉዳይም ጥርስ በጣም ያስቃል።
ጸሃፊው በአብዛኛው ርእሶቹ እንደመነሻ የሚያደርገው የበረከት ስምዖንን “የሁለት ምርጫዎች ወግ” እንደሰበዝ የሚመዘዙ ስንኞች በመጠቃቀስ ነው። በአንባቢያን ዘንድ ብዝም ትኩረት ያልሳበው የበረከትን መጽሃፍ በውሽት የታጨቁ ድርሰቶች አድርጎ ለማቅረብ ሞክሯል። በከፊል በማስረጃ እያስደገፈ ነው ድርሰቱን ያጣጣለው። የበረከትን “የሁለት ምርጫዎች ወግ” ያላነበበ ካለ ዋና ዋናዎቹን የበረከት መርዘኛ መልዕክቶች ከነማፍረሻቸው በዚህ መጽሃፍ ውስጥ ያገኛቸዋል። ኤርምያስ አብዮታዊ ዲሞክራሲን በበረሃ ከተጠመቁት የህወሃት ካድሬዎች ጋር እኩል ቀርቦ ከማእዱ ሊቋደስ ከቶውን እንደማይችል እርግጥ ነው። በዚያ ላይ ከቅዱሰ-ቅዱሳኑ ለመግባት የዘር መስፈርቱን አያሟላም። እንደማንኛውም የድል አጥብያ ካድሬ በታማኝነቱ መጠን እነ በረከት እውቀቱን ተጠቅመውባታል። በሃገሪቷ ወሳኝ ጉዳዮችና ውሳኔዎች ላይ የመጀመርያ መረጃ ሊኖረው እንደማይችል ግልጽ ነው። ከመጽሃፉ እንዳየነው አብዛኞቹን መከራከርያ ነጥቦቹ የሚያተኩሩት ከየግምገማዎቹ ባገኛቸው መረጃዎች ላይ ነው። በምኒስትር ዴኤታ ማዕረግ ላይ ያለ ሰው ማወቅ የሚገባውን እንኳን አያውቅም። ለምሳሌ በገጽ 376 ላይ በኢትዮ-ኤርትራና ኢትዮ-ሶማልያ ጦርነት ክ120ሺህ የሃገራችን ወጣቶች ማለቃቸውን በይፋ የሰማው በአንድ ግምገማ ላይ ከወ/ሮ አዜብ መሆኑን ይናገራል።
በመጽሃፉ አልፎ አልፎ በቅንፍ የቀረቡ መረጃዎች ውስጥ፤ የሃይሌ ገ/ስላሴ አድርባይነት፣ የቴዲ አፍሮ በአዜብ ጥርስ ውስጥ መግባት እና ጉዳዩን ይዞ የነበረው ካድሬ ዳኛ ልዑል፣ የፕ/ር መረራና ዶ/ር በየነ ጉዳይ የሚያስደምሙ ናቸው። “ጉራጌ መራሽ አብዮት” ያሉትን ነቅናቄ ለመቀልበስ በተከወነው ሴራ (ገጽ 232-234) ታታሪውን የጉራጌ ህዝብ ዛሬ ከጫወታ ውጭ እንዳደረገው ይገልጻል።
የአያት መኖርያ ቤት ድርጅትን (ሪል ስቴት) ሙስና ለመታደግ፤ እነ በረከት ስምዖን የግሉን ፕሬስ ሳይቀር በማሳተፍ የሰሩት ድራማ (ገጽ 326) ለአንባቢው አዲስ ነገር ነው። የዚህ መጽሃፍ ደራሲ፣ ኤርምያስ ለገሰ በዚህ “አሳዛኝ” በሚለው ጥፋት ላይ መሳተፉን በጸጸት ጽፎታል። ያንን ሁሉ አመት ከህወሃት ጋር በእምነትና በትጋት ሲሰራ እንደነበር ቢነግረንም ከዚህ ውጭ የተናዘዘው ሃጥያት ግን የለም።
በምኒስትር ዴኤታ ማዕረግ ላይ ካለ ሰው የምንጠብቀው ከዚህ ላቅ ያለ ምስጢር ነበር። መጽሃፉ በሰብአዊ መብት ጥሰት ላይ ብዙ ትኩረት አልሰጠም። ሌላው ቢቀር የግል ፕሬሱ ይዘግባቸው የነበረው በካዛንችዙ ስውር መንግስት ስር የሚሰሙ ሰቆቃዎች፣ ስቃይና ግድያዎች ጸሃፊው እንደዋዛ አልፏቸዋል። እንደ እንጉዳይ ተክል በአንድ ሌሊት ብቅ ያለው የአባይ ጉዳይ ላይ ኤርምያስ አንድ ነገር ይላል የሚል ግምትም ነበረን። ይህንንም በዝምታ አልፎታል። ምናልባት የምስጢሩ ተቋዳሽ አይሆን ይሆናል። ምናልባትም በቀጣዩ ማስታወሻው ይመለስበት ይሆን ይሆናል። ስለ ሃይሌ ገብረስላሴ አድርባይነት በሚገልጸው ክፍል (ገጽ 285) ስለ አትሌቱ፤ “እንቁ እግር፣ አድርባይ ጭንቅላት” የሚል ርእስ በሚቀጥለው ማስታወሻ እመለስበታለሁ ብሎናል። ይህም ደራሲው ቀጣይ ስራ እንዳለው ያመላክተናል።
መጽሃፉ በርካታ የፊደል ግድፈቶች ይታዩበታል። አንዳንዶቹ ግድፈቶች የመልዕክቱን ትርጉሙ ሁሉ ቀይረውታል። ከዚያም አልፎ፤ በአማርኛ ተስተካካይ ፍቺ ያላቸው እንደ ዲሞቢላይዜሽን፣ ኔትወርክ፣ ኦረንቴሽን፣… የመሳሰሉ የባዕድ ቃላት በአማርኛ ተዛማጅ ትርጉም አልያም በቅንፍ ቢቀመጡ ይመረጥ ነበር።

ላቂያ! (ሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 8.08.2014 (ሲዊዘርላንድ -ዙሪክ)

ይህቺ ተመስጥራ የኖረች እርዕስ በዬትኛውም መጸሐፌ ላይ የለችም። በዬትኛውም ወጋወጎቼም ላይ ታዳሚ ሆና አታውቅም። ቁጥብ ነበረች። ዛሬ ግን ከማህደረ የህሊና ሰሌዳ ብቅ ብላ እነሆ ለአደባባይ ትውል ዘንድ ቀይ ጃኖዋን ለብሳ ከመንበሯ ላይ ጉብ። ላቂያን የመረጥኩት የበለጠ ፍቅር – አትኩሮት – ትህትና – ተደማጭነት – እንክብካቤ ጥበቃ ሊሰጠው የሚገባ የተስፋ አምክንዮ ይዤ ስለቀርብኩ ነው። ይህቺን የምወዳትን ዬክት እርእስ ይዢ ብቅ ያልኩት።

1. መነሻ

10ዘመናዊቷን የደብረማርቆስ ከተማን ለማዬት የዳጎሰ ህልም ነበረኝ። አብዝቼ እሻቅልም ነበር። ስለምን? የሴቶች ዓለምዐቀፍ የርትህ አንደበት የተከፈተባት ታላቅ ባለውለታ የተግባር ማሳ በመሆኗ። የዴንማርኳ ርዕሰ መዲና ኮፐንሀገን የማህበረሰቡ ጸሐይ ለሆኑት አንስተ – ትጉኃን የአርነታችን ልዩ ጧፍ ነበረች። ዴንማርክ ሀገርነቷ በደሴት ውበት የተነጠፈላት ነው ማለት ልቻል ይሆን?

ዴንማርክ በተፈጥሮ የኃይል ማመንጫ ተጠቃሚነቷ የዘመናቱን ሱናሚያዊ ጥፋትን ለመታደግ በብዙ ሁኔታ መሰናዶዋን ያሟላች አብነታዊ ሀገር ስትሆን፤ በተገጣጣሚ ዬቤት ግንባታ ዘርፍም አንቱነቷ ቁንጮ ነው – ለአውሮፓውያኑ። በእንሰሳት ተዋፆ ምርትም የተባ ብቃት እንዳላት ይነገርላታል። ከዚህ በተረፈ የባሩድ መርዛማ ጪስ፤ የመትረዬስ አሲዳማ ሩምታ ፈጽሞ ያልደፈራት የሰላም ድንግል ምድር ናት። አምላክ መርቆ በፈጠራላት ጸጋዋ ንጹህ አዬርን የምትመገብ ደልዳላ ውብ ወ/ሮ ሀገር። ክረምት በሰማዩ ነጭ የአሻቦ አበባ – በጋ ደግሞ በተፈጥሮ ልምላሜ የፈካች። ታድላ!

የኮፐንሀገን ርዕሰ መዲናዋ ዴንማርክን ስታዩ ልክ ደብረ ማርቆስ እንዳላቸሁ ይሰማችኋል። ልዩነቱ እነሱ በ21ኛው ምዕተ ዓመት ላይ ያሉ ዘመኑ ለፈቀዳላቸውን ሥልጣኔ ተጠቃሚዎች ሲሆኑ ማርቆስዬ ደግሞ ገና ጎሳ ላይ ባለ በወያኔ ሃርነት ትግራይ ቡድናዊ አስተዳደር በቀል ከሚደቃቸው ከተሞች አንዷ መሆኗ ነው። ፍትህ – የራባት -የራቃትም።

በተረፈ የተፈጥሮ መልክዕ ምድራዊ አቀማመጧ፤ የከተማዋ አመሰራረትና ግራና ቀኛ ያሉት ዬቤቶች ሰልፍ ሁኔታ ክረምት ላይ ከዝናቡ ጋር ያለው የውቂ ደብልቂ ጠረን ሁሉ ቁርጥ ደብረማርቆስ – የዴንማርክ ርትዑዋ ከተማ ኮፐንሀገን። እናላችሁ የነፃነት ትግሉ ቤተሰቦች ገና ወደ ዴንማርክ ለመሄድ ስናሰብው ጀምሮ ነው በመንፈስ አብርን ቤተኛ የሆነው። ማንና – ማን? ይመጣበታል —-

2. ምልሰት

በ2009 ከታህሳስ 18 ቀን ጀምሮ አፈሩ መርግ ሆኖ ይክበዳቸውና የወያኔው ዞጋዊ ድርጅት መሥራች ሄሮድስ መለስ ዜናዊን ጨምሮ የኃያላን ሀገሮች መሪዎች በG20 ዓለምአቀፋዊ ጉባኤ ለመታዳም በዴንማርክ ርዕሰ መዲና ኮፐንሀገን ላይ እንደሚገኙ ከታወቀበት ቀን ጀምሮ የነፃነት ራህብተኛ ወገኖች በዬተዳራጁባቸው መድረኮች ሆነ ድርጅቶች ስንቃቸውን ማሰናዳት – ለጉዟችው የሚያስፈልገውን ትጥቅ ማሟላት ቀድመ ብለው ነበር ዬተያያዙት። በዬአውሮፓው ሀገር ነፃነት ከናፍቆቱ ጋር በህብረት መከረ። ዘመቻው ማዕከላዊ ከመሆኑም በላይ የተቃዋሚ ድርጅቶችንም ያሳተፈ ነበር። ዋና አዝማቻቸው እረኛው ጋዜጠኛ አህመድ ሲሆን ዬስምሪቱ ጠቅላይ አዛዥ ደግሞ የከረንት አፌርስ ዴስከሽን ፎረም ፊት ላይ ነበር። በዬአካባቢው ዝግጅቱ በግልና በወል ጦፈ። በቂ ፍላዬር ፖስተር በአይነት በብቃት ተዘጋጀ። ኮፐንሀገንን በፍትህ ፈላጊያኑ ኢትዮጵያዊ ድምጽ ቀውጢ ለማደረግ መንፈስ አሳምሮ ተሳለ። የኮፐንሀገን የነፃነት ትግሉ ልጆች ስምንት ብቻ ስለነበሩ ጎደሎውን ሁሉ ለመሙላት በትጋት በዬአካባቢው ይጎድለናል፤ አቅም ያስፈልገዋል ባልናቸው መሰረታዊ ጉዳዮች ሁሉ ከአገልግሏ ጀምሮ ሰፊ መሰናዶ ለዘመቻው ተደረገበት።

ቀኑ በጉጉት ሲጠበቅ ደረሰልን። አቶ መለስን ከሥፍራው ተገኝቶ እርቃናቸውን ማስቀረት፤ ቀልባቸውን መግፈፍ፤ በአለም አደባባይ ሊዘግቡ በተዘጋጁት ጋዜጠኞች አቤቱታውን ማስቀረጽ ጉልበታሙ ዓላማችን ነበር። በረዶው ታዲያ ጉድ ነበረ። በተለይ ለሲዊዝ ታዳሚ ኤክሲሞስ ምስጋን ይነሳው - 21 ግራድ።

አይዋ በረዶው በነፃነቱ ተጠቅሞ በተመቸው ሁኔታ ተደራጅቶ ማን ነክቶኝ ብሎ፣ ተራራ ሰርቶ፣ ምሽጉን አጠናክሮ ጠበቀን። ታዲያላችሁ ከበረዶው ተራራ የሚልከው በረዳማ ንፋስ ሰውነትን ፍሪዝ አደረገው። ተመሳስለን ቁጭ። ነጩን ባዘቶ ለብሰን በሰማይ አሻቧዊ አበባ ተሽሞንሙነን የጎጠኛውን መሪ ሴራ ለማራገፍ አቅማችን በእልህ አደራጅተን ማን ደፍሮን አለን – እኛው። ሰልፉ ዓለምዓቀፉ ጉባኤ እስኪያበቃ ድረስ በተከታታይ ቀናት የሚከውን ነበር። ውሏችን ከዛው ስለነበር የአርበኛን ስንቅ የተሸከመች ታሪከኛዋ አገልግሏም ተሰላፊ ነበረች። እኔው አጮልቄ ሳያት አገልግሏን እሷንም አይዋ የሰማይ አመልማሎ ጎሰም ያደርጋት ነበር። አልራራላት – ሲገርም።

እውነት ለመናገር የበረዶው ክምር የዴንማርክን ከተማ አስተዳደር በፍጹም ሁኔታ ያሸነፈ ጡንቸኛ ነበር ማለት ይቻላል። ሰፈር አድባሩ በተለይ መንገዱ በመልክ የለሽ ሁኔታ ተለነቆጠ። ታዲያንላችሁ አይዋ በረዶ ሌትና ቀን ከተሰለፍንበት እምንቀር መስሎት ሳይደክመው ያወርደዋል – ያወርደዋል። በሌላ በኩል ደግሞ ሰውም መኪናም በማይደርስበት ቦታ በነጭ ተፈጥሯዊ አሻቧዊ አበባ ጋራ ምድሩ ተንቆጥቁጦ ለሽ ባሉት ወንዞቿ ላይ ሳይቀር  ነጭ አልጋ ተዘርግቶ በነጭ አልጋ ልብስ ተሽሞንሙኖ ስታዩት ናፍቆ- ገነት ከዚህ ደግሞ ምን ጣለህ ያሰኝ ነበር።

ጉዙው ደግሞ ሌላው ፈታኝ ጉድ ነበር። ብዙ መንገዶች ዝግ ነበሩ። በበረዶ ብቻም ሳይሆን ለጥበቃ ተብሎም። ስለሆነም የጋራ መጓጓዣዎቻችንም እንዲሁ ሞተራቸውን ለማስነሳት ሆነ ለማራመድ ጋዳ ነበር። እዛው በረዶ  ሳንዱቹ አለሁኝ ቢልም እጅ አልታዘዝለትም ብሎ አሻፈረኝ ስላለ ዬጉርሻዋ ዓይን ከእኛ ራህብ ይልቅ  ወደ አመልማሎው ያደላ ነበር። መሬት ነህና ወደ መሬት ትመለሳለህ አሰኘው። እንዲህ  ዬእናት ሀገር ልጆች በዬአሉበት – በዬተገኙበት ፈተናን ለማሸነፍ ስንዱዎች ናቸው። ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጥር እምለውም ለዚህ ነው።

ከሰላማዊ ሰልፉ ደግሞ ማታ ቅልጥ ያለ እመቤት ኢትዮጵያን ማዕከሉ ያደረገ የሰከነ ህዝበዊ ስበሰባ ይካሄዳል። መስተንግዶው ተሟልቶ። አዳር ላይ ሌላ ጨዋታ የለም። የቀጣዩ ቀን ሰላማዊ ሰልፍ በምን ሁኔታ ቢሆን የበለጠ ተደማጭነት ይኖረዋል ነበር። በዬት አቅጣጫ ቢሆን የዓለምን የሚዲያ አትኩሮት ቀልብ መሳብ ይቻላል ነበር የወልዮሹ ዕድምታ። ፈጽሞ ብዕሬ አቅም ኑሯት ልትገልጸው አትችልም የነበረው አመራር – አደረጃጀት – መተሳሰብ – መደማመጥ – ፍቅር – መከባበር – የወይይት ፍጭት እንዴት ነፍስን ይታደግ ነበር። ዕድለኛነቴን ዛሬ ላይ ሆኜ ሳስበው ዕጣዬ ሁሉንም ዓይነት ገጠመኝ እንዳጣጥም – እንድኖርበት አምላኬ የመፍቀዱን ሚስጥር ዕሴቱን ሳስተውለው ባልፍም ካለ ጸጸት እንዲሆን አድርጎልኛል። „አድርገህልኛልና አመሰግንሃለሁ“

እስካሁን ከታደምኩባቸው ብሄራዊ ሆነ ዓለምዓቀፋዊ የውጭ ሀገር ዜጎች ጉባኤዎች በሀገር ወስጥም ሆነ በውጭ ከገበሬው መንደር ቀጥሎ የዴንማርኩ የመንፈሴ ልዩ ሙሽራ – የጸደቀ ምዕራፍ ነበር ማለት እችላለሁ። ሌላ ዓለም ሌላ ውበት ነበረው። እናት ሀገር የሁለመና መሠረት ናትና! በስደት ሀገር ደግሞ የዚህ ጥልቅ የአብሮነት መንፈስ ሲገኝ የምድር ገነት ነው። ይህን መንፈስ እንዴት መልሰን ማምጣት እንደምንችል አምላክ ይርዳን። አሜን! ምክንያቱም በዚህ መስዋዕትንት ያላፈን መንፈስ ለማስቀጠል ያለው አሳር፤ የድልድይ ሰባራው ዘመቻ፤ የአቅም ብክነቱ … እሱ ባለቤቱ ይፍታው። የሚገርመው የዛ አቅም ሞገድ ጉልበታምነት በወያኔ አስተዳደር ተፈቅዶላቸው የስበሰባውን ሂደት እንዲዘግቡ የመጡትን ጋዜጠኞች እስከማሸፈት የደረሰ ነበር። መርምሩት —-

2. መዳረሻ

በዚህ ወቅት ከካናዳ ድረስ ፕሮግራሙን ከሰላማዊ ሰልፍ ጋር አደራጅቶ  ከእኛ ጋር ዴንማርክ የነበረ ምርጥ ኢትዮጵያዊ ወንድም ነበረን። እንደኛው ማደሪያ ዶርሚተሪ ተመድቦለት አብሮን ሰሜን አሜሪካን አውሮፓ ላይ ወክሎ በዕንባ ምጡ ታደመ። የዕንባ ምጥ ቀለበት የአህጉር ድንበር የለውምና። ድንቅ ልዩ ወንድም። የእኔ ጌታ ናፍቆቴን በፍቅር ጠልፌ አክብሮታዊ ምስጋናዬ ይደረስህ እላለሁ። ሌላው የአንድ ቤት ልጆች ስንገናኝ የነበረው የፍቅር ጥበብ፤ የጠረኑ ደም ግባት ዬጸዳሉ ኢትዮጵያዊ ጥሪኝ ለትውፊትነት ብቁ ነበር። ከረንት ልዩ እኮ ነው። መግቢያ ዓውደ ምህረት እኮ ነው። ለከረነት ዋጋ አነሰው። እስኪ ኢሳቶች ስለከረንት ህይወት ገባ ብላችሁ ቃለምልስ አድርጉ በተራቸው እነሱም ይጠዬቁ። ውብ አንባ ወርቅ መንደር ከረንት! ዬታሪካችን ዘለበት ነው ከረንት! የስደቱ የመከራ ዘመን በኽረ በልግ።

በ2009 ከታህሳስ 17 እስከ ፍጻሜው የዴንማርክ ውሎ በተቃውሞ ሰልፉና በህዝባዊ ስበሰባው ለመገኘት ከመላ አውሮፓ  የተውጣጡ ካናዳንም ጨምሮ የተግባር አርበኞች በግልም በድርጅትም ታደሙበት። „ኢትዮጵያዊነትን“ ማዕከላቸው ያደረጉ ደፋር ማህበራዊ ድህረ ገፆች፤ የኮሚኒቲ ራዲዮ ፕሮግራም አዘጋጆች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ተሳታፊ ነበሩ። ሞትም ቢሆን አብረን ብለው።

ዬኔዎቹ ዬነፃነት ራህብተኞች ወገኖቼ መነሻዬ ሆነ መድረሻዬ የወያኔ ልብጥ ሁለተኛ ቪዲዮ ነው። አሁን የወያኔ የጎጠኝነት ፍቅረኞች ዝርዝር አገኘን ብለው የሚያላዝኑት ስሰማ ወያኔ እዬተኛ ነው የሚኖረው ለማለት ልድፈረው። እንደነገርኳችሁ ገና ሃሳቡ ሲወጠን ቤተኛ ቤተሰብ ነበርን። ስንደርስ ደግሞ ለቅድመ መሰናዶ ምግብ ለማዘጋጀት ካሳለፍነው ሌሊት በስተቀር እዛው ዴንማርክ ዬሚኖሩትን ጨምሮ በአንድ ካንፕ ውስጥ ነበርን። ለእኔ ከሥጋ ዝመድና በላይ – በላይ  - በላይ ዓላማዬ ላቂዬ ነው።

ዶር. ሙሉአለምን ያገኘሁት በዚህ ወቅት ነበር። እንደሚታወቀው በዘመነ ቅንጅት ድጋፍ ድርጅቶች በዬአካባቢው ተደራጅተው ነበር። ከቅንጅት መራራ ስንብትም በፊትም ሆነ በኋላ አቅም በፈለገው ጅረት ተበትኗል። ኖርወይ ላይ ግን በዚህ ላቂያ በሆነ ብቁ ሙሴ አማካኝነት ሃይል አልባከነም። አቅም አልሾለከም፤ ዓላማዊ ድርጅታችን አልተናደም፤ ቤተሰባዊ ግንኙነቱ በማፍያ ሰላዮች አልተበከለም። ማህበራዊ ዘርፉ ተወሳክ አልበቀለበተም። የወያኔ ሴራም አላፈራበትም – እንዲያውም የወያኔ መርሃ ግብር በውጭ ሀገር ድቅቅ ብሎ አመድ ስንቁ የሆነበት መሰረታዊ አመክንዮ በዶር. ሙሉዓለም ነበር ማለት ልቻል። ኖርወይ ላይ የሚታዬው ቋሚና በተግባር የሰከነ የእኩልነት ዓውደ ምህርት የአብነቱ ተከታታይነት ስምረት ሚስጥር ይህ ነው። ዶር ሙሉዓለም አቅም ነው። እሱ እራሱ ስክነት ነው። ብቁ መሪም አባትም ነው። የቀለም ዕውቀት ተመክሮው አቅም እንዴት እንደሚፈጠር፣ ከዬት እንደሚገኝ፤ ከተገኘ በኋላም እንዴት መያዝ እንዳለበት፤ እንዴትም እንደ መክሊቱ ጥቅም ላይ መዋል እንዳለበት ለተግባር ሰልጥኖ የተፈጠረ ብቁ ሰው ነው።

ይህን ለምናውቅ – ለምንረዳ ሰዎች የሰሞናቱ ሚስጥር የግንቦት 7 ሰዎች በአውሮፓ ዝርዝራቸው ተገኜ  በማለት ወያኔ የሚረጨው ፍዝ መረጃ  ጭድ ነው። የወያኔ ዘገባ ቀለሙ ያለቀ ቀፎ ነው።

እኛ የነፃነት ትግሉ ቤተሰቦች ምን በመዳፋችን እንዳለን ጠንቅቀን እናውቃለን። ዛሬ አይደለም ይህ የነፃነት ትግሉ የተግባር ላቂያ ወንድማችን የምናውቀው ….. እኔ እራሴ በ2010 በጸጋዬ ድህረ ገጽና ራዲዮ ፕሮግራም ቃለ ምልልስ አድርጌለት ነበር። ዶር. ሙሉዐለም የምርምር ሰው ስለመሆኑ በቃለ ምልልሱ ተካቷል። የጸጋዬ ድህረ ገጽ ሆነ ራዲዮ ፕሮግራሜ ታዳሚዎች የምርምር ሰው – ሳይንቲስት ስለመሆኑ በሚገባ ያውቃሉ። ዛሬ አይደለም ወያኔ ለእኛ የሚነገረን አሳምረን ጌጣችን – ክብራችን – ኩራታችን – ተስፋችን እናውቀዋለን። እንዲህ ላለ ብርቅ ወንድም ምንም እንኳን በቅርቡ ሁነን ልንረዳው ልናግዘው ባንችልም በመንፈሳችን ሰሌዳ በውስጡ ስላለ ሰንደቃችን አድርገን እንደታቦት የምንከበክበው የተከደነ ሃብታችን ሲሳያችን ነው። ጥበቃው ደግሞ የመዳህኒተአለም ነው።

ክብርት ዳኛ ብርቱካን ሜዴቅሳ ታስራ በነበረችበት ጊዜ ቤተሰቧ ምንም ዓይነት የኢኮኖሚ መስተጓጎል ሳይደርስበት ልጇ ሃልዬ የተገባውን ሳታጣ እንድትማር ያደረገው በቋሚ የተግባር ጌታው በዶር. ሙሉአለምም የሰከነ የአመራር ክህሎተ -ብቃት ነበር። እንዲያውም የመጀመሪያ ልጁ ባለው ለሴቶች ቅናዊ አክብሮታዊ ታማንነትም ምክንያት ማን ብሎ እንደጠራት እናውቃለን። አብሶ ለሴት ታጋይ እህቶቹ ሲመሰክር አንደበቱን ከፍቶ፤ ሲከታተል መንፈሱን ውስጡን በፍቅር በልግስና ሰጥቶ በልዩ አክብሮት ነው። በዚህ ዘርፍም ክህሎታዊ አንባሳደራችን ነው ብዬ ደፍሬ መናገር እችላለሁ።

ያ ብርቅና ድንቅ ሳይንቲሰት ከእኔ ከትቢያዋ ከማህይማ ጋር ነበር አብሮ በዛ ብርዱ በሚጋርፍበት ቦታ የታደመው። እራሱን ዝቅ አድርጎ ለኢትዮጵያ ዬዕንባ ዬምጥ ብሄራዊ ጥሪ በግንባር ቀደምትንት መሰለፉ ኢትዮጵያ ሀገራችን ፈጣሪያዋ የማይረሳት መሆኑን የሚያሳይ የሃቅ ዬወርቅ እንክብል ነው። ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ልጆቹን እንዴት ይጠብቅ – እንዴትስ ኃላፊነቱን ወስዶ ይንከባባከብ እንደነበር ላሰተዋለው ዶር. ሙሉ ዓለም የሥጦታ ሥነ – ጥበብ ነው ማለት እችላለሁ። እኔ በኖርዎይ ልጆች አዘውትሬ እቀናለሁ። እዛ ብሆን እልምአለሁ።

ወገኖቼ የእኔዎቹ ያ ሰላማዊ ሰልፍ የለዬለት ነበር። ገንዘባቸውን ከስክሰው ብቻ ሳይሆን ዴንማርኮች 8 ብቻ ስለነበሩ ሌሎችንም ሃላፊነቶች ወስደው የቆረጡ – የወሰኑ የኢትዮጵያ ልጆች ለጦርነት ነበር የሄዱት። ስለዚህ ይህ ዕንቁ ሳይንቲስት ዬኢትዮጵያ ብርቅዬ ልጅ ዬእናቱን የምጥ ዘመን የጸነሰ፤ ችግሯን ለመጋራት የቆረጠ፤ ማናቸውን መስዋዕትንት ለመቀበል የወሰነ የሰብዕዊነት ተሟጋች ተምሳሌት፤ የሙህርነት ህይወታዊነት ናሙና ልዩ ምልክታችን ስለመሆኑ የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያውቀው አበክሬ በአጽህኖት ልገልጽ እሻለሁ። በዛ ሰላማዊ ስለፍ እኮ ከሳይንቲስቱ ጋር ብዙ ሚዲያዎች ቃለ -ምልልስ እድርገዋል። ዬት ሄዶ ነበር ወያኔ? ለነገሩ 5ኛ ክፍል ላይ እንዴት ተብሎ …..

ሌላው ሁለተኛው ላቂዬ ደግሞ እኔ እንኳን ቅዱስ ሚኬኤል ነው የምለው ግሩምዬ ነው። ዛሬ አይደለም የጉርምዬን  ዬአይቲ (IT) ባለሙያነት ሽፍታው ወያኔ የሚነግረን። እኔ እንዲያውም እንዳገኘሁት ነበር „አንዲት የነፃነት ታጋይ ሴት ድህረ ገጽ ኖሯት ድህረ ገፆን ሊንክ አልደረጋችሁም። ደግሞ የልጆች ፕሮግራምም አላት እሱን እንኳን እንዴት?“ ብዬ ነበር ዬወቀስኩት። በዕድሜ ታናሼ ነው ገሩሜ። በተግባሩ ደግሞ ከድርጊት የበቀለ ታላቄ። ይህን ጥያቄ እንዳገኘሁት ያነሳሁለት ሙያውን አሳምሬ ስለማወቀው ነበር። ወያኔ የግል ልብሱን አደፈ ብሎ ቆሻሻ ውስጥ ጨምሮ በሌላ ቀን ከቆሻሻ ቅርጫት ውስጥ አውጥቶ መልሶ ይለብሰዋል ልበልን?

ከዬት ይመጣል ጫካና ሀገር መምራት አራባና ቆቦ ነው ….

ወያኔ የሚያንደፈድፈው፣ ዛሩ እንዲህ የሚቀሰቀሰበት ሙያተኞችን ትጥቅ አስፈትቶ ለእሱ ለራፊ ለፍርፋሪ እንዲያጎነብሱ ማድረግ አለመቻሉ ነው። ሙሁሮቻችን እውቀታቸውን ሃገራቸው መሬት ላይ ተግባራዊ ማደረግ ባይችሉም ቁጭታቸውን ሆነ እልሃቸውን መወጣት የሚችሉት በነፃነት ትግሉ ዬሙያቸውን ሃላፊነት በተባ ድርጊት ማዋህድ ሲችሉ ብቻ ነው። ይህ ደግሞ ለወያኔ አብሾው ነው ያንደፈድፋዋል።  …. ግሩሜ ግን አድርጎታል – አሳብዷቸዋል። ስለዚህ ይህ ቀንበጥ ወጣት ታሪኩም ትውልዱም ዕንባ ያማጠውን ጥሪ የተገበረ የድርጊት ቀንድ እንዲሆን አድርጎታል። ስታዩት እራሱ ወርቅ ነው። ፍልቀቱ ነገን ያበራል። የእውነት የተግባር ጸዳሉ ሌትና ቀን የሚያበራ የሚንቦገቦግ የሰብል አዝመራ ነው። ግሩሜ አዝመራ ነው። እሱም ታዳሚ ነበር በኮፐንሃገኑ የዴንማርክ የተቃውሞ ስለፍም ብሄራዊ ስበሰባችንም ላይ ነበር። እኔ በአካል የማውቀውም እዛ ነው ከተባረከው የዴንማርክ የተቃውሞ የዕንባ ምጥ ጥሪ ላይ።

ግሩሜ ማለት ሲደመር – ሲደመር፤ ሲባዛ – ሲባዛ ሥራ ነው። ሃብትነቱ ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው። የግሩሜ የትኩሮት አቅጣጫ አንደኛው ሰብዕዊነት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ልዐላዊነት ነው። የደንበር ጉዳይ ለግሩሜ ደሙ ነው። በቃ! እኔ እራሴ ስለ ሰባዕዊነት መረጃ ስፈልግ እማገኘው ከእሱ የመረጃ ቋት ነው። አሁን ለዛ ራሱን በቤንዚን በማቃጠል ሰምዕትነቱን ስለገለጸው ስለ ዬኔሰው ገብሬ ማን ቋሚ ሁነኛ አለው? ለግሩሜ የኔሰው ገብሬ የጭንቅላቱ ህሊና ነው እንዲህ ልግለጸው። ግሩሜ ረቂቅ የብሩህ ተስፋ ብርሃናማ ማዕረግ ነው።  እና ጭዶቹ ሳታውቁት ቀርታችሁ ነው ድህረገጹን boycott እንዳይታይ ያደረጋችሁት – ታላግጣላችሁ …. ተረት ተረቶች fantasise/ize ስልችት ብሎናል ይህን ቆርጦ ቀጥል የጭቃ ለጭቃ ጨቀጨቅ ጉዟችሁ —-

3. ክወና

ሁለቱም ወንድሞቼ ለሥም – ለዝና – ለታይታ – ለዕውቅና አይደለም የሚደክሙት። ኑሯቸውን የሰጡት ዛሬ በወመኔው ወያኔ ለሚጠቀጠቀው „ኢትዮጵያዊነት“ ነው። እነሱ የአደራ የተግባር ሙዳዮች ናቸው፤ የበቀል ብቅሉ ወያኔ በንቀት የእግር ገንባሌ ያደረገውን ሰንደቅአላማችን፤ በተጨማሪም ጨርቅ ተብሎ በሄሮድስ መለስ ስላቅ የተንቋሸሸውን ብሄራዊ ዓርማ እነዚህ ተስፋዎች ወደ ክብሩ ለመመለስ ነው ውስጣቸውን ለነፃነት ትግሉ የሸለሙት። በማናቸውም የርሃብ መስክ ሁሉ እንደ ጥንቸል ሰንሰለታማ የመከራ ሙከራ ለሚደርግበት ሀገራችን ኢትዮጵያ ብሩህ የነገ ቀን ነው የሚባትሉት። በወያኔ ለተገፋችው ለተፈናቀለችው እናት ምድር ነው የሚባትሉት። ክብሯ ለተገፈፈው መሬት ነው ከፊት ለፊት ወጥተው የሚታገሉት። ውለታቸው ጥልቅ ፊኖሚናል ነው።

ስለዚህ ያ — እሮ አሮ የተመለሰበትን ካሳ ለማግኘት ቆራርጦ በሚያቀርበው ልብድ ዘገባ መረታት መፈታት ለአፈታም አይገባም። ነገ እነዚህ የቁርጥ ቀን ልጆች በባዶ ሳጥን ላይ ባለው የሙት መንፈስ  እዬገላበ ያለው የትግሬ ነፃ አውጪ ድርጅት ወያኔ ሞት ሆነ ዬእድሜ ልክ እስራት ሊፈርድባቸው ይችላል። ጉዞው ወደዛ ነው። ሲያሰኘውም የሰው ዘረፋውን ወይንም ዬማጥቃት መርዙን አጋጣሚ ጠብቆ ይፈጽማል – በብዙ መልኩ። ትውልድን መንቀል ነው ተልዕኮው።

ግን ግን የኔዎቹ – ክብረቶቼ አንድ ነገር ወያኔ በቀል ተብሎ ሥሙ ቢቀዬር ምን ይመስላችኋል? ወያኔ እኮ የበቀል ብቅል እኮ ነው። ስለሆነም የበቀሉ መረጃ፤ የበቀሉ የፍርድ ሂደት ሰለባ ላለመሆን የበቀሉ ዘገባ አራጋቢና አሽቃባጭ ላለመሆን  ደጉ ጨዋውና ቻዩ የኢትዮጵያ ህዝብ መሰናዳት አለበህ እላለሁ።

አንተን እዬገደለ ነው የበቀል ብቅሉ ወያኔ ለአንተ ቆሜአለሁ የሚለው -። አንተን እዬደረመሰ ነው ከእኔ ወዲያ ነፃነት ሰጪ ላሳር እያላ የሚደለልህ – የበቀል ብቅሉ ወያኔ። ስለዚህ በጥብጦ ሊግትህ የሚሻውን መርዝ በቃህኝ! ብልህ ልታስቆመው የምትችልበት መንሹም ያለህ ከእጅህ ነው።

በተረፈ በኮፐንሀገኑ የተቃውሞ የዕንባ ዬምጥ ጥሪ ላይ የተገኛችሁ ስበሰባውንም ሆነ የተቃውሞ ስልፉንም እንዲሳካ ያደረጋችሁ ብዙኃኑ የነፃነት አርበኞች፤ የንብ አውራ የነበረውን ጋዜጠኛ አህመድንም አክዬ እንዲሁም የኮፐን ሀገን የነጻነት ትግሉ ብርቅዬ ልጆች አዘጋጆች በተጨማሪም ድርቡን ሃላፊነት የወሰዱት የሲዊዲን ናፍቆቶቼን በድጋሚ አመሰገንኩ። ናፍቅኩኝም።  …. ታሪካችን ይፍልቃል …. አይዞን! የበቀል ብቅሉ ወያኔ እኛን አለማሸነፉን የሚረጋገጠው ማናቸውንም የድውይ ወያኔን መረጃ ማፍሰስ – ማባከን – ማክሰል ስንችል ብቻ ይሆናል። ትጋት ስንቃችን፤ ጥንካሬ ቀለባችን ጽናት ትጥቃችን  ይሁን። በዬትኛውም ቦታ በዬትኛውም ሁኔታ ዬአርበኞቻችን ተስፋ የመጠበቅ ግዴታ ይኖርብናል!  www.tsegaye.ethio.info Aktuell Sendung www.lora.ch.tsegaye

የነፃነት ባለውለታው ሰንድቅዓላማችን እንዲህ ያምርበታል! http://www.zehabesha.com/amharic/archives/33255

 

ውዶቼ የኔዎቹ  - እጣታችሁን እባካችሁ  ከተግባር ጋር አቆራኙት። ፍጥነት …. እሺ – እንበርታ!

http://ecadforum.com/2014/07/31/urgent-campaign-to-call-fax-white-house/

 

ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጥር ኢትዮጵያዊነት!

ጀግኖቻችን ቋሚ ዬህሊናችን መንገዶች ናቸው!

ነፃነት ያለው ማንነት ለነፃነት ክብር አለው። ግን የነፃነት የቃና መንፈስ ከተገለጠለት ብቻ!

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

እንግሊዝ እና ጫት፡ ጫትም “አሸባሪው”ተክል ይባል ይሆን?

$
0
0

ከረ/ፕሮፌሰር መኩሪያ መካሻ አ.አ.ዩ

በኢትዮጵያ፣ በኬንያ፣ በሱማልያ፣ በጅቡቲና የመን የሚዘወተረው አነቃቂው ጫት ምሥራቅ አፍሪካን አልፎ አውሮፓን ሲያስጨንቃት ኖሯል፡፡ ዛሬ ግን የጫት አድባር በአውሮፓ አልቆመለትም፡፡ ከአውሮፓሀገሮች እስከ ዛሬ ድረስ ጫትን በህገ-ወጥነት ሳትፈርጅ የቆየችው እንግሊዝ ሰሞኑን የመጨረሻውን ውሳኔ አስተላልፋለች፡፡ ጫትን የቃመም ሆነ የነገደ የሚቀጣና ይህ አደገኛ ዕጽ የተከለከለ መሆኑን ይፋ አድርጋለች፡፡
Khat
የጫት ተጠቃሚዎች ጫትን እንደሚያሞካሹት ‹‹ጫትን ስንቅም ንቁ፣ ደስተኛና ተናጋሪ ያደርጋናል›› ቢሉም ከእንግዲህ በኋላ በሀገረ እንግሊዝ ጫትን መቃምም ሆነ ማዘዋወር የተከለከለ ሁኗል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በተለይ ለእንግሊዝ ገበያ በቀጥታ ከኬንያ የሚያቀርቡ የጫት ገበሬዎች በውሳኔው ተደናግጠዋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ናሲር አደም የተባለው የካርዲፍ የሶማሌ ማህበረሰብ መሪ አብዛኛዎቹ የሶማልያ ማህበረሰብ አባላት ጫት በመታገዱ ደስተኞች ናቸው፡፡ ጫትን በብዛት መቃም በሰዎች የአእምሮ ህመምና የቤተሰብ መፍረስን ያስከትል እንደነበር ጨምሮ አስረድቷል፡፡
ናሲር እንዳለው በቀድሞ ጊዜ አዛውንቶች ነበሩ የሚቅሙት፣ በአሁኑ ዘመን ግን ወጣቶች ተለቀውበታል፡፡ የእንግሊዝ የሶማሌ ማህበረሰብ ጫት እንደታገድ ሲታገል ቆይቷል፤ ፖሊስ፣ የጤናና የፓርላማ ባለስልጣናት ሕብረተሰቡን በማዘጋጀት በኩል ምን አድርገዋል? ሲልም ጠይቋል፡፡
በተፃራሪው የጫት ኤክስፖርት ነጋዴው ማቲዎስ ጊቶንጋ ‹‹ጫትን ማገድ ሰብአዊነት አይደለም፡፡ የእንግሊዝ መንግሥት ዕገዳውን ቢያንስ እንኳ እኛ እስከምንዘጋጅ ድረስ ለአንድ ዓመት ሊያነሳ ይገባል›› ሲል አምርሮ ተናግሯል፡፡ ሌላኛው ሴት ቤሲያ ካቱሬ ደግሞ ‹‹ተስፋዬን አጥቻለሁ፡፡ ልጆቼን እንዴት እንደምመግብና የትምህርት ቤት ክፍያ እንደምከፍል አላውቅም›› ብላለች እገዳውን ተከትሎ፡፡

የእንግሊዝ የዕጾች ጉዳይ ክትትል ኃላፊ ቺፍ ኮንስታብል አንዲ ቢሊስ ደግሞ ፖሊስ ከጤና ሙያተኞችና ከማህበረሰቡ አባላት ጋር ስለ ዕገዳው ተቀናጅቶ እየሠራ ነው ሲል አስታውቋል፡፡ በነገራችን ላይ በብርስቶል ከተማ ከዚህ ቀደም ጫት የሚሸጡ 30 የንግድ ተቋማት በዕገዳው ምክንያት ሥራቸውን እንደሚያቆሙ ገልፀዋል፡፡

በሀገረ- እንግሊዝ ጫት መታገዱን በተመለከተ የተለያዩ አስተያየቶች ያሰነዘራሉ፡፡ አንዳንዶቹ ጫት አንደ አደገኛ ዕፅ ተወስዶ መታገዱ ትክክል አይደለም ሲሉም ተደምጠዋል፡፡ ለምሳሌ ያህል ዳኒ ኩሽሊክ የተባለ የፀረ- ዕፅ ዝውውር ፋውንዴሽን ኃላፊ ሲናገር ‹‹አልኮል መጠጥ በሰፊው ጥቅም ላይ እየዋለ ጫት መታገዱ ትክክል አይደለም!›› ብሏል፡፡ አይይዞም የተወሰኑ ህዳጣን የሕብረተሰብ ክፍሎችን ማለትም ሶማሌውያንና የመናውያንን ጫት ጋር በተያያዘ መወንጀል አይገባም ሲል ተችቷል፡፡

በወጣው የዕገዳ ህግ ጫትን ለመቃም ይዞ የተገኘ 60 ፓውንድ ይቀጣል፡፡ የእንግሊዝ የሀገር ውስጥ ሚንስትር ቴሬዛ ሜይ እንዳሉት ጫት በእንግሊዝ ብቻ ሳይሆን በኔዘርላንድስ፣ በአብዛኛዎቹ የአውሮፓ ሕብረት ሀገራት፣ በቡድን 8 ሀገራት ማለትም ካናዳና አሜሪካን ጨምሮ ጫትን አግደዋል፡፡ በአዲሱ ህግ መሰረት በእንግሊዝ ሀገር ጫትን ማዘዋወር ለ14 ዓመት እስራት እንደሚዳርግ ታውቋል፡፡

በሀገራችንም ሆነ በአካባቢው ሀገሮች በስፋት የሚመረተውና ኤክስፖርት የሚደረገውን ጫት ማገድ ለምን አስፈለገ? ብሎ መጠየቅ ተገቢነት አለው፡፡

በብዙዎች ዘንድ ካት፣ በሀገራችን ደግሞ ጫት፣ በኬንያ ሚራ የሚባለው ተክል እጅግ ስለ ተከሉ ሲንቆላጰስ ደግሞ ‹‹የአረቦች ሻይ›› በመባል ይታወቃል፡፡ ጫት በበለፀጉት ሀገራት ቢታገድም በሀገራችንና በአካባቢው መመረቱና ጥቅም ላይ መዋሉ ቀጥሏል፡፡ በአብዛኛዎቹ ተጠቃሚዎች ዘንድ ከጫት ይልቅ አልኮል ጉዳት አለው ይባልለታል፡፡ ጫት እንደ ቡናና ሻይ ሁሉ ጉዳት የለውም የሚሉ ሞልተዋል፡፡

በእንግሊዝ የዕጽን አላግባብ መጠቀም አማካሪ ምክር ቤት ግምት ወደ ሀገረ- እንግሊዝ በዓመት 2,560 ቶን ጫት ይገባል፡፡ ከዚህ ውስጥ የእንግሊዝ መንግስት 2.5 ሚልዮን ፓውንድ ቀረጥ ያገኝበታል፡፡ ብዙ በእንግሊዝ የሚኖሩ ሱማልያውያን፣ ኢትዮጵያውያንና የመኖች በጫት ንግድ የሚተዳደሩ በመሆኑ እነዚህን ነጋዴዎች ስራ ፈት ያደረጋቸዋል፡፡ ከሁሉም በላይ ዕገዳው በምሥራቅ አፍሪካ በጫት ምርት የተሠማሩ 500,000 የሚደርሱ ገበሬዎችን ይጎዳቸዋል፡፡

ጫት አእምሮን ይረብሻል፣ ያሰንፋል፣ ድብርት ያሳድራል፡፡ በተጨማሪም አፍን ማሽተት አልፎ ጥርስን ይጎዳል፡፡ ብዙዎቹ ቃሚዎች ጥርሳቸው የሻገተና የወላለቀ ከመሆኑም በላይ የአፍ ካንሰር ያመጣል ተብሎ በተመራማሪዎች ተነግሯል፡፡ ጫት ከአእምሮ ወታወክ (psychosis) በሽታ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው በሚል የተረጋገጠ ማስረጃ ግን አልቀረበም፡፡ በአንድ በየመን ሀገር በተደረገ ጥናትና ለዓለም ጤና ድርጅት የቀረበው ማስረጃ እንደሚያመለክተው 90 በመቶ የሚሆኑ ጎልማሳ ወንዶች ለሦስትና አራት ሰዓታት ጫት ይቅማሉ፡፡ ዶክተር ጓንኤይድ ከሰንዓ ዩኒቨርስቲ ሲናገሩ ‹‹ጫት ቃሚዎች መጀመሪያ ደስታ፣ ከዚያም በድብርት ስለሚያዙ ለአእምሮ መታወክ ተጠቂዎች ሊሆኑ ይችላሉ ብለዋል፡፡ በእንግሊዝ ሀገር የተደረገው ጥናት የሚያመለክተው ብዙ ወጣቶች ከትምህርት እንዲቀሩና ቤተሰቦቻቸው ደግሞ ሥራ ከመሥራት ይልቅ በጫት ደንዝዘው ቤት እንዲውሉ ማድረጉን በተጨባጭ ማስረጃ ያቀርባል፡፡ በተጨማሪም አል-ሻባብ የተሰኘው አሸባሪ ድርጅት በጫት ኤክስፖርት ገቢውን እንደሚያጠናክርም ይጠረጠራል፡፡ አል-ሽባብ ለሽብር ድርጊቱ ማጠናከሪያ ጫትን የሚጠቀም መሆኑ ከተረጋገጠ ጫት- አሸባሪው ዕጽ መባሉ አይቀሬ ይሆናል፡፡

ዓባይ እንደዋዛ፤ የግብፆች “ተፈጥሯዊና ታሪካዊ መብት” ክስተቶች ክፍል አምስት (አክሎግ ቢራራ)

$
0
0
Dr. Aklog Birara

Dr. Aklog Birara

አክሎግ ቢራራ (ዶር) የዛሬዋ ኢትዮጵያ ባለቤት አላት ለማለት አያስደፍርም። የህወሓት/ኢህአዴግ ሕገ-መንግሥት ኢትዮጵያ የምትባለ ረጂም ታሪክ ያላላት እንዳትሆን ከስሯ አናግቷታል። ሉዓላዊነት ከኢትዮጵያ ተዘዋውሮ በቋንቋ ለተደራጁ አዲስ መሳፍንት ለሆኑ የክልል አለቃዎች ተሰጥቷል። ህወሓት/ኢህ አዴግ ይኼን ያደረገበት ስትራተጂካዊ ምክንያት የታወቀ ነው፤ ከፋፍሎ ለመገዛት እንዲያመች። አስቸጋሪ ሆነ የምናየው ተቃዋሚው ክፍል ባለቤትነት ለመያዝና አገሪቱን ለመታደግ ብቁነት አለማሳየቱ ነው። ሻቢያ፤ ህወሕትና ሌሎች የጎሳ ስብስቦች አገሪቱን ለድርድር አቅርበው እንደ ሸቀጥ ቸርችረው የባህር በሯን ከዘጉ በኋላ አሁንም ልዩ ልዩ ክፍሎች ካለፈው አልተማሩም ለማለት ይቻላል። ዛሬም እንደ ዱሮው፤ ኢትዮጵያ በገዢው ፓርቲና በአንዳንድ ስብስቦች ለድርድር ታጭታ ትገኛለች። በ60ዎቹና በ70ዎቹ መጀመሪያ ለሃገራቸው ልማትና ለዲሞክራሲ—   [ሙሉውንለማንበብእዚህላይይጫኑ]—-

የህብረቱ ሂደትና የውህደት ጥያቄ (ኢትዮ ለጋ)


ዐይነ ስውር ድንጋይ ወርውሮ፣ ጠላቱን ስቶ ወዳጁን መታ!

$
0
0

“ምነው ወዳጅህ እኮ ነኝ፤ ቢለው”
“ዝም በል! ዋናው አለመሳታችን ነው!” አለው

ከዕለታት አንድ ቀን ሁለት ጓደኛሞች ጫካ ሄደው እንጨት ቆርጠው ለመምጣት ይፈልጋሉ፡፡ አንደኛው በመጥረቢያ ቅርንጫፍ እየቆረጠ ሳለ እጁና ሳያስበው ቆርጦ ጣለው፡፡ 
ጓደኝየው የተቆረጠውን ክንድ በፌስታል ውስጥ ከትቶ፤ እጁ የተቆረጠ ጓደኛውን ይዞ ወደ ቀዶ – ጥገና ሐኪም ወሰደው፡፡ 
ዶክተሩም – “በጣም ዕድለኛ ነህ እኔ የተቆረጡ አካላትን መልሶ የማጣበቅ ክሂል ባለሙያ ነኝ፡፡ በአራት ሰዓት ውስጥ ተመልሰህ ና” አለው፡፡ 
ጓደኝየው – “እሺ ዶክተር ባሉኝ ሰዓት እመጣለሁ” ይልና ይሄዳል፡፡ 
ከተባለው ሰዓት በኋላ ሲመለስ፤ ዶክተሩ፤ 
“እጨርሳለሁ ካልኩበት ሰዓት ቀድሜ ጨረስኩ፡፡ ገዋደኛህ ጤንነቱ ተመልሶ እዚህ ታች ወዳለው ግሮሠሪ ሄዷል፡፡”
ጓደኝየው በደስታ ጮቤ እየረገጠ ወደተባለው መጠጥ ቤት ሄደ፡፡ ጓደኝየው ጭራሽ የዳርት ውርወራ ግጥሚያ ይዟል፡፡ 
ከጥቂት ሣምንታት በኋላ ጓደኛሞቹ አሁንም ወደጫካ ሄደው እንጨት ቆረጣ ላይ ተሰማሩ፡፡ ባለፈው እጁን የቆረጠው ሰው አሁን ደግሞ እግሩን ቆርጦ ጣለው፡፡ ጓደኝየው እንዳለፈው ጊዜ የተቆረጠውን እግር ፌስታል ውስጥ ከትቶ ጓደኛውን ይዞ ወደዚያው የአካል ቀዶ ጥገና ሐኪም ዘንድ ይዞት ሄደ፡፡ 
ሐኪሙም፤ 
“አየህ፤ የእግር ቀዶ – ጥገና ትንሽ ከበድ ያለ ነው፡፡ ከስድስት ሰዓት በኋላ ተመለስ” አለው፡፡ 
ጓደኝየውም፤ 
“እንዳልከው አደርጋለሁ ዶክተር” ብሎ ሄደ፡፡ 
ከስድስት ሰዓታት በኋላ ተመልሶ ውጤቱን ለማወቅ ወደ ሐኪም ሲመጣ፤ 
ሐኪሙ “ይገርምሃል ከነገርኩህ ሰዓት አስቀድሜ ሥራ አገባደድኩ፡፡ ጓደኛህ እዚያ ታች ወዳለው እግር ኳስ ሜዳ ሄዶልሃል” አለው፡፡ 
ጓደኝየው ሐኪሙ አመስግኖ ወደ ኳስ ሜዳው ወርዶ ሲያየው፡፡ ያ እግረ የተገጠመለት ጓደኛው ምን የመሳሰሉ ጎሎች እያገባ ነው፡፡ 
ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ግን፣ ያ ጓደኝየው እጅግ ከባድ የመኪና አደጋ ይገጥመውና አንገቱ ሙሉ ለሙሉ ተቆረጠ፡፡ ጭንቅላቱ ብቻውን ወደቀ፡፡ 
እንደተለመደው የፈረደበት ጓደኛ ጭንቅላቱን በፌስታል ከትቶ ቀሪውን የጓደኝየውን አካል ጭኖ ወደ ሐኪሙ በረረ፡፡ 
ሐኪሙም፤ 
“ጭንቅላት መግጠም እጅግ ከባድ ነው፡፡ ለማንኛውን ከአሥራ ሁለት ሰዓት በኋላ ተመለስ” አለው፡፡ 
ተመልሶ ሲመጣ፤ ሐኪሙ፡- 
“ይቅርታ አድርግልኝ፡፡ ጓደኛህ ሞቷል” አለው፡፡ 
ጓደኛውም፤ 
“ዕውነትክን ነው፡፡ የጭንቅላት ነገር ከባድ መሆኑን እገምታለሁ” አለ፡፡
ሐኪሙም፤
“ቀዶ ጥገናውን እንኳ ደህና አድርጌ ነበር የሰራሁት፡፡ ግን አየህ፤ አንተ ስታመጣው እዛ ፌስታል ውስጥ ታፍኖ ትንፋሽ አጥሮት ነው የሞተው!” 
*   *   *
እጅ እግሩን ከቆረጠበት አደጋ ያልተማረ፣ አንገቱን የሚቆረጥበት ሰዓት ይመጣል! ከስህተት አለመማር መዘዙ ራስን እስከማጣት ያደርሳል፡፡ 
የአካላችን ሁሉ አናት የሆነው ጭንቅላት የሁሉ ነገራችን መሪ ነው፡፡ አንዴ ካመለጠ የማይገጣጠም መሆኑም ይሄንኑ የሚያመላክተን ነው፡፡ ሁሉን ተግባራችንን በአቅል በአቅል የሚያስቀምጥልን፣ የሚያደራጁልን፣ መንገድ የሚያገባልን የህይወት መሪያችን እሱ ነው፡፡ በሀገር ደረጃ ሲታይም፤ ተቋሞቻችንን፣ ድርጅቶቻችንን፣ ት/ቤቶቻችንን፣ ኮሚሽኖቻችንን፣ ሚኒስቴሮቻችንን፣ ኢንዱስትሪዎቻችንን ወዘተ የሚመሩ ርዕሰ – አመራሮች እንደጭንቅላት ናቸው፡፡ የእነዚህ ጭንቅላቶች ልክ መሆን፣ ቅጥ መያዝና የድርና ማግ መቀናጀት ነው የሀገርን ጤና ልክነት የሚረጋግጠው፡፡ ይህ የጭንቅላት ክህሎት ከሌለ፣ ካልተባ፣ ከቀልብ ካልተዋሃደ ወጥነት ያለው አመራር ማግኘት አይቻልም፡፡ ጨርሶ ባዶ የሆነ ዕለት ደሞ መሄድ ቀርቶ መቆም ያቅታል፡፡ 
ገጣሚና ፀሐፌ ተውኔት ፀጋዬ ገ/መድህን፣ በ “በልግ” መጽሐፉ፤
“በዚህ በያዝኩት ጎራዴ፣ አንተግክን ቀንጥሼ ብጥለውም” 
ከባርኔጣህ በስተቀር፣ ዋጋ ያለው ነገር አይወድቅም”
የሚለን ለዚህ ነው 
“የዕውቀት ማነስ ፓለቲከኛ አደረገኝ” ከሚል ሰው ይሰውረን፡፡ አንዳንድ ፖለቲካ እጅግ አስመሳይ ከመሆኑ የተነሳ “የፆም መኪያቶ” “መኪያቶ” የሚባለውን ዓይነት ይሆናል፡፡ ወይ ሙሉውን መፆም ነው፣ አሊያ የሚለውን ሃሳብ ጨርሶ መርሳት ነው፡፡ “ፀብ ክርክር ካለበት ጮማ – ፍሪዳ፤ ፍቅር ያለበት ጎመን ይሻላል” ይላሉ አበው፡፡ በላሸቀ ኢኮኖሚ ውስጥ የፖለቲካ ጀግና መሆን እያደር ሽባ እንደሚያደርገን መገንዘብ ጭንቅላት ይዞ ማሰብን አይጠይቅም፡፡ ስለዚህ አስቀድሞ ኢኮኖሚውን ማዳን ነው፡፡ የዝሆን ጥርስ አናት ያለው ጉልላት ላይ ያለ የታችኛው ህዝብ መከራ አይታየውም፡፡ ያም ሆኖ የማይለወጥ ነገር የለም ሁሉም የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡ ወይም እንደ ቪክተር ፍራንክል፤ 
“ሁኔታዎችን መለወጥ ካልቻልክ ራስህን ለመለወጥ ትገደዳለህ” እንላለን፡፡ ቪክተር ከ2ኛው ዓለም ጦርነት ሆሎኮስት ቃጠሎ እልቂት የተረፈ ሳይካትሪስትና ፀሐፊ ነው፡፡ ከእልቂት ከተረፈ በኋላ በሰው ልጅ ላይ ምን ለውጥ እንደሚመጣ አስተውሏል፡፡ ለእያንዳንዱ ለውጥ ያ ሁሉ መስዋዕትነት መደገም አለበት ማለት አይደለም፡፡ ከማዕበሉ በኋላ የረጋ አየር፣ አየርም ቢሉ ለውጥ የሰፈነበት፤ ይመጣል ማለት እንጂ! 
የበላይም ይናገር የበታች ለሀገራችን የሚጠቅመው መደማመጥ ነው፡፡ በአንድ አቅጣጫ ብቻ እንደሚኬድበት መንገድ (One way road) አንሁን፡፡ የሚነገረንን እንስማ፡፡ ሌላው ሰው ድንገት ከእኔ የተሻለ ሀሳብ ቢያቀርብስ? እንበል፡፡ 
ደራሲ ከበደ ሚካኤል 
“አሁን የት ይገኛል ቢፈልጉ ዞሮ
መስማት ከማይፈልግ የባሰ ደንቆሮ”
ያሉትን አለመዘንጋት ከብዙ አባዜ ያድናል፡፡ እርግጥ ይህንንም የሚሰማ ካለ ነው፡፡ 
አበሻ በኢኮኖሚው መዘበትና ምፀት ማውራት ይችልበታል፡፡ ኢኮኖሚው አላፈናፍን ሲለው መውጫው በግጥም መተንፈስ ነው፡- 
“በቆሎ፤ በዝናብ፣ ሲጠብስ እያያችሁ
ሰዉ ሥራ አይሰራም፣ ለምን ትላላችሁ!”
የፖለቲካ ምፀት ሲያምረው ደግሞ፤ 
ዐይነ ስውር ድንጋይ ወርውሮ፣ ጠላቱን ስቶ ወዳጁን መታ፡፡
“ምነው? ወዳጅህን? ወዳጅህ ነኝ እኮ!” ቢለው፤
“ዝምበል፡፡ ዋናው አለመሳታችን ነው!” አለ ይባላል፤ ይላል፡፡ 

ምንጭ፥ –  አዲስ አድማስ

Comment

‹‹አያ ጅቦ ሳታመኻኝ ብላኝ›› በበፍቃዱ ሃይሉ

$
0
0

‹‹ታዲያ ጥፋቴ ምንድን ነው ትላለህ?!››፣ ብሎኛል አንዱ መርማሪዬ ስለዞን ዘጠኝ እና እኔም እራሴ እንደጦማሪም እንደአራማጅ ተራማጅም ሠራሁ የምላቸውን ነገሮች ዝርዝር ነግሬው ሳበቃ፡፡ በኋላ ላይ በእስር ቤት ቋንቋ ከ‹‹አባሪዎቼ›› ጋር መገናኘት ከተፈቀደልን በኋላ ስንጠያየቅ ለካስ ሁላችንም ይቺኑ ጥያቄ ተጠይቀናል፡፡ ይኼ ነው እንግዲህ የምርመራችንን ሒደት የሚገልፀው ጥያቄ፡፡ ‹‹ተጠርጥረን›› የተያዝንበትን ጉዳይ የሚያረጋግጥ ሥራ ሠርተን ባለመገኘታችን (ወይም ‹‹ባለመናገራችን››) ታዲያ ጥፋትህ ምንድን ነው? ተባልን፡፡ ምርመራው የኛን ነፃ መሆን አለመሆን ለማጣራት ሳይሆን ጥፋት ለማግኘት ነበር፡፡ ብዙዎች ‹መንግሥት ዞን ዘጠኝን ለምን ሁለት ዓመት እንደታገሠው› ግራ በመጋባት ይጠይቃሉ፤ ባሕሪው አይደለምና፡፡ የኢትዮጵያ ሀሳብን የመግለጽ ነጻነት ምኅዳር በቀላሉ እንደገመቱት ተይዘን፣ ተመርምረንና ‹‹ተገኘባችሁ›› የተባልነው ‹‹ የግንቦት 7 [እና ኦነግም ጭምር] አባልነት [ብሎም ግብ አስፈጻሚነት] ›› በሽታ ለተከሳሽነት አብቅቶናል፡፡ ቀጣዩ የክርክር ሂደት ነው፡፡
ከዚያ በፊት ግን ዞን ዘጠኝን በሩቅም በቅርብም የሚያውቁ በግራ መጋባት መልስ እንደሚሹ በማሰብ ይቺን አጭር ማስታወሻ ለመጻፍ ተገድጃለሁ፡፡ የእስራችን ሂደት ምን ይመስላል? የምርመራችንስ? እውን የግንቦት ሰባት አባል ነን? [ታዲያ] ለምን ታሰርን? በቅርቡ እንፈታ ይሆን?

ደቂቅም ይሁን ሊቅ ስለኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እውነታ የሚጽፍ ማንኛውም ሰው [ኢትዮጵያ ውስጥ ሳለ] አንድ ቀን እታሰር ይሆን እያለ መስጋቱ አይቀርም ፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም በአንድ መጽሐፋቸው ላይ ሰው ነገረኝ ብለው የኢትዮጵያ ሕዝብን በሦስት የመደቡት፡- የታሰረ፣ ታስሮ የተፈታ እና ወደፊት የሚታሰር በማለት፡፡ እርግጥ ዞን ዘጠኝ ‹‹ሐሳቡን መግለጽ ፈርቶ ዝም ያለ ሁሉ እስረኛ ነው›› ብሎ መደምደም ሦስቱም ምድብ አንደኛው ውስጥ ያጠቃልለዋል ‹‹የታሰረ›› በሚል፡፡ ዞን ዘጠኞች ጦማራችንን በከፈተን በሁለት ሳምንት ሲታገድብን እና ሌላ ስንከፍት ግና መጨረሻ ላይ ታጋቾቹ እኛ እንደምንሆን እናውቅ ነበር፡፡ ያንን የሚያረጋግጥ ተደጋጋሚ የደህንነቶች ክትትል እና ምልክቶች ስለደረሱን መታሰራችን ማስደንገጡ ባይቀርም ያልተጠበቀ ግን አልነበረም፡፡
እስሩ በክትትሉ የተገኘነውን ስድስት የዞን ዘጠኝ አባላት እና ሦስት ጋዜጠኛ ጓደኞቻችንን መሆኑን በተለይ የጋዜጠኞቹ [ቢያንስ ለእኛ] ያልተጠበቀ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ የኋላ ኋላ ስንመለከተው ግን በእኛ አስታኮ እነሱንም ማሰሩ የታሰበበት ዘመቻ እንደሆነ መገመት አይከብድም፡፡ እኛን በቁጥጥር ስር የማዋሉ ሒደትም ቢሆን በቅጡ የታሰበበት ነበር ሁላችንም (ከአስማማው በቀር) ከቀኑ በ11፡00 ገደማ በያለንበት ስንያዝ አስማማው በማግሥቱ ታስሯል፡፡ ሌሎቻችን ቤታችን በሚፈተሸበት ሰዓት ሕጉ የሚፈቅድበት ሰዓት(12፡00) አልፎ ነበር፡፡ በቁጥጥር ስር ካዋሉን በኋላ የሕገ-ወጥ አያያዝ ሰለባ የመሆናችን ሂደት የሚጀምረው ከዚህ ነው፡፡

ማዕከላዊን በክፉ ስሙ ቀድሞ ለሚያውቀው ሰው ግቢውን መርገጥ በራሱ ልብን ያርዳል፡፡ ሆኖም በልቤ /ጓደኞቼም እንደእኔ ሳይሰማቸው አይቀርም/ አንደኛ እኛ ጸሐፊ እንጂ ወታደር ወይም ሰላይ ባለመሆናች፣ ሁለተኛ መቼም ከበፊቱ የተሻለ ሰብዓዊ አያያዝ ሳይኖርም አይቀርም የሚል የዋህ ተስፋ በማሳደሬ ብዙም አልተሸበርኩም ነበር፡፡ የገባሁ እለት ከታሳሪዎች በተሰጠኝ ማብራሪያ ‹‹ሳይቤሪያ›› መግባቴን አወቅኩ፡፡ ከዚያ የ HRW-They want confession የተሰኘ ሪፖርት ላይ የተፃፉ ነገሮች ሁሉ ትክክል መሆናቸውን ለመረዳት የፈጀብኝ ከአንድ ሳምንት ያነሰ ጊዜ ነበር፡፡

ምርመራ ማዕከላዊ ስታይል
ምርመራ በማዕከላዊ ከብልጠት ይልቅ ጉልበት ይበዛበታል፡፡ መርማሪዎቹ የምርመራ ችሎታቸው ተጠርጣሪውን የተጠረጠረበትን ጉዳይ ከማውጣጣት ይልቅ የምርመራ ችሎታ እንዳላቸው ለማሳመን የሚጥሩበት ጊዜ ይበዛል፡፡ ይህም አልሰራ ሲል ጥፊ፣ ካልቾ፣ ከአቅም በላይ ስፖርት ማሰራት እና ግርፋት ድረስ ይዘልቃሉ፡፡ ይህ እንግዲህ እኔ ላይ ከተፈራረቁብኝ አምስት መርማሪዎች እና ሌሎችም አብሮ ታሳሪዎቼ ከነገሩኝ የተረዳሁት ነው፡፡ እርግጥ ሌሎች ‹‹እርቃንን ቁጭ ብድግ›› የሰሩ ተጠርጣሪዎችም ገጥመውኛል፡፡ ከባባድ ቅጣት (ወፌ ላላ ግርፋት፣ ጥፍር መንቀል) የደረሰባቸው ሌሎች ታሳሪዎች አብረውኝ የታሰሩ ቢሆንም ይህ የተፈፀመባቸው ግን ወደማዕከላዊ ከመምጣታቸው በፊት ነው፡፡ ከነዚህ መካከል የሀሮማያ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ይገኙበታል፡፡ የሚገርመው በዚህ ዓይነቱ ምርመራ የሰጡት ቃል ለማመሳከርያ ማዕከላዊ መምጣቱ ነው፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ወደማዕከላዊ ከመዛወራቸው በፊት ከባድ ቅጣት የተቀጡበትን ቦታ የት እንደሆነ እንዳያውቁ አይናቸው ተሸፍኖ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ እሥረኞችም መኖራቸው ነው – የደርግን ‹‹ቤርሙዳ›› ያስታውሳል!

እናም በሚያዋርድ እና ክብርን በሚነካ ስድብ በሚያስፈራ የቤቱ (የማዕከላዊ) ጥላ እና ኃይል በተቀላቀለበት የምርመራ ሂደት የተከሳሽ ቃላችንን ሰጠን፡፡ ቃላችን መቶ በመቶ እውነት አልነበረም፡፡ ጫናው በበረታ ቁጥር መስማት የሚፈልጉትን ‹‹ዓመፅ ለመቀስቀስ ፈልገን›› የመሳሰሉ በራስ ላይ ፈራጅ (Self-incriminating) ሐረጎችን እየተናገርን ነበር፡፡ ያም ግን ለመርማሪዎቻችን በቂ አልነበረም፡፡ ስለዚህ በሚጽፉበት ሰዓት እያንዳንዷን ‹‹ሠራን›› ያልነውን ሁሉ ሊያስከስሰን በሚችልበት ሁኔታ እየገለበጡ እና እየበጠበጡ ፃፉት፡፡ አንዳንዶቻችን እየተከራከርን ሲያቅተን ፍርድ ቤት ይፍታው ብለን ፈረምን፣ቀሪዎቻችን የቻልነውን ያህል ተደብድበንበት ፈረምን፡፡ ‹‹ከተናገርኩት ቃል ውጪ አንድም ቃል አልፈርምም›› በሚል እስከመጨረሻው ታግሎ የተሳካለት አቤል ብቻ ነበር፡፡

በምርመራው ሂደት የተረዳነው ነገር ቢኖር የማዕከላዊ መርማሪዎች ብቃት (Intelligence) አርጩሜ ብቻ መሆኑን ነው፡፡ እኔ ምርመራ ሲባል ይመስለኝ የነበረው ፖሊሶች ተጠርጣሪዎችን ፈፀሙ ስለሚባለው ነገር በቂ መረጃ ይዘው ግፋ ቢል ለምንና እንዴት እንደፈፀሙት ማውጣጣት ነበር፡፡ ‹‹ዕድሜ ለማዕከላዊ›› የተረዳሁት ነገር ቢኖር ምርመራ ማለት ለካስ ‹‹የሠራኸው ወንጀል ምንድን ነው?አውጣት!›› ማለት ኖሯል- ማዕከላዊ ስታይል፡፡ ‹‹ነጻ ነኝ›› ቢሉ ሰሚ የለም፡፡ አንዴ ታስረሃል ወንጀል ሊገኝብህ የግድ ነው፤ ካልሆነ ይጋገርብሃል፡፡
አሁን ሳስበው ማዕከላዊ ፈርሶ በሥር-ነቀል ለውጥ እንደገና መቋቋም ያለበት ተቋም ነው፤ ቢያንስ በሁለት ምክንያት፡፡ አንደኛ የምርመራው ሂደት (በራሳችን ጉዳይ እንደተረዳሁት) ትዕዛዝ አስፈፃሚነት ይስተዋልበታል፡፡ ማለትም በመርህ የሚመራ አይደለም፡፡ ሁለተኛ ምርመራው እውቀት መር አይደለም፡፡ ይህ ደግሞ የአገሪቱን ደህንት አደጋ ውስጥ የሚጥል ጉዳይ በምርመራው ድክመት ሳይታወቅ ሊታለፍ ይችላል፡፡ ይህ ችግር የተከሰተው ደግሞ መርማሪ ፖሊሶቹ ከብቃት ይልቅ ለታዛዥነት የተመቹ ታማኞች ሆነው በመመልመላቸው ነው፡፡

‹‹ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ››
በምርመራው ሂደት የተጨቀጨቅነውም ሆነ ተገድደን የፈረምነው ጽሑፎቻችንን የበይነ መረብ ዘመቻዎቻችንን፣ የወሰድናቸው ስልጠናዎችም ሆኑ አንዳንዶቻችን የሰጠናቸው ስልጠናዎች አመፅ ለማስነሳት መሆኑን ‹‹እመኑ›› በሚል ስለነበር የጠበቅነው ግፋ ቢል በወንጀለኛ መቅጫው አንቀጽ 238 ወይም 257 ሊከሱን አስበው ነው ብለን ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የክስ መዝገቡ ሲመጣ ‹‹ሽብር›› ያውም ከአስራ አምሰት ዓመት እስከ እድሜ ልክ የሚያስቀጣ አንቀጽ 4 መሆኑን ሳውቅ በበኩሌ ሳቄ ነበር የመጣው፡፡

ማስረጃ ተብለው ከክስ መዝገቡ ጋር የተያያዙት በአብዛኛው ጽሑፎቻችን፣ የዘመቻዎቻችን፣ የጋዜጣ መግለጫዎች እና በተለያዩ ሥልጠናዎች ወቅት የተዘጋጁ የሥልጠና መመሪያዎች (Manuals) ናቸው፡፡ ከዚህ በተረፈ ከግንቦት 7 እና ከኦነግ ጋር ያገናኛችኋል የተባልነው በሦስት ‹‹ሰነዶች›› ነው፡፡ አንደኛው ናትናኤል ኢሜይል ውስጥ በጥቅምት 2001 ተልኮለት የተገኘ የግንቦት 7 የዜና መጽሔት ነው፡፡ ይህ እንግዲህ ገና የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉ አዋጁ ሳይወጣ፤ ግንቦት ሰባትም አሸባሪ ከመባሉ በፊት መሆኑ ነው፡፡ ሁለተኛ ሶልያና ቤት ተገኘ ተብሎ እናቷ ‹‹ቤቴ ውስጥ አልተገኘም፣አልፈርምበትም›› ያሉት እና ለግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል ሰራዊት ምልመላ መመዘኛ ሰነድ ነው፡፡ ይህ የሶሊ የዘለቀ አቋም ለሚያውቅ ሙግት አያስፈልገውም፡፡ እኔ እንደውም ትዝ ያለኝ ከመታሰሬ በፊት የትዊተር ፕሮፋይሏ ውስጥ የነበረው ‹‹no for war›› የሚል መፈክር ነው፡፡ ሦስትኛው ደግሞ ማሕሌት ኮምፒውተር ውስጥ የተገኘው የኦነግ ፕሮግራም ነው፡፡ በርግጥ አብረው የተገኙት የሌሎች የኦሮሞ ፓርቲዎች ፕሮግራሞች ማስረጃ ተብለው አለመቅረባቸው መረዳት ብቻ – እሷም ለምን ፕሮግራሙን እንደያዘችው፤ እነሱም ለምን የኦነግን እንደመረጡ ያጋልጣልና የእመኑኝ ሙግት አያስፈልገንም፡፡ በመሰረቱ ሦስቱንም ‹‹ሰነዶች›› መያዝ ከቡድኞቹ ጋር ግንኙነት መመሥረት የሚሰሩትንም መውደድ ማለት አየደለም፡፡ ይህም ለመሪዎቻችን ባይታያቸውም እንኳ ለወገኖቻችን የጠፋቸዋል ብዬ አላስብም፡፡

ሌላውና በአስቂኝለቱ ተወዳዳሪነት የሌለው ውንጀላ ‹‹48 ሺሕ ብር በናትናኤል በኩል ተቀብለው ተከፋፍለዋል›› የሚለው ነው፡፡ ይህ ብር ፤‹‹አሸባሪ›› ከተባሉት ቡድኖች የተወሰደ እንዲመስል በሚያደናግር አገላለጽ የተጻፈ ቢሆንም የክስ መዝገቡ ውስጥ የተያያዘውና ገንዘቡ የመጣበት ደረሰኝ እንደሚያረጋግጠው የተላከው ከARTICLE 19 ነው፡፡ ይህንን ጨምሮ በእስር ላይ ለምትገኝ ጋዜጠኛ ቤተሰቦች መደገፊያ /ለእስረኛይቱም ማበረታቻ/ የተላከ መሆኑን ለመርማሪዎቹ በዝርዝር አስረድተናቸዋል፡፡ ይህንን እያወቁ ውንጀላውን ማኖራቸው እውነትም እኒህ ሰዎች ወንጀለኞች ናቸው ብለው አምነው ሳይሆን ‹‹ከቻልን አደናግረን እናስቀጣቸዋለን (የማይችሉበት ሁኔታ አይታየኝም)፣ካልቻልን ደግሞ በቀጠሮ ጊዜ እንገዛበታለን፣ ነጻ እስኪወጡም ቢሆን በእስር እናቆያቸዋለን›› የሚል ክፉ ምኞት ነው፡፡
befekadu
… ሳታመኻኝ ብላኝ!
አህዩት ከታች አያ ጅቦ ከላይ ሆነው ወራጅ ውሀ እየጠጡ ነበር አሉ፡፡ ነገር ያማረው አህዩትን ‹‹አታደፍርሽብኝ›› ሲላት ነገሩ የገባት አህይትም ‹‹ሳታመኸኝ ብላኝ›› አለችው ይባላል፡፡ የኛም ነገር እንደዚያው ነው፡፡
ፖሊስ ሲይዘን እኛ ላይ ይህ ነው የሚባል የመክሰሻ መረጃ አልነበረውም፤ እንዲያውም ከስማችን በቀር የሚያውቁት ነገር አልነበረም፡፡ ሌላው ቀርቶ ከደህንነቶታቸው በአንዱ ልከንላቸው የነበረውን የጽሑፋችንን ስብስብ እንኳን ሳያነቡት ነበር የያዙን፡፡
አሁንም ማስረጃ ብለው ከክስ መዝገባችን ጋር ያያያዙት ቢያንስ በእኔ ግምት ዘጠና በመቶ የሚሆነው ‹‹ሰነድ›› እኛው ነፃ ያወጣናል ብለን የሰጠናቸው ጽሑፎቻችን ናቸው፡፡ በመርማሪዎቻችን ንግግር ውስጥ እኛ ላይ ወንጀል የማግኘት Desperate ፍላጎት አይተናል፡፡ ምናልባትም እንደገመትነው ቢያንስ እስከ 2007ቱ ምርጫ ድረስ ከማኅበራዊ ሚዲያ ገለል እንድንልላቸው ፈልገዋል፡፡ ከዚህ የተሻለም አማራጭ አልታያቸውም ይሆናል፡፡
በእስካሁኑ ሂደት የማዕከላዊን ለገዢው ፓርቲ ወገንተኝነት በዓይናችን አይተን አረጋግጠናል፡፡ ቀጣዩ ደግሞ የፍትሕ ሥርዓቱን በአደባባይ መፈተሽ ይቀረናል፡፡ ለአሁኑ ግን በቅርቡ እንፈታ ይሆን… የሚል ጥያቄ ‹ሕጋዊ› ሳይሆን መላ ምታዊ አማራጮችን እገምታለሁ፡፡
ኢህአዴግ ወይም የኢህአዴግ መንግሥት የሚያዘው ፖሊስ እኛን በቁጥጥር ሥር ሲያውለን ስለወንጀላችን ማረጋገጫ (ጠበቆች Beyond reasonable doubt) እንደሚሉት ዓይነት ባይኖረውም መቼም የሆነች ስህተት ሳላገኝባቸው አልቀርም በሚል ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ወትሮም የተንቦረቀቀ የሚባለው የፀረ-ሸብርተኝነቱ አዋጅ ውስጥ የሚጥለን ነገር በቀላሉ ማግኘት አልቻሉም፡፡ አለመቻላቸው ግን የተነሱበትን እኛን የመክሰስ ዓላማ አላጠፋውም፡፡ የክስ መዝገቡን ሲያዘጋጁ አንድም የረባ ዐረፍተ ነገር ሳይጽፉ ይዘውን ፍርድ ቤት መቅረባቸው በራሱ አንድም የረባ ጥርጣሬና ማረጋገጫ እንደሌላቸው አመላካች ነው፡፡ ቢሆንም በቅርቡ ይለቁናል የሚል ግምት የለኝም፡፡ ለምን;

1ኛ. ኢህአዴግ በጣም የሚናደድባቸው እና ታሳሪውን በሚያዋርድ መልኩ ካልሆነ በቀር ከማያደርጋቸው ነገሮች ውስጥ አንዱ- አንዴ ያሰረውን ተቺውን ፤ ያውም ብዙ ደጋፊ ያለውን መፍታት ነው፡፡ ኢህአዴግ እንደልጅ እልህ ይጋባል ማለቴ ነው፡፡ (ይህንን ስል የእስራችንን ኢፍትሀዊነት የተመለከቱትን ጩኸቶች መጥላቴ አይደለም፤ ያለ እነርሱ መንፈሳችን አይጠገንም ነበር፡በአደባባይ የምናመሰግንበት ቀን ይመጣል)
2ኛ. መጀመሪያ የተጠራጠሩበት እና ኋላ የዋጧት ጥርጣሬያቸው፤ ማለትም (ምርጫውን ተከትሎ) አመፅ ማስነሳት በሚሉት ጉዳይ ላይ እቅድ እንደሌለን ቢያምኑም እንኳን ምናልባት እምነታቸው ከተሳሳተ Risk መውሰድ አይፈልጉም፡፡ ( መጀመሪያም የቀለም አብዩት ዶክመንተሪ አዝማሚያ ያስታውሷል)
3ኛ. ምንም እንኳን ዓመፅም፤ሽብርም የማስነሳት ፍላጎትም አቅምም፤ እንደሌለን ቢያምኑም የገዥው ፓርቲ ጠንካራ ተቺዎች መሆናችንን ስለሚያውቁ እና ስላልወደዱልን ፍርድ ቤት በምንመላለስበት ረዘም ያለ ጊዜ ባለው እስር ወቅት ቢያንስ የእስርን ምሬት እንድንቀምሳት ይፈልጋሉ፡፡ ቅጣትን ጨርሶ በነፃ መለቀቅ እንደማለት፡፡
4ኛ. ኢህአዴግ መፍረድ አይፈራም፡፡

የሁለት ሀገር ስደተኛው –ጋዜጠኛ። (ሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 10.08.2014 (ሲዊዘርላንድ -ዙሪክ)

እንሆ – በዚህ ዘመን ታሪክን እንደ ከሰል አመድ ባደረገ ጽልመታዊ የወያኔ ሃርነት ትግራይ ዘመን – የአንድነቱ ልዑል የአሉላ ማሾ ከወደ ስሜን የብራና ኮከብ መሪን አሰቀድሞ ብቅ አለ። ይህ ደፋርና ንቁ፤ በራስ የመተማመን መንፈሱ ሙሉዑ የሆነ ዕንቡጥ ስሜቱን ለመግለጽ ያለውን ብቃቱን ብራና ቆሞ የሚመስከርለት ድንቅ ወጣት ጋዜጠኛ አብርሃማ ደስታ ነው። አብርሽ የሥርዬት መንገድ ነው።

የወያኔ ሃርነት ትግራይ በጎሳ የሚዘረዝራቸው በደሎችን ሁሉ እዬመነዘር በግልጽ፤ በተብራሩ፤ ስሜትን በሚፈትሹ፤ አጫጭር ዘገባዎቹ ዘመኑ የፈቀደለትን ታሪክ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ ሲያኮመኩመን የቆዬ ትንታግ ነው። ጋዜጠኛና መምህር አብርሃም ደስታ „ ትግራይ የኢትዮጵያዊነት ባለ ጉልትነቷን እዬፈገፈገ እንድታጣ ከዘመተባት ጠላቷ ከአረሙ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌስቶ ጋር ትፋታ ዘንድ ቆሞ ያሰተማረ – የሰበከ – የመከረ ትጉህ ወጣት ነው።

ታናሼ አብርሽ በፎሎቄማ የአጻጻፍ ለዛው የብዕር ፍቅረኞችን ሰጥ ብሎ እንደሚወርደው ኢትዮጵያዊ ወንዝ መንፈሳቸውን የገዛ፤ ማህል ላይ ወለል እያለ የሚያስቸግረውን ግራጫማ የዞግ ወረርሽኝ በሽታንም ሳይቀር በመግራት ህሊናን ሚዛን ላይ ያሰቀመጠ –  ዬእርቅም ድልድይም ነው። በቀልና እኛ - በበደል ዓይን፤ በቀልና እኛ በፍትህ ጆሮ፤ በቀልና እኛ በመገፋት የዕንባ ምጥ እያቆላመጠ በሥነ – ጥበብ ማራኪያዊ ውበት እንድንፈታተሽ ከህሊና መንበር ጋር ፊት ለፊት ያገናኘ ብቁ የጥበብ ሰው ነው። እንደ እኔ ብዙ ነፍሳትን ከጥፋት ውሃ በሁሉም አቅጣጫ ታድጓል ባይም ነኝ።

አብርሽ በራሱ ውስጥ ስሜቱን – ፍላጎቱን – ራዕዩን አቅርቦ እያባበለ – እያሟገተ ቀልብን ይዞ መልእክቱን በማስተዋል እንከታተለው ዘንድ በብቃቱ ፍቅርና ሰፊ ተደማጭነት ያገኘ ትጉህ የብዕር ገበሬ ነው። አብርሽ ጨርሶ ሚዲያ ዳስሷቸው ያማያውቀውን የገበሬ መንደሮችን ሳይቀር ከትግራይ ወጣ ብሎም የዳሰሰ ወርቅ ወጣት ነው። ለምሳሌ በዘመነ ታሪካቸው ብዕርና ብራና ጎብኝቷቸው የማያውቁትን በጎንደር እንደ „ጮንጮቅ“ ያሉትን እጅግ ትንሽ የገበሬ መንደር ሳይቀር የደረሰውን ህዝባዊ በደል በማጋለጥ ሃቅን አደባባይ አቅርቦ ዬወያኔ ሃርነት ትግራይ የነፃነት ጠላትንትነት፤ የርትህ ዘረፋን፤ የሰላማዊ ሰዎችን ሰላም ቀማኛነትን ቁልጭ ባለ ንጹህ አግባቢ ቋንቋና በውባውብ የቃላት ቅንብሮቹ ዘዬ ዕውነትን ለባለታሪኩ ለፍተሻ ያቀረበ ባተሌ የሰከነ ጋዜጠኛ ነው።

አብርሽ መምህር እንደመሆኑ መሰሉን ለመተካትም በትምህርቱ ዘርፍም አባታዊ ሃላፊነቱን የሚወጣው ወያኔ ሃርነት ትግራይ „ ከትግራይ ውጪ ያሉ ኢትዮጵውያን በጥቅሉ አማራ በሚል ሥያሜ ሰው ያልሆኑ፤ ሁለት ትላልቅ ጆሮ ያላቸው። አንዱን ጆሮውን ለብሰው፤ ሌላውን አንጥፈው የሚተኙ“ እያለ ትግራይን ከኢትዮጵያ ገንጥሎ፤ ጥላቻን ኮልኩሎ በበቀል ብቅል አብቅሎ ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት የነበረውን መሬት ያያዘ የቁርሾ ብክል ደም በማምከን በኢትትዮጵያዊነት መንፈስ የኔ ፍሬዎችን ያጠበ፤ ያጸዳ፤ የወያኔ ቆሻሻውን ሁሉ የጠረገ ብልህ ወጣት ነው። መምህር አብርሃ ደስታ በተማሪዎች የኢትዮጵያዊነትን አቅም በመገንበት፤ ኢትዮጵያዊነትን ብድግ ያደረገ ለጋ ወጣት ነው። እንደ ሌሎቹ የጎሳ ጥመኞች አዛውንት መምህራን የመረጥከውን መውሰድ ትችላልህ በማለት ታሪክን ለባንዳ በረድ ያለጋለጠ ንቁ ወጣትም ነበር። ታሪክን ማህል ላይ ገትሮ ያለጠቆረ የሙያውን ሥነ – ምግባር ክብር ያስጠበቀ ታታሪ ወጣት ነው። ስለሆነም ይህ ጋዜጠኛ፤ ጸሐፊና መምህር ወጣት ድርብ ሃላፊነቱን የተወጣ – የቆረጠ የቀለም – ቀለማም አባትም ነው።

እጅግ የምትናፍቁኝ የሀገሬ ልጆች። „የሥላሴ አንድነትና ልዩነት“ ለተዋህዶ ልጆች የተሰጣቸው አባቶች ብቻ ነው የሚተረጉሙት – የሚያመሳጥሩት። „ካህን“ በመሆን ብቻ ይህ ታላቅ የዕምነት ዶግማ ሊደፈር ከቶውንም አይችልም፤ ስለ „ነገረ ማርያምም“ ቢሆን በተመሳሳይ ሁኔታ የተፈቀደላቸው ብቻ አንደበታው ተከፈቶ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ በአማንያን ሥረ ህሊና ማብቀል ይችላሉ። ታናሼ ጋዜጠኛ አብረሃም ደስታም „ማንነትን“ የተነተነበት መንገዱም ሆነ የሂደቱ ረቂቅነት ፍጹም ልዩ ስለነበር „እኔ ማን ነኝ? ከዬት ተገኘሁ? እንዴትስ መጣሁ? ከማንስ ተፈጠረኩ? ግንደ – ዘሬ እንዴት ተፈጠረ? ቅርንጫፉና ግንዱ እንዴት ሀረግን ፈጠሩ?“ በማለት ልክ የተቋም ያህል ነበር ያስተማረው። ዬአብርሽ ጸጋ ከሩቅ፤ ወይንም ከወንዝ ወዲያ ማዶ ወይንም ህዋው ላይ አይደለም የሚነሳው – ከተጨባጩ ከጠረኑ ከራሱ ውስጥ ተነስቶ አካባቢውን ቃኝቶ ደረጃውን እዬጠበቀ ወደ ብሄራዊ፣ አህጉራዊና፣ ዓለማቀፋዊ ትንፋሹን ያመጠዋል – ያጣጥመዋል። መሬት ይዞ ስለሚነሳ ዘርቶ ሊያበቅል የሚፈልገው ነገር  እጥፍ ድርብ እንደ ተፈጥሮው ማብቀል ዬቻለ ትምህርተ – ገቢራን ነው። አብርሽ ለትግራይ ህዝብ የታሪኩ አባወራ እንደ ሥሙ የአብራሃሙ ቤት ነው። „መድህን“ ቢሉትም ይገባል። ታዳሚዎችም ሆነ አድናቂዎቹ ዕልፍ ነን።

እኔ አብርሽን እጅግ አውደዋለሁ። እሱ በሚጽፋቸው ጹሑፎች ሥር የአስተያዬት ግድፈቶች ከሥር ተጽፈው ሳይ እጅግ ልቤ ይቆስል ነበረ። ይህ ልጅ – ይህ ወጣት – ይህ ቀንበጥ – ይህ ጀግና በወያኔ ሃርነት ትግራይ ሆነ በሰሉ የወያኔ ደጋፊዎቹ  የከረፋ የበደል ክምር ተጠያቂ ሊሆን ከቶውንም ፈጽሞ አይቻልም።

ወገኖቼ ይህን ቢፈቅድ እኮ ጋዜጠኛ አብርሃም ደስታ ለዶተሬትነቱ ሰፊ ዕድል ማግኘት ይችል ነበር። ተነጥፎ ተጎዝጉዞለት። ሀገር ውስጥ እኖራላሁ ቢልም እስከ ሚ/ር ደረጃ የሚያደርስ ዕድሉ ሰፊ ነበር። የመጀመሪያውን የወያኔ ሃርነት ትግራይ መስፈርት የሚያሟላ ጉልህ ወጣት ነበር። ግን አላስፈለገውም። መኖር የፈለገው በእውነተኛው ዓለም በጋህዱ ዓለም ነበር። ገሃዱ ዓለም የሚፈልገው ደግሞ እንደ ተፈጥሮው የሆነ ነፃነትን ነው።

የመኖር – የመተንፈስ፤  የመናገር፤ የመጻፍ፤ የመደራጀት፤ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ፤ የህግ የበላይነት፤ በድምጽ የሚመራ ሀገር፤ በደል – አድሎ – ስጋት – ረሃብ የሌለበት የእኩልነት ዜግነት ዓለም ነው። ይህን ከወያኔ ሃርነት ትግራይ የ40 አመት ትግል ጠብቆ ማዬት አልቻለም። ስለዚህ ከበደሉ ማሳ እራሱን አውጥቶ እሱ ስለሚያልማት ኢትዮጵያ መናገር ጀመረ …. ማስተማር ጀመረ …. መስዋዕትነቱን ተርጉሙት በነፃነት ህገ – ህግጋት መገዛት ቻሉ! በማለት ወቀሳውን ካለይሉኝታ  ለአራዊቱ ወያኔ  ገለጸ …. ሰሚ አጣ … እንዲያውም ተጠቂም ሆነ።

እኔ በጣም ለረጅም ጊዜ አስተውለው የነበረው አብይ ጉዳይ „ጋዜጠኛ አብርሃ ደስታ“ ለማለት እንኳን ጋዳ ነበር። ሙያው የሚጠይቀውን ያሟላ ሆኖ እያለ። ዘገባዎቹ ትኩስ – ግልጽ – የተብራሩ – ከማህበረሰቡ የተነሱ – ፈጽሞ በግነት ያልተወረሩ – ብዙኃኑን ያደመጡ –  አጭር – ደፍረው ጦርነት ውስጥ የሚያገቡ – ቅራኔ የተጋሩ፤  ዬእውነትን ጅረትን ተከትው ዬሚጓዙ – የዘመኑን ባህሪ ያደመጡ ነበሩ። ይህ ሙያው የሚጠይቀው በጋዜጠኛ አብርሃም ደስታ በቀጥታ በተፈጥሮው ያገኘው ልዩ ብቃቱ ነበር። ለነገሩ በሥልጠና የሚገኝ ክህሎት ነበር — ግን እሱ ከላይኛው ተፈቀደለት።

ወደ ሥነ -ጹሑፍ ሥልጡነነቱ ስትሄዱ ደግሞ  የነጠረ አቅም ነበረው፤ ጹሑፎቹ  የወያኔን ሆድዕቃ አሳምረው ጎርጉረው ግን ሳይጠገቡ እንዳጓጉ ላጥ ይሉ ነበር። ልብን እንደ ቅል አንጠልጥለው። ዝንፈት ያልጎበኛቸውም ነበሩ።

በሰብዕዊ መብት ተቆርቋሪነቱም ቢሆን ቁስሉ የተሰማው መንፈስ ነበር የሚታይበት። በሴቶች የእኩልነት ተሳትፎ ላይም አንጋፋ – ጎልማሳ – ወጣት – ጋዜጠኞች የሚዘሉትን ሥነ – ምግባር ያሟላ ነበር ማለት እችላለሁ። እጅግ አብዝቼ እምከታተለው ዘርፍ ነውና። በአብርሽ የዜና ትንተና የመረጃ አቅጣጫ ደግሞ ድንቅ ትርጉም ይታፈሳል። ዘገባዎቹ ሁሉ – ከቆዳ መልስ ነክቷቸው አያውቅም።  ወይንም ተቆርጦ እንደ አደረ ዝንጣፊ ጥንዙል አልነበሩም። ትኩስ ትኩሱን ለመንፈሳችን ይቀልብን ነበር። እንሆ አሁን ትግራይ አንደበቱ ተዘጋ …. ስለ አሉላ መንፈስ፣ ስለ አሉላ ጸሐይ – ትግራይ ምን ይል ይሆን? ጸጥ – ረጭ – ዝም —-  ያቺ የእኔ ጀግና ወ/ሮ አልጋነሽ ገብሩና መንገድ እንደወጡ ያዳመጥነው ዬፍሬዎቻስ – የነገ ተስፋዎቻችን ጉዳይ ማን ይንገርን – ዝግት ድርግም ያለ ጉድ …. ዳፍንት!

እኔ አንጀቴን የሚበላኝ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ጎጣዊ ማንፌስቶ ትሸታላቸሁ ብሎ የሚመጣን ኢትዮጵያዊ ዜጋን ለመቀበል ያለን አቅም ስስ መሆኑ ነው። ሁልጊዜ ጥርጣሬ። ሁልጊዜ ወቀሳ። ሁልጊዜ ዱላ። አብሶ ወጣቶች ባልበሉት ዕዳ ስለምን እንደሚወቀሱ ፈጽሞ አይገባኝም። እንዲገባኝም አልፈቅድለትም።

ማያያያዣ ነገር – አሁን የአንድነቱ አንደበቱን – ብቃቱን – አቅሙን ሳልጠግበው ለካቴና የበቃው አቶ ሃብታሙ አያሌው „ዬወያኔ ደጋፊ ዬነበር“ በሚል ከልብ ለመቀበል የነበረን ፈቃደኝነት ያረረ ነበር። አሁን ሲታሰር ጀግና እንለዋለን? ወያኔ አሁን ከሚያደርስባቸው ማናቸውም ስቃይ የኛውም የመንፈስ ረገጣ ሆነ ጥቅጠቃ ዘመን ይቅር የሚለው አይመስለኝም። አንድ ሰው በነፃነት ትግሉ እሰለፋለሁ ሲል በጣም ብዙ ነገሩን ነው የሚያጣው። የሚተርፈው የመንፈስ ጥሪት ለህሊና ማደሩ ብቻ እንጂ በግራ በቀኝ በሚወርደው ወጀብ ያለው ወጨፎ መመዘን ከቶ አይቻልም።

ለነፃነት ታጋዮቻችን ለመንፈሳቸው ጥበቃ ጥንቃቄ በሚመለከት ምድረበዳ ነው። ወያኔ እዬከፈለ። ውጭ ሀገር ላሉ ቱቦዎቹ ሳይቀር እንኳን ቀለብ እዬሰፈረ የእኛ ደግሞ በብላሽ ለማገልግልም ቆመጥ —- እም!

እርግጥ ተሰውረው – ተቀላቅለው አንድ ደረጃ ላይ የሚሾልኩ ይኖራሉ። ከዚህ ስጋት አንጻር ሊሆን ይችላል። ነገር ግን አራሳቸው ከፈለጉ ወደ ውርዴታቸው ያዝግሙ። በእኛ በኩል ያለውን መልካም አቀባባልና ፍቅር ከመሰጠት መቆጠቡ ግን የማይጠቅም ነው። ባይሆን ደረጃውን ይጠብቅ ያግባባል — እንጂ ገና በሩ ሳይደርሱ …

አንጀቴን እዬበለኝ የምጽፈው አብርሽ የሁለት ሀገር ስደተኛ የነበረ መሆኑ ነው። እኛ የነጻነት ፈላጊ ቤተሰቦች በይደር ዬያዝናቸው ጉዳዮች ነበሩን። ወያኔ ከጎጥ ዶክተሬኑ በማምለጡ እርምጃውን እዬተከታተለ መተንፈሻውን መዝጋቱ በሁለት ወጀብ ሲንገላታ እነሆ በእጅ ወድቆ እንደፈለጉት ይዘለዘላል። የበለጠ – የቀደመ – የተሸላ በመሆኑ ብቻ ሳይሆን „የኢትዮጵያዊነት ፋና“ በመሆኑም ጭምር ሁለመናውን ይደምስሱታል።

ፎቶዎቹን ስብስብ አድርጌ ስመለከታች መልሼ በዚህ መንፈስ እንደማለገኘው ሳስበው መንፈሴ ይመረቅዛል – በመግል። ፈዞ በድኑን ብቻ ይሆናል ዬሚሰጡን። ቀጣዩ የእሱ የወደፊት ተስፋ ሁለት ያጣ ጎመን እንዳይሆን እንደማንንኛውም የብዕር አርበኛ ለዓለም ዓቀፉ የብዕር ሽልማት ይበቃ ዘንድ ተግቶ መሥራት ያስፈልጋል። የታሪኩ ጠበቂና ዘብ አደር ልሆንለት ይገባል። አብሶ ወጣት ኢትዮጵውያን አብርሽን እንደ ወጣት አብነታቸው፤ እንደ ወጣት ሙሴያቸው ሊያዩት እንደሚገባ በእናትነቴ ዝቅ ብዬ እጠይቃለሁ።

የተግባር ዲታው እውነተኛውና አንጋፋው የኢትዮጵያ መምህራን ማህበርም በክህሎት የተቀመመውን ተመክሮውን አበልጽጎ ለሙያ አጋሩ ያለውን አክብሮትና አድናቆት ሊገልጽ ዬሚችልበትን ስልት መፍጠር እንዳለበት አሳስባለሁ – በትህትና። በአንድ ወቅት የክፍለሃገር አዳራጃችሁ ነበርኩና – ህገ ደንባችሁ እንዲህ ለሙያው አርበኛ አክብሮቱን እንደማይነፍገውም አስባለሁ። በተጨማሪም ጋዜጠኛና መምህር ርዕዮት ዓለሙም ታሪካችሁ ናት። እሷንም አዘውትራችሁ ልታስቧት እንደሚገባ በትህትና እጠቁማለሁ።

በሌላ በኩል ደግሞ እንደ ሥነ ጥበብ ቤተሰብ አባልንቴ ወጣት ከያንያን አብርሽን – ክታባቸው እንዲያደርጉት በትህትና አሳስባለሁ። እንደ ጋዜጠኝነቴም ደግሞ የሙያ አጋራቹ ከፊተኛው ረድፍ ላይ በመገኘት ለሙያው አህጉርና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ወቅታዊ መረጃዎችን በመላክ – ተግባሩን በማስተዋወቅ እረገድ ተጓዳኝ ተግባራትን አቅሙ ያላችሁ ወገኖቼ ትከውኑ ዘንድ በአጽህኖት አሳስባለሁ።

ምን ቀረኝ? ለሰብዕዊ መብት አስከባሪ ድርጅቶችም መረጃዎችን በአጫጭር በእንግሊዘኛ ከተሰሩ ባለው መስመርና ግንኙነት የሎቢውን ተግባር በቀላሉ መከወን ይቻላል። አብሶ የፍርዱን ሂደት የቀጠሮ ቀናቱን ውሎዎች ሁሉንም በእንግሊዘኛ መሠራታቸው እጅግ ጠቃሚው መንገድ በመሆኑ አትኩሮት ቢሰጠው መልካም ነው።

ማህበራዊ ድህረ ገጾች፤ የመወያያ መድረኮች፤ ሚዲያዎች ለአጋራቸው – ለጀግናቸው የነበራቸው አቅርቦትና አክብሮት አብነት ነበር ማለት እችላለሁ። የአብርሽ ጹሑፎች ሆኑ ዘገባዎችን በሽሚያ ነበር የሚያወጡትና አዬር ላይ የተገባውን አክብሮት ይሰጡት የነበረው። ተመስገን። በዚህ ልጽናና።

በቀጣይም በአብርሽ የነጻነት ራህብተኛ ጹሑፎቹ ዙሪያ ውይይቶች – ትናንሽ ወርክ ሾፖችን በዬአካባቢው ፈጥሮ አጀንዳ ማደረግ የተገባ ይመስለኛል። አሁን ለምሳሌ „እኔና ሚኒሊክ“ የሚደንቅ ጹሑፍ እኮ ነው።  ስለሆነም የቆዩትንም  ከአርኬቡ እያወጡ ድጋሚ እንዲነበቡ ቤተኛ ማደረጉ መንፈሱ ከመንፈሳችን ጋር እንዲቆራኝ ይረዳል። አብሶ አሁን ፆም ስለሆነ በጸሎት መተጋጋዙም መልካም ነው። ፎቶውን በፌስ ቡኮች – በቲተር አካውንቶች ሁሉ መጠቀም ሌላው መንፈስ አራሽ መንገዶቻችን ሊሆኑ ይገባል። ጹሑፎቹ የማሰባሰብና ታሪካዊ ቋት ማበጀትም – ነገን ያሳድራል።

በማናቸውም ብሄራዊ ህዝባዊ ስበሰባዎች ሰላማዊ ሰልፎች፤  ጀግናችን አጀንዳችን፤ ጀግናችን ኮከባችን መሆኑን ከውስጣችን ሆነንበት እንታይበት ዘንድ ዝቅ ብዬ አሳስባለሁ። ለእኔ አብርሽ የአንድነቱ ልዑል ዬአሉላ አባነጋ የአደራ ማሾዬ ነው። በብዙ ጹሑፎቼ እሱን እንደ ማመሳካሪ እያደረኩኝ ሰርቼበታለሁ። አሁንም ከልቤ ውስጥ ትንሽ ሙዳያ አለች። በእሱ ውስጥ ታናሼ የሙያ አጋሬ፤ የሥነ ጥበብ ቤተኛዬ፤ እንዲሁም የነፃነት ፈላጊ ቤተሰቤ አበርሽ በክብር ለዘለአለም ይኖራል፡“ አራዊቶች የፈለገውን ነገር አስገድደው ያሰፈርሙት። የእሱ ነው ብለው ይጻፉ። ለእኛ የባንዳ መረጃ ምናችንም ነው። ይልቁንስ አብርሽን የሚገልጸው የሚያብራራው ዬሚያነበው “ የኢትዮጵያዊነት ህግ – አመክንዮ“ መሆኑ ብቻ ነው መስተውታችን ሆነ ሰነዳችን።

ማንም ሰው የአብርሽን ፍቅር ሊቀማን አይችልም። አይፈቀድም። የተከለከለ መንገድ ነው። የእሱ የተስፋ ማሳዎች ዕሸቶች ናቸው – ነገን ያበልጋሉ። እኔ አብዝቼ  እወደዋለሁ። የእሱ መፈጠረ ከብዙ ነገር ታድጎናል። ኢትዮጵያን ከበቀል ያዳና ትንሽዬ ወጣት የድህነት መንገድ ነው …..  አብርሃ ደስታ። አጋጣሚና ሁነኛ ጊዜ አግኝቶ ቢሆን ኖሮ ሰፊ ማሳን ማልማት በቻለ ነበር። ታዲያ ወ ያኔ አቅል ብሎ አልሰራለት። ፈሪ – ብዕርን መድፈር የተሳነው ልፍስፍስ።

የትግራይ ህዝብ ቢያውቀው አብርሽ እንደ መጥምቁ የኋንስ „መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስኃ ግብ“ እያለ እንደ መራው ሐዋራያዊ ተግባር ነው የፈጸመው እሱ እራሱ መልእክተ የኋንስ ነው። በሁሉም ዘርፍ ሲመዘን የአብርሽ ተልዕኮ የብዙኃኑ ፍቅርና ሰላም የተራቆተው ወያኔ ሃርነት ትግራይ እርቃነ – መንፈስ ጎጂ ጉዞ ስለመሆኑ፤ ነገን የማያሳድር ዛሬንም ያማያበርክት ስለመሆኑ ነበር እንደ ተሰጠው መክሊት ሲፈጽም የቆዬው።

ክወና – አብርሽ ሞገድ ነው – ሃቅን የታጠቀ፤ አብርሽ ነበልባል ነው – በራስ መተማመንን የዋጠ፤ አብርሽ ፍቅር ነው  የነፃነት መርህን ከልቡ የተቀበለ። አብርሽ አብነት ነው መከራን ለመቀበል የፈቀደ። ስለሆነም ስቃዩ ስቃያችን፤ መከራው መካራችን፤ ሰቆቃው ሰቆቃችን ነው። የኔ አባት ላደርክልን መልካም ነገር ሁሉ አመስግንሃለሁ። ውድድድ /////

 

የኔዎቹ እንሰነባበት – ፍቅርም – ናፍቆትም – ውስጥም ተሸለማችሁ። ቸር አገኛችሁ ዘንድም አምላኬን ጠዬኩኝ። ደህና ሰንብቱልኝ። ውድድድ

 

ጀግኖቻችን የመንፈስ ሀብሎቻችን ናቸው!

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጥር!

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

Comment

ለዲያስፖራ ኗሪ ኢትዮጵያውያን በሙሉ።

$
0
0

endaleየትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ)ለስድብና ለማዋረድ ሥራ በክፍያ ያሰማራቸው ቅጥረኛ ባንዳዎችን እንዋጋ!! ለሃገርና ለሕዝብ የቆሙ ግለሰብ ኢትዮጵያውያንን፤ ድርጅትና፤ ተቋማትን እያሳደዱ እንዲሰድቡና እንዲያዋርዱ ወያኔ አሰልጥኖ ያሰማራቸው ቅጥረኞች ሕዝብን ስይፈሩና ሳያፍሩ የባንዳነት ተግባራቸውን ቀጥለውበት ይገኛሉ። የኢትዮጵያ መንግሥት የሚል ስያሜን የያዘው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) እነዚህን ተሳዳቢ ቅጥረኞች ያሰማራው የቻይና መንግሥት የኮሚንስት ፓርቲውን አመራር የሚቃወሙና የሚተቹ ግለሰብና ተቋማትን ለማሸማቀቅ ሲል አቋቁሞት የነበረውን የ50 ሳንቲም ፓርቲ (50 Pence Party ) ዘዴን በመውረስ ሲሆን ዓላማውም ለወያኔ የማይመችን ኢትዮጵያዊ ግለሰብ፤ ማህበረሰብንና ተቋምን ሁሉ በመስደብ በማዋረድና በሃሰት ክስ በማሸማቀቅ ቅስሙን ሰብሮ ተገዢ ለማድረግ ነው። —- [ሙሉውንለማንበብእዚህላይይጫኑ]—-

ታሪክ ሲደገም! –ከኢየሩሳሌም አረአያ

$
0
0

Interview with the former Ethiopian PM Fikre Selassie Wegderes – Pt 1
የደርግ ዋና ሞተር የነበረው ፍቅረስላሴ ወግደርስን ጨምሮ በርካታ ነፍሰ በላዎች ከእስር ተፈተው መፅሐፍ በነፃነት ሲፅፉ እያየን ነው። ለምን ፃፉ የሚል ተቃውሞ የለኝም። ነገር ግን ፍቅረስላሴ ደራሲ በአሉ ግርማን ቀርጥፈው ከበሉ ቁልፍ የደርግ ባለስልጣናት ዋናው ሆኖ ሳለ አንድም ነገር ስለበዓሉ ግድያም ሆነ ስለጨፈጨፏቸው በሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ምንም ያለው ነገር የለም።

እንዳውም ደርግ ትክክለኛ እንደነበረ ሊሰብክ ሞክሮዋል። የጥቃቱ ሰለባዎች ምን እንደሚሰማቸው ለማወቅ የግድ እነሱን መሆን አይጠበቅም። እነፍቅረስላሴ ወንጀላቸውን ሸፍነው ውሸት እየፃፉ በሚኖሩባት አገር እውነት የፃፉ ሰላማዊ የአገር ልጆች ዞን 9ኝና ጋዜጠኞች፣ የተቃዋሚ አባላት እነሃብታሙና አብርሃ የመሳሰሉት በሚያሳዝን ሁኔታ በነፍቅረስላሴ ቦታ ወንጀል ተፈብርኮባቸው እስር ቤት መግባታቸው ያቃጥላል።

እነፍቅረስላሴ በበአሉ ግርማ ላይ ያነሱትን የጭካኔ በትር የአሁኑ ገዢዎች ከላይ በጠቀስኳቸውና በነእስክንድርና ርእዮት ወዘተ..ንፁሃን ላይ በተመሳሳይ የጥፋት ሰይፋቸውን መዘዋል። የደርግ ጨካኞች እነገስግስ ገ/መስቀልና እርገጤ መድበው በተባሉ ይፈፅሙ የነበረውን ዘግናኝ ስቃዮች “እቃወማለሁ፣ ታግየዋለሁ” ይል የነበረ ድርጅት ወይም ስርዓት ዛሬ እነ ታደሰ መሰረትን የመሰሉ ገራፊዎች አሰማርቶ ንፁሃን የኢትዮጵያ ልጆችን እየገረፈ ማሰቃየቱ ታሪክ እራሱን እየደገመ እንዳለ በቂ ማሳያ ነው! ገዢዎቹ ግን ማወቅ ያለባቸው ነገር እስር፣ ግርፋትና ስቃይ በጭራሽ መፍትሄ ሊሆኑ አይችሉም። ደግሞም በግዜ ሒደት እናንተና የደርግ ነፍሰ በላዎቹ እነፍቅረስላሴና ተከታዮቹ በፍርድ አደባባይ መገተራችሁ አይቀሬ ነው። .
« እናንተም እረሱ እኛም እናርሳለን
መኸር ሰብሳቢውን አብረን እናያለን» ….ወዳጄ ኮሜዲያን አብርሃም አስመላሽ (አፈሩን ገለባ ያድርግለት) ለገዢው ተላላኪዎች በምሬት የተናገረው።

የመኢአድ እና አንድነት ዉህደት ለማጨናገፍ ችኮላው ለምን? (አልዩ ተበጀ)

$
0
0

አልዩ ተበጀ

አብዛኞቻችን የአንድነት እና መኢአድ ዉህደት ተጠናቆ፣ በአዲስ መንፈስ የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄን እንቀጥላለን የሚል ተስፋና ጉጉት ነበረን። የኢትዮጵያዉያንን መተባበር የማይፈልገው ሕወሃት/ኢሕአዴግ፣ በሚቆጣጠረው ምርጫ ቦርድ አማካኝነት፣  ዉህደቱን ለማጉዋተት እንደተለመደው መስራት ጀመረ። «መኢአድ ያላሙዋላቸው ወረቀቶች አሉ» በማለት ዉህድቱን ማድረግ እንደማይችል አሳወቀ። (የተለመደው የማሰናከል እጁት ተግባር) መኢአድ ሕዝብ ያውቀው ዘንድ፣  ያለውን ሁኔታ ለማሳወቅ መግለጫ አወጣ። በጉዳዩ ላይም ከምርጫ ቦርድ ጋር ስብሰባዎች በማድረግ ከመፍታት ጀምሮ ሌሎች አማራጮችን እየፈለገ ዉህደቱን ለማሳካት በስፋት መንቀሳቀስ ጀመረ።

ከመኢአድ ጋር ዉህደት ለማድረግ ከ2 ፣ 3 አመታት በላይ ንግግሮች ሲደረጉ ነበር። አገዛዙ የደነቀረዉን ትንሽ እንቅፋት ለማስወገድ አንድ ወይንም ሁለት ሳምንት መጠበቁ ችግር የሚኖረው አይመስለኝም። ነገር ግን እንደ አንድነት ደጋፊ እጅግ በጣማ ያሳዛነኝ እና ልቤን ያደማው ክስተት ተፈጸመ።

የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው፣ ለብዙ አመት የተደከመበትን፣ የዉህዱ ሰብሳቢ ሊቀመንበር የነበሩት አቶ ሃብታሙ አያሌው የታሰሩበትን ፣ በአገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በጉጉትና በተስፋ የምንጠብቀዉን፣ ምርጫ ቦርድ ካስቀመጣት ትንሽ መሰናክል ዉጭ፣ ሁሉም ነገር ያለቀለትን፣ የመኢአድ እና የአንድነት ዉህደት እንደማይፈልጉ በመገልጽ የዉህደት አመቻች ኮሚቴን እንዳፈረሱ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

በሚኔሶታ  ቤተክርስቲያን ስሄድ ፣ የአንድነት ድጋፍ ድርጅት አስተባባሪ መሆኔን የሚያዉቁ ሲያገኙኝ ፣ አንድነት ከመኢአድ ጋር የሚያደርገውን እንቅስቅሴ እንደተደሰቱ ነበር በስፋት የሚነግሩኝ። ህዝቡ፣ ደጋፊው ስሜቱ በጣም ተጋግሎ ነበር። በአሁኑ ጊዜ የሕዝቡ መከራ በበዛበት፣ አንድነት ፓርቲ ሌሎችን እያሰባሰበ፣ የተጀመረዉን የሚሊዮኖች ንቅናቄ ይቀጥላል ብለን ስንጠብቅ፣ ያለ ምንም በቂ ምክንያት ሕወሃት/ወያኔ ትንሽ መሰናክል ስላስቀመጠ ብቻ ፣ በየክልሉ ያሉ አባላትና ደጋፊዎች እየፈለጉት፣ ዉህደቱ እንዲቆም ማድረግ በጣም፣ እጅግ በጣም ትልቅ በደል ነው።

በአንድነት እና በመኢአድ መካከል፣ ዉህደት እንዲደረግ ቁልፍ ሚና ከተጫወቱት ወገኖች መካከል አንዱ፣ በሕወሃት/ኢሕአዴግእጅ ስር ታስሮ የሚገኘው ሃብታሙ አያሌው ነው። ሃብታሙ አያሌ ከኢንጂነር ግዛቸው ጋር ብዙ ይከራከር የነበረና ኢንጂነሩም ለሚሰራው ስራ መሰናክል ሆነውበትምእንደነበረ ይታወቃል።  ከአምስት አመታት በፊት፣ ኢንጂነር ግዛቸው ከትናትናው “ዝምአንልም” የዛሬው በአብዛኛውየሰማያዊ አመራሮችአባል ከሆኑት ጋር ተመሳሳይ ችግር እንደነበረባቸው የሚታወቅ ነው:: እነዚህን በርካታ ወጣት የቀድሞ የአንድነት አመራሮችን፣   እንዲሁም እንደ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም ያሉትን ማባረራቸው ይታወቃል። ያኔ ፓርቲው ተከፋፍሎ በትግሉና በታጋዮች ሞራል ዘንድ ምን ያህል ከፍተኛ አሉታዊ ተጽእኖና ጉዳት እንዳመጣም የሚታወቅ ነው።

ኢንጂነር ግዛቸው የመኢአድ እና የአንድነት ዉህደት እንዲኖር ፍላጎት  ብዙ እንዳልነበራቸው የሚናገሩ አሁንምጥቂቶች አልነበሩም። (ዉህደቱ ከተሳካ ሊቀመንበር የመሆን እድላቸው በጣም የመነመነ በመሆኑ) የምርጫ ቦርድንም ተንኮል ሳያጡትቀርተው አደለም፣  ምርጫ ቦርድ ለአገዛዙ እንደሚሰራ እያወቁ፣ ምርጫ ቦርድ የሚያቀርባቸውን እንቅፋቶች እንደ ሰበበ በመቁጠር የዉህደት አመቻች ኮሚቴዉን ማፍረሳቸው፣  እንደ አንድ የአንድነት ደጋፊ ልረዳው የማልችለው ጉዳይ ነው። በሚሊዮኖች ዘመቻ የተነሳሳዉን፣  በሚሊዮኖች የሚቆጠር ኢትዮጵያዊ ወኔ ለማኮላሸት፣ ከትግሉና ከአገር ጥቅም ይልቅ የራሳቸውን ስልጣን ብቻ በመፈለግ ለሕዝብ ጥያቄ ንቀታቸውን በመግለጽ ትልቅ ጥፋት እያደረጉ ናቸው።

ሕዝቡ አብሮ መስራትን ይፈልጋል። የመኢአድ እና አንድነት ዉህደትን ይፈልጋል። የማይፈልጉት አምባገነኖች ብቻ ናቸው። ኢንጂነር ግዛቸውና ለርሳቸው ድምጽ የሰጡ የአንድነት የምክር ቤት አባላት፣ «ሕወሃት/ሕአዴግን የሚያስደስተዉን ነው ወይስ ህዝቡ የሚያስደስተው ማድረግ የምትፈልጉት ?» ለሚለው ጥያቄ በግልጽ ሊመልሱ ይገባል።

በኢንጂነር ግዛቸው የተወሰደው ሕወሃት/ሕአዴግን ብቻ የሚጠቅም እርምጃ በአስቸኩዋይ ተቀልብሶ ፣ አንድነት ከመኢአድ ጋር የጀመረዉን ዉህደት አጠናቆ፣ ሕወሃት/ኢሕአዴግ አፍሮ፣ ትግሉ ወደፊት መዉሰዱ ብቸኛ አማራጭ ነው።

ኢንጂነር ግዛቸው ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ችግር አላቸው። አሁን ደግሞ ከመኢአድ ጋር ከተጣሉ፣ ታዲያ እመራዋለሁ የሚሉት አንድነት ከማን ጋር ነው አብሮ የሚሰራው ? በዘር ከተደራጁ ድርጅቶች ጋር ? ወይስ ተመልሰው ወደ መድረክ በመግባት የ2002ቱን ሩጫ ሊደግሙልን ነው ?

የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች፣ እኛ በሚሊዮኖች የምንቆጠር ነን። ወሳኝ ጊዜ ላይ ነው ያለነው። ጥቂቶች ንቅናቄያችንን ወደሁዋላ ሊጎትቱ አይገባም።በመሆኑም ከመቼዉም ጊዜ በላይ ድምጻችንን ማሰማት አለብን። የአንድነት ፓርቲ የኢንጂነር ግዛቸው ብቻ ሳይሆን የሚሊዮኖች ነው። በደሴ፣ በጎንደር፣ በአርባ ምንጭ፣ በናዝሬት፣ በባህር ዳር፣ በአዳማ ..የምንኖሩ የአንድነት አባላትን የክልል አስተባባሪዎች፣ በዉጭ አገር ያለን  ድምጻችንን እናሰማ። በየአካባቢያችን ከመኢአዶች ጋር አብረን በስራ ተዋህደን እየሰራን ነው። አብረን እየታሰርን፣ አብረን እየተደበደብን  ነው። አገዛዙ ከሚያደርገው በማይተናነስ ሁኔታ ኢንጂነር ግዛቸውና ከርሳቸው ጋር የቦደኑ ጥቂቶች እንዲከፋፍሉን መፍቀድ የለብንም። አንድነታችንን ለማሳየት የምርጫ ቦርድ ወረቀት አያስፈልገንም። ትግሉን ተያይዘን መቀጠል አለብን። ትግሉ የሚሊዮኖች ንቅናቄ ነው። ትግሉ ወደፊት እንጂ ወደ ሁዋላ አይሄድም ።

 

udJ&AEUP

ፕሬስ የሌለው መንግስት ከሚኖረን መንግስት የሌለው ፕሬስ ቢኖረን እንመርጣለን

$
0
0

ዳዊት ሰሎሞን

10570542_10204024912521089_4618968976545930065_nእርግጥ ነው የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የአዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጆች ለስደት ሲዳረጉ ‹‹አዲስ ዘመንንም አዲስ ነገርንም አላነብም››በማለት ነግረውን ነበር፡፡ሌጋሲያቸውን ለማስቀጠል ቤተ መንስግስት የገቡት ሃይለማርያም በበኩላቸው በአንድ ጋዜጣዊ መግለጫ የፎርቹንን ኮሪደር እንደሚያነቡ ሲናገሩ አድምጫለሁ፡፡

የቅንጅት አመራሮች በድርድሩ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ እንደገቡ ብዛት ያለው የኢትዮ ቻናል ጋዜጣ ተጠርዞ መመልከታቸውን መናገራቸውም አይዘነጋም፡፡ገዢዎቻችን ከቀድሞዎቹ ነገስታት ባነሰ መልኩ ‹‹አዝማሪ ምን አለ?››በማለት ለመጠየቅ አለመፍቀዳቸው ትርጉሙ ንቀት ብቻ ነው፡፡ህዝቡን የሚፈልጉት እነርሱ

ሲናገሩ እንዲያደምጥ ብቻ እንጂ ሲናገር ሊሰሙት አይደለም፡፡ስለዚህ ጋዜጦችን አያነቡም፡፡የማያነቧቸውን ጋዜጦች አዘጋጆች ለስደት ሲዳረጉ ደግሞ ቅንጣት ታህል አትሰማቸውም፡፡
በጥቂት ወራት ውስጥ የተደረጉ ፕሬስን ከአገሪቱ ገጽ ለማጥፋት የተወሰዱና እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን ተመልከቱ፡፡ጋዜጠኞች ተሰባስበው ለመመስረት ቀና ደፋ ያሉለት አዲስ ማህበር እውቅና ተነፈገው፣የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና ሶስት ጋዜጠኞች ለእስር ተዳረጉ፣ትግራይን ህዝብ ፍዳ በሶሻል ሚዲያ ሲያጋልጥ የቆየው አብርሃ ደስታ ጨለማ ቤት ተወረወረ፣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አስጠናሁ ያለውን ወረቀት አቅርቦ ጋዜጦችን በኒዮ ሊበራሊስትነት ከሰሰ፣ከጫካ ጀምራ የህወሃት አፍ የነበረችው ፋና የጋዜጣ አከፋፋዮች ላይ ዘመቻ ከፈተች፣ዘመቻውን ተከትሎ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ አከፋፋዮችና ጋዜጣ አዟሪዎች ስቅይት ደረሰባቸው፣ፍትህ ሚኒስትር የህትመት ውጤቶች አሳታሚዎች ላይ ከፍተኛ የወንጀል ክስ መመስረቱን ነገረን፣ክሱ መነገሩን ተከትሎ ማተሚያ ቤቶች ጋዜጦችን የማስተናገድ ፍርሃት ወረራቸው አንዳንዶቹም በግልጽ ይህን ጋዜጣ እንዳናትም ቀጭን ትዕዛዝ ደርሶናል አሉ፣ካፌዎች በግድግዳቸው ላይ ‹‹ጋዜጣ ባለማንበብዎ እናመስግናለን እና ጋዜጣ ማንበብ አይቻልም››የሚሉ ማስታወቂያዎችን መለጠፍን ስራቸው አደረጉት ፡፡

ስደት ብርቃችን አይደለምና ይህው የተወዳጇን አዲስ ጉዳይ መጽሔት ባለቤትና አዘጋጆች ስደት ሰማን ፡፡ይህ ለኢህአዴግ ምኑ ነው?ፕሬስ የሌለው መንግስት እንዲኖረን የሚፈልግ በመሆኑ ደስታውን የሚችለውም አይመስለኝም፡፡ኮካዎች ምን ትላላችሁ?


ዐማራው በመስዋዕትነቱ ባቆያት ኢትዮጵያ ለምን ዘሩ ከምድረ-ገፅ ይጥፋ?

$
0
0

moreshየትግሬ-ወያኔ መሪዎች እነ መለሰ ዜናዊ እና ስብሐት ነጋ ወደ ደደቢት በርሃ የገቡበት ዋና ምክንያት በዐማራው ህዝብ ላይ ካላቸው ፍራቻ እና ጥላቻ በመነጨ የበቀል ስሜት ነው። ይህንኑ በፖሊሲ የተነደፈ የበቀል ስሜት ከበረሃ ጀምረው በረቀቀ መንገድ እና በተቀናጀ ሥልት በተከታታይ ተግባራዊ በማድረግ ዐማራን ከኢትዮጵያ ምድር ለማጥፋት ሌት ተቀን ተግተው በመማሰን ላይ ናቸው። ነገር ግን ዐማራው በምን በደሉ እና ኃጢያቱ፣ በደም ዋጋ አንድነቷን ጠብቆ ካኖራት ውድ እናት አገሩ ፈጽሞ ይጥፋ? ለምን?

ለዚህ መነሻ የሚሆነው የትግሬ-ወያኔን መርኅ፣ የአባሎቹንም ማንነት ጠንቅቆ ማወቅ ሲቻል ነው። የትግሬ-ወያኔ ቡድን ጎጠኛ ትግሬዎች የመሠረቱት፣ ናዚያዊ እና ፋሽስታዊ ባሕርይዎች ያሉት ድርጅት ነው። በመሆኑም ኢትዮጵያን ለማፍረስ የኢትዮጵያዊነት መሠረት እና ምንጭ የሆኑ ተቋሞችን ለማጥፋት ይንቀሣቀሣል። የትግሬ-ወያኔ ዐማራውን እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ኃይማኖትን ከሥር መሠረታቸው መንግሎ ለመጣል ፖሊሲ አውጥቶ ሌት ተቀን የጥፋት ዘመቻውን ያጧጧፈ የዐረመኔዎች እና የሠይጣን አማኞች ድርጅት ነው። የዚህ ቡድን እንቅስቃሴ በባሕርይው ከደቡብ አፍሪቃ የአፓርታይድ ሥርዓት አራማጆች እና ከጀርመኖቹ የናዚ ፓርቲ ጋር ተመሣሣይነት አለው። የጀርመኑ ናዚ ፓርቲ መርኃግብርም ሆነ የመሪዎች ጽኑ ምኞት በዘረኝነት እና በፀረ-አይሁዳዊነት የተሞላ ነበር። በትክክለኛ ቅጅም የትግሬ-ወያኔ ከመሠረቱ ሲታይ ፀረ-ዐማራ እና ፀረ-ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ኃይማኖት እንደሆነ በድርጅቱ ማኒፌስቶ ላይ በግልጽ ተቀምጧል። ስለሆነም በዛሬይቱ ስሟ በካርታ ላይ ብቻ በቀረው ኢትዮጵያ፣ ዐማራው በምን ደረጃ ለፈጽሞ ጥፋት እንደተጋለጠ ለማየት ያስችላል።   ( ሙሉውን ከዚህ ላይ ያንብቡ )

የትንሳኤ ጥሪ ለኢሕአፓ –ቁጥር 2

$
0
0

የትንሣኤ ጥሪ ነሀሴ 2006
ቁጥር 2

‘’we must accept finite disappointment, but never lose Infinite hope.”
MARTIN LUTHER KING JR

“በትግል መሞት ህይወት” ብለው የተነሱት የኢሕአፓ ልጆች አሁንም እንደትናንቱ የሕዝብን መብት፥ የሀገርን ሉአላዊነት እና ክብር ከማንኛዉም ነገር አብልጠው ይታገሉለታል። ይህንንም ሲያደርጉ በድርጂቱ በኢሕአፓ ውስጥ ያገኙትን ልምድ ለሕዝብ በማካፈል ሕዝብን የስልጣን ባለቤት ለማድረግ ነዉ።

በአሁኑ ወቅት ያለብንን ትልቅ ፈተና ለማለፍና ሕዝብን ለድል ለማብቃት በመጀመራያ ሀገርን ከሁሉም በላይ ማስቀደም፤ በውስጣችን ያለዉን መከፋፈል ማጥፋት፡የድርጅትን ህይወት ከግለሰቦች በላይ ማየት፤ ሌት ተቀን ጠንክሮ መስራትን፡ ብሎም ለራስ ጥቅም ተገዢ እለመሆንን ይጠይቃል። የኢሕአፓ መሪወችም ሆነ አባላት እንደማንኛዉም ታጋይ የድርጂታቸዉና የኢትዮዽያ ሕዝብ አገልጋዮች መሆናቸዉን በመገንዘብ ድርጂቱ በኢሕአፓነቱ ሳይሆን፣ ታጋዩ በታጋይነቱ ሳይሆን በመሪዎቹ ሥም ሲጠራና ሲክፋፈል በግዴለሽለት ከአዩት በታሪክ ፊት ይጠየቃሉ።
ውድ ወገኖቻችን በሚያዝያ ወር ትንሳዔ በሚል የመሰባሰቢያ ርእስ አንድ ጽሁፍ አውጥተን መበተናችን ይታወሳል ከዚህም ጽሁፍ ቦኋላ በአንዳንድ የዜና ማሰራጫዎች በመቅረብ የሰብስባችን አላማ ምን እንደሆነ ማብራሪያዎች ለመስጠት ሞክረናል ሆኖም አሁንም የተነሳንለትን ዓላማ እንደገና ማብራራት አስፈላጊ በመሆኑ ትንሳኤ ቁጥር ሁለትን አውጥተናል።
Tensaye
አላማችን አንድና አንድ ነው ይሄውም በኢትዬጵያ ዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶችን የሚያከብር ለህግ የሚገዛ በህዝብ ውክልና ያለው ስርአት እንዲገነባ ጠንካራ ትግል ማካሄድ ነው። ለዚህ ትግል በቆራጥነታቸው የተመሰከረላቸውና ከፍተኛ ልምድ ያላቸውን የኢህአፓ ልጆች እንደገና ማሰባሰብ ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋል ብለን እናምናለን። ቅሬታዎቻችንና እና ልዩነታቸውን አስወግደን ስርዓት በአለው መልክ በዴሞክራሲያዊ አሰራር ድርጅታችን አጠናክረን ብንወጣ ትግሉን ለውጤት ለማብቃት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
የትንሳኤ ንቅናቄ ጥረት አንድና ጠንካራ ኢህአፓ እንዲኖር ነው፤ በኢህአፓ ውስጥ የደረሰው መከፋፈል መሰረታዊ በሆኑ የመርህ ልዩነቶች የመጣ ሳይሆን ጓዶች በሰከነ መንፈስ በመግባባትና እንደቀድሞው በመተማመን ባለመወያየታቸው የተፈጠረ ችግር ነው ብለን እናምናለን። ስለዚህ መሰረታዊ ልዩነት በኢህአፓ ታጋዮች ማህል የለም እያልን አስታራቂ ሆነን መቅረብ አንችልም እኛም እራሳችን የሂደቱ አካል ነንና።

ይህ የአንድነት እንቅስቃሴ ሁሉንም የኢህአፓ ልጆች በማሰባሰብ ጠንካራ የሃገርና የህዝብ ሃይል እንዲሆኑ የማድረግ ጥረት በመሆኑ በትግሉ ውስጥ ያለፋችሁ ሃይሎች ሁሉ የኔ ጉዳይ ነው ብላችሁ ልትሳተፉበት ይገባል። ይህ ጥሪ ሀገራችን የገጠማት ችግር እንዲወገድላትና የሰላም፤ የፍትህ፤ የእኩልነትና የብልጽግና ሃገር እንድትሆን ለሚመኙ ወገኖች ሁሉ የሚቀርብ ጥሪ ነው። እንደገና እንዳንሰባሰብ ተጠናክረንም እንዳንወጣ ያልሆነ ቀለም የሚቀቡ ግለሰቦች ካሉ እባካችሁን ወደ ህሊናችሁ ተመለሱ ሁላችንም የምንኮራባቸው የተሰውት ጔዶች አጽም እና ደም ይፋረደናል እንላቸዋለን።
የኢሕአፓ መዳከምና መከፋፈል ለዘረኞችና ለጎጠኞች የልብ ልብ ሰጥቷል። ጠባቡም የወያኔ በድን ኢትዮጲያን እንደዘመነ መሳፍንት በጎሳና በጎጥ ከፋፍሎ ለማጥፋት ታጋዮችን ያስራል፡ይገድላል፡ይደበድባል፡ያሳድዳል፡ሲያስፈልግም ከጎረቤት አገሮች ጋር በመመሳጠር በማንአለብኝነት እስሮ ይወስዳል። ከዚህ በፊት ሱዳን በነበሩ ታጋዮች ላይ ያደረገውን በቅርቡ የመን ላይ በአቶ አንንዳርጋቸዉ ጽጌ ላይ አድርጎታል። የኢሕአፓ ልጆች ከተመክሮ እንደተማርነዉ አንድ ታጋይ መሰዋእትነት ሲከፍል በሺ ታጋዮች እንደሚተካ ስለምናውቅ የብዙሀን ድል ይገኛል በቆራጥ ትገል እያልን ድርጊቱንም በጥብቅ እናወግዛለን። እንዲያዉ ነገርን ነገር ያነሰዋልና በአረመኔዉ የደርግ መንግስት የታጋይ ጓዶቻችን እሬሳ መንገድ ላይ ዘርረዉ የዝንብ መጫወቻ ያደረጉትን ታላቁን ታጋይ ዮወሴፍ አዳነን አይኑን እየሸነቆሩ ቁዋንጃዉን እየቆረጡ የገደሉትን የፋሺስቱን ደርግ አባሎች ህይወት ወያኔ ሲያተርፍ ህይወታቸዉን በሙሉ ለህዝብ ሥልጣን ባለቤትነት እና ለዴሞክራሲ ሲታገሉ ሲወድቁ ሲነሱ የቆዩት ታጋዮች እነፀጋዬ ገ/መድህንን(ደብተራዉ)፡ እነ አበራሺ በርታን፡ እነ ስጦታዉ ሁሴንን ,,,ወዘተ የት እንዳደረሳቸዉ እስከ አሁን እንኩዋን አናዉቅም። ወያኔና የወያኔ መሪወችም ይህን ሚስጥር እንደያዙ አንዳንዶቹ እየሞቱ ቢሆንም ቀሪዎቹ ነገ በህዝብና በህግ ፊት ይጠየቁበታል።

አዎን የኢሕአፓ ጀግኖች ሙሾ ተወርዶላቸዉ፡ ደረት ተመቶላቸዉ፡ የስርዓተ ቀብር ተደርጎላቸዉ ባያዉቅም ያሞራ ቀለብ የዝንብ መጫወቻ ቢሆኑም፡ሰልፋቸዉ ከህዝብ ጋር ነዉና ሕዝብ ሲያሸንፍ ያን ግዜ ያን ቀን ታሪካቸዉ ይዘከራል። አሁንም ቢሆን ቀሪዉና ቀጣዩ ትዉልድ ሰንደቃቸዉን አንስቶ፡ መፈክራቸዉን አንግቦ በመታገል ከዓለሙት እና ከተሰዉለት ግብ ይደርሳል። በሕዝብ ሀይል የሚያምን ሁሉ ይህን አይጠራጠርም።ለዚህ ነዉ ትንሥኤ ኑ በቤታችን እንሰባሰብ ኑ እንታገል የትግላችን ጉዞ እንደ ኩሬ ዉሀ አንድ ቦታ ላይ ተገድቦ መንቀሳቀስ አልቻለምና መፍትሄ እንፈልግለት እያለ ጥሪውን የሚያቀርብ።
መሪነት ታላቅ ሀላፊነት እንደመሆኑ መጠን እንደ ሺልማት የሚሰጥ ገፀ በረከት አይደለም።ታግሎ ማታገልን ቀድሞ መገኛትን ከቂም ነጻ ሆኖ አርቆ አስተዋይነትን ይጠይቃል። “ከሊቀመንበር መንግሥቱ ጋር ወደፌት” ያሉትን ወይም በሙት መለስ “ራዕይ” የሚመሩትን ስናወግዝ ወደ ራሳችንም ዘወር ብለን እራሳችን ልንፈትሽ ይገባል። ከዚህ አንጻር በየትኛውም እርከን የታገላችሁና በመታገል ላይ ያላችሁ ጔዶች ሃላፊነታችሁን በአግባቡ እንድትወጡ አጥብቀን እንጠይቃለን።

ከዚህም ባሻገር የትንሥኤ ቡድን ህልም ኢሕአፓን አጠናክሮ ማውጣት ብቻ ሳይሆን ድርጂቱ እሱን ከመሳሰሉ ጠንካራ ድርጂቶች ጋር በመቀናጀት የጋራ ትግል እንዲያደርግም ይገፋፋል።ወቅቱ በጋራ መሥራትን አጥብቆ ይጠይቃልና።ሕዝቡም “ተባበሩ ወይም ተሰባበሩ” የሚለውን ጥሪ አሁንም እያቀረበ ነው፤ ለሕዝብ የሚሰራ ሁሉ የሕዝብን ድምፅ መስማት አለበት።በህዝብ ያልታቀፈና የሕዝብን ቃል የማያከብር ድርጂት ብቻዉን እነደቆመ ግንድ ነዉ። የሳለ መጥረቢያ በቀላሉ ይቆርጠዋል ለሕዝብ ለመቆም የሕዝብን ድምፅ መስማት፡የሕዝብን ፍላጎት ማወቅ፡ ያንንም ተግባራዊ ማድረግን ይጠይቃል። ያለሕዝብ ድጋፍ ድርጂት ሊኖር አይችልም።ድጋፉን የሚሰጥ ሕዝብ ድምፁን የማሰማት መብት አለዉ የድርጂት መሪወች ይህንን ተገንዝበዉ መተባባር አለባቸዉ እልህ ግትርነትና በድርጅት ውስጥ ለራስ ከፍተኛ ቦታ መስጠት የተከፈለውን መስዋእትነት ያበላሻል። ልዩነትን በነጻ መድረክ ተወያይቶ መፍታት የግድ ባህልና የውዴታ ግዴታ መሆን አለበት። አባላትም መሪዎቻቸውን መከታተል የድርጅታቸውን ፖሊሲ መመርመር ልዩነትን ከማራገብ ይልቅ አንድነትን ማጠናከር ይኖርባቸዋል። በዚህ ዙሪያ ያሉትን ድክመቶቻችን ካስወገድን ኢህአፓን በማጠናከር ተባብሮ በመስራት የሕዝብን ትግል ከግብ ማድስ እንችላለን ብለን እናምናለን።

ለዚህም የተቀደሰ አላማ ኢህአፓ የከፈለውን መስዋእትነት የምናከብር በኢሕአፓ ዙሪያ እንደገና ለመሰባሰብና ኢህአፓን አጠናክሮ እንደቀድሞዉ ቆራጥና የተባበረ ትግል ለማካሄድ ለምትፈልጉ ሁሉ የትንሥኤ ቡድን በድጋሚ ጥሪዉን ያቀርባል። ይህንም እንቅስቃሴ ተካፋይ ለመሆን የምትፈልጉ ሁሉ በነዚህ ኢሜል አድራሻወች ልትገናኙን ትችላላችሁ

TINSAE64@GMAIL.COM
ስለ ሀገር ፍቅራችሁ እና ቅን አመለካከታችሁ አስቀድመን እናመሰግናለን
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

2007ን ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ሲባል እስከ ምርጫ ወይስ እስከ ዴሞክራሲያዊ መንግስት (ዳንኤል ተፈራ)

$
0
0

ዳንኤል ተፈራ

ዳንኤል ተፈራ — የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ

ዳንኤል ተፈራ — የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ

በጣም በቅርቡ አንድ ስላልነገርኩት ስሙን የማልጠቅሰው ጉምቱ የሚባል ጋዜጠኛ ወዳጄና ሌላ አንድ ጎልማሳ ጋር ኢ-ወጋዊ በሆነ መንገድ ስለተቃዋሚ ጎራው ማውጋት ይዘናል፡፡ የጨዋታችን መነሻ ደግሞ አንድነትና መኢአድ ከብዙ ውጣ ውረድና ድርድር በኋላ ከፍፃሜ ለማድረስ ደፋ ቀና እያሉበት ያለው ውህደት ነው፡፡ የተቃውሞ ፖለቲካውን በቅርበት እንደሚከታተሉ አንዳንድ ግለሰቦች አስተያየት ‹‹ውህደቱ መሳካት አዎንታዊ ጎን ቢኖረውም ዘግይቷል፡፡ በዚህ ጊዜ የውህደቱ ጣጣ አልቆ፣ የሚተባበሩት ተባብረው ወደ ሰፊ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚገቡበት ነበር›› ይላሉ፡፡ የውህደቱ መሳካት ጥሩ ሆኖ ውህደቱም ሆነ ትብብሩ ዘለቄታ ላለው ዴሞክራሲያዊ ለውጥ ለማምጣት ወይስ ምርጫ ስለደረሰ ብቻ? የሚል ጥያቄ አንስቶ መመለስ ተገቢ ነው፡፡

ጎልማሳው ሰው ቀበል አድርጎ ለተቃዋሚው ጎራ ቅርበት አለው ብሎ ስላመነ ይመስለኛል አይኖቹን እንደ ቆመህ ጠብቀኝ መሳሪያ ፊቴ ላይ ወድሮ ‹‹በተቃውሞ ጎራው በኩል ተቀራርቦ፣ ተባብሮና ተዋህዶ የመስራቱ ነገር እምብዛም ባለመለመዱ ወይም እስካሁን ባለመሳካቱ ይመስለኛል ውህደት እንዳንድ አደረጃጀትን የሚያጠነክር የፖለቲካ ስራ ሳይሆን እንደግብ ይታያል፡፡ ከፖለቲካ ጠቀሜታ አንፃር ሳይሆን ከምርጫ፣ ከግል ጥቅምና ዝና አንፃር ይታል፡፡ ውህደት እንዳንድ የለውጥ ማምጫ ስትራቴጅ ባለመታየቱ በህዝቡ ዘንድ በጉጉት የሚጠበቅ ነው፡፡ መጠላለፍና ሴራ በብርቱ የሚያጠቃው የፖለቲካ ባህላችን ግን ‹‹እኔ ብቻ አዋቂ፣ እኔ ብቻ ንጉስ›› ከሚል ጨፍላቂ ሰርዓት ጋር ሲደመር ግራ ማጋባቱ ላይገርም ይችላል፡፡ በአጠቃላም የተቃውሞ ጎራውን ከአሮጌና ምርጫን ግብ ካደረገ አስተሳሰብ አላቅቀው የራሱ መነሻና መድረሻ ያለው ስትራቴጅ የሚነድፉ መሪዎች ያስፈልጉታል›› አለ፡፡

ጎልማሳው ሁለታችንም ዝም ብለን የልቋጨውን ሀሳብ እንዲጨርስ እየጠበቅነው እንደሆነ ሲረዳ፡- ‹‹ለነገሩ መምራት የሚችሉ ግለሰቦች ለመምጣት ቢሞክሩም በጥርጣሬና በሴራ ፖለቲካ ተስተካካይ የሌላቸው ግለሰቦች እንዲርቁ ያደርጓቸዋል፡፡ ከነሱ ተረፉትን ደግሞ ኢህአዴግ ‹‹አሸባሪ›› ብሎ ያስራል፡፡ ስለዚህ ውህደት ብቻ ሳይሆን ውህደቱን የሚመራ ጥብቅ መሪ ያስፈልጋል፡፡ ምርጫ ሞክሮ የሚሄድ ሳይሆን ከምርጫ ባሻገርም ለውጥ የሚመጣበትን መንገድ የሚቀይስ ብርቱ ሰው›› በማለት ሃሳቡን ጠቀለለ፡፡

ያነሳው ሃሳብ ጥቅል ቢሁንም ለውይይታችን ማጠናከሪያ መሆኑ አልቀረም፡፡ የጨዋታችንም ጭብጥ ሰፋና የተለያዩ ጋዜጦች ላይ ስለተቃዋሚው የሚፃፉትን አሉታዊ ትንታኔዎችን እያነሳን ነበር፡፡ የተቃዋሚ ጎራው መተቸት አለበት ወይስ የለበትም፤ ትችቱ ምን አይነት ቢሆን ለሀገር ይጠቅማል፤ ገዥው ፓርቲ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ምን አይነት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል፤ ለምን? የሚሉ ጉዳዮችም ተነሱ፡፡ መቼስ ተቃዋሚው መተቸት የለበትም የሚል ድምዳሜ ላይ መድረስ አይቻልም፡፡ ኢህአዴግ ካቴና ይዞ የሚመጣው ‹‹ለምን ነካችሁኝ፤ ለምን ተቻችሁኝ›› ብሎ አይደል እንዴ? ታዲያ እንዴት አሁን ካለው ስርዓት የተሻለ ሀገር መምራት እችላለሁ ብሎ እየታገለ ያለውን ተቃዋሚ አይነካ ማለት ይቻላል? እያልን ስናነሳ ጋዜጠኛው ወዳጄ የተቃውሞ ጎራ አሁን ባለበት አቋም የሚያስፈልገው ገንቢ ትችት ነው የሚል ነገር ዱብ አደረገ፡፡ በድማሜ ውስጥ ሆኜ ‹‹ለምን?›› የምትል ቤሳ ጥያቄ ማቅረቤ አልቀረም፡፡ እሱም እንዲህ መለሰልኝ፡፡

‹‹አየህ ተቃዋሚው ባጠቃላይ ከአፈጣጠሩ በርካታ ችግሮች ያሉበት ነው፡፡ ኢህአዴግ የሚፈጥረው ችግር ደግሞ ብዙ ነው፡፡ ለባለፉት 23 ዓመታት ተቃዋሚው በተበታተነ አሰላለፍ፣ ምርጫን ብቻ ግብ አድርጎ ቆይቷል፡፡ ይህ አሰላለፍም ዘላቂነት ላለው ድልና የማይናድ የተቃዋሚ ግንብ ለመገንባት አላስቻለውም፡፡ ግልፅ ራዕይና ስትራቴጅ በማስቀመጥ፣ ተተኪ ፖለቲከኞችን በማፍራትና በውስጡ ተሰግስገው እንደ አሜባ የሚራቡትን ሰርጎ ገቦች ማጥራት አልቻለም፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ኢህአዴግ ‹‹ተቃዋሚዎች እግር እስከሚያወጡ መጠበቅ ተገቢ አይደለም›› በሚለው የተበላሸ አመለካት የተነሳ ከፍተኛ ወጭ መድቦ ተቃዋሚ ጎራውን በአይነ ቁራኛ ይጠብቃል፡፡ ከተራ ስም ማጥፋትና በውስጥ ክፍፍል ለመፍጥር ከመስራት ጀምሮ እስከ ‹‹ሽብርተኛ›› ብሎ እስከማሰር የደረሰ መዋቅር ዘርግቷል፡፡ ስለዚህ አሁን መሆን ያለበት ተቃዋሚውን ሃይል መተቸት ሳይሆን  መደገፍ ነው፡፡ በህጋዊ መንገድ ተመዝግቦ፣ በሰላማዊ ትግል አምኖ እየታገለ ያለን ሃይል እንደ ጠላት የሚቆጥር መንግስት ባለበት ሀገር፤ ተቃዋሚው የስብሰባ አዳራሽ፣ የሚከራይ ቢሮ ለማግኘት በሚቸገርበት ሁኔታ፤ አባሎቹን እየተከታሉ ‹‹ወይ ከስራህ አሊያም ከተቃውሞህ አንዱን ምረጥ›› በሚባልበት ስርዓት ውስጥ ቀዳሚው ነገር ተቃዋሚውን መተቸት ሳይሆን ተቃዋሚው እግር እንዲያወጣ ማገዝ ነው፡፡ እግር አውጥቶ የቡጢ ሚዛኑ ሲስተካከል ግን ገንቢ ትችት ብቻ ሳይሆን አሁን ኢህአዴግ በሚተችበት ደረጃ መተቸት ነው›› የሚል ትንሽ ትንታኔ አቀረበ፡፡

በርግጥ በጋዜጠኛው ወዳጄ በጎ ሃሳብ የሚስማሙም የማይስማሙም ይኖራሉ፡፡ አንዳንዶች መጠንከርም ሆነ መልፈስፈስ የተቃዋሚው የራሱ ምርጫ ነው የሚሉ አጋጥመውኛል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ተቃዋሚው ጠንካራም ሆነ የተልፈሰፈሰ እንዲሆን የሚያደርገው ህዝቡ ሊሆን ይገባል የሚሉም አሉ፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ የሚቋቋመው ለህዝብና ለሀገር አገለግላለሁ ተብሎ ነው ስለዚህ ባለድርሻው ህዝብ ከሆነ ጠንካራ ለሚለው ድጋፍ በመስጠትና በአጉል አቅጣጫ ለሚነጉደው ትብብር በመንፈግ ለተቃዋሚው አቅም ሊፈጥር ይችላል፡፡ እኔም አዳምጨ ሳበቃ ይህንን ሃሳብ ተመርኩዤ የራሴን ምልከታ ለመሰንዘር ወደድሁ፡፡

‹‹ጋንግስተሪዝም››

አስቀድሞ ትውስ ያለኝ ጋንግስተሪዝም ነው፡፡ ለሀሳቤ መነሻ ሆነኝ ጋዜጠኛ ዮናስ በላይ በቅርቡ ያሳተመው ‹‹የትግራይ ሕዝብ፤ ወያኔዎቹና ሽፍቶቹ›› የሚለው መፅሀፍ ነው፡፡በመፅሐፉ በ1993 ህወሃት ለሁለት ስትሰነጠቅ መሰረታዊ ልዩነቶች ምን እንደነበሩ ስብሃትን ጠይቋቸው ሁለት ነገር አስቀምጠዋል፡፡ በተለይም በኤርትራ ጉዳይ አንደኛው እነ ስየ መለስን ‹‹ተንበርካኪ ሆናችኋል›› የሚል ሲሆን የነ መለስ ቡድን በበኩሉ በመልሶ ማጥቃት ተንበርካኪነትን ባለመቀበል ዴሞክራሲያዊ አመለካከት ጠፍቷል ‹‹ጋንግስተሪዝም›› እያደገ ነው በማለት ለመመከት ተገድደዋል፡፡ የፖለቲካ ጉዳይ ስለሆነ እንጅ እነ መለስ ለዴሞክራሲ ተጨንቀው እንዳልሆነ አሁን ያለው ተጨባጭ ሁኔታ ምስክር ነው፡፡ ጋንግስተሪዝም በተገላቢጦሽ በክፍፍሉ አሸናፊ ሆኖ የወጣው የነ መለስ ቡድን መለያ መሆኑ ፈገግ ያሰኛል፡፡

ጋንግስተሪዝም (ቦዘኔነት) ዋናው የተቃዋሚ ጎራ ችግርም ነው፡፡ ቦዘኔዎች ዋና ተግባራቸው ስራ መስራት አይደለም የሚሰሩትን እየተተከተሉ ማጥቃት እንጅ፡፡ አሁን ያለው ወጣት ትውልድ ግን ከጋንግስተሪዝም ይልቅ ዴሞክራሲ ልዩ መለያው እንደሆነ መመስከር ይገባኛል፡፡ ጋንግስተሪዝም በዋናነት የአባቶቻችን ትውልድ መለያ ነው ብሎ መከራከር ይቻላል፡፡ የሃሳብ ልዩነትን በውይይት ከመፍታት ይልቅ ማጥፋት የተለመደ ነው፡፡ በተቃዋሚው ጎራም አባራሪና ተባራሪ አለ፡፡ ‹‹የተቃዋሚዎች እናት አንድ ናት›› እንዲል አስራት አብርሃም በቅርቡ እንኳን ታዋቂውን ፀሃፊና ፖለቲከኛ አስገደንና ሌሎችን አረና አባሯል፡፡ አረና ወደ ማባረሩ የገባው ሌላው በአጭር ጊዜ በፖለቲካ ስራውና በሚያቀርባቸው ፅሁፎቹ እውቅና ያተረፈው አብርሃ ደስታ ከታሰረ በኋላ ነው፡፡ ታዲያ የተያዘው ማጠናከር ወይስ ማላላት? ፕሮፌሰር እንዳሉት የስላሴዎች እርግማን ይሆንን? አደህይቶ መግዛት፤ አጎሳቁሎ ተስፋ ማሳጣት፤ ባዶ ማድረግ፡፡ ጋንግስተሪዝም፡፡ ይሄ የትውልድ ውልቃት መጠገን አለበት፡፡ ቅድሚያ ለውጥ ፈላጊነት ጋንግስተሪዝምን ማሸነፍ አለበት፡፡

በመቀጠል የተቃውሞ ጎራው ከተከላካይነትና ከተጠቂነት ወደ አጥቂነት የሚሸጋግርበትን የፖለቲካ ስትራቴጂ የሚነድፍ መሪ ያፈልገዋል፡፡ ትግሉን ከምርጫ ፖለቲካ በላይ አሻግሮ የሚመለከትና የኢህአዴጋውያኑን የጠቅላይ አምባገነንነት አባዜ ተረድቶ የመስበሪያ ስልት የሚቀይስ የፖለቲካ ማሃንዲስ መፍጠር ይገባል፡፡ የተቃውሞ ጎራው እስካሁን በመጣበት መንገድ ከፍተኛ መስዋዕትነት ተከፍሎበታል፡፡ አሁንም ስለለውጥ ከፍተኛ ዋጋ ዕየተከፈለ ነው፡፡ ነገ ትልቅ መሪ የሚሆኑ የኢትዮጵያችን ተስፋዎች ጨለማ ክፍል ውስጥ ተጥለዋል፡፡ እነ አንዷለም አራጌ፣ ኦልባ፣ በቀለ ገርባ፣ ሀብታሙ አያሌው፣ ናትናኤል መኮንን፣ የሽዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ዳንኤል ሺበሺና ሌሎች በፖለቲካ እምነታቸው ብቻ ወደ ጨለማ ክፍል የተወሰዱ ዜጎች የከፈሉት ዋጋ ፍሬው መታየት አለበት፡፡ ይህ ሊሆን የሚችለው ደግሞ ምርጫ ስለደረሰ ብቻ ሱፋቸውን አሳምረውና ጫማቸውን ወልውለው ከተቻለ ፓርላማ፤ ካልተቻለ ደግሞ ሌላ አምስት አመት እስከሚመጣ እቤታቸው በሚቀመጡ ፖለቲከኞች አይደለም፡፡ ለውጡ ሊመጣ የሚችለው ያለ ፋታ በሚሰሩ ለውጥ ፈላጊ ሃይሎች እንጅ፡፡

ጋንግስተሪዝምን (ቦዘኔነትን) አሸንፎ ምርጫ ካለና በአግባቡ ከተጠቀሙበት የለውጥ ማምጫ መሳሪያ ነው፡፡ አሁን ያለው ገዥ ፓርቲ ፍትሃዊ ምርጫ ለማካሄድ ቁርጠኝነቱ አለው ተብሎ አይገመትም፡፡ ነገርግን የተቃዋሚው ስራስ ምን መሆን አለበት? አፋኝነቱን ከመተንተን ያለፈ የማስገደድ ሃይል ያለው ጡንቻ ያስፈልገዋል፡፡ በምርጫው መሳተፍ ይገባል ወይስ አይገባም፤ ብንሳተፍ ምን ምቹ ሁኔታዎች አሉ፤ ምን ተግዳሮቶች አሉ፤ በአማካይ ስንት ወንበር አሸንፈን ስልጣን መያዝ እንችላለን፤ ምርጫው ኢፍትሃዊ እንዳይሆን ምን ምን ርምጃዎች መወሰድ አለባቸው፤ ህዝቡን የማንቂያ ስትራቴጅዎች፣ ህዝባዊ ንቅናቄ የመፍጠሪያ ስልቶች፣ የችግር አፈታት ስልቶችና የታሰሩ አመራሮች ለምርጫው ያላቸው አጋርነት መፈተሽ ይገባል፡፡

በአመራር ደረጃም በምርጫው ተቃዋሚ ጎራው ሞካሪና አዳማቂ ሆኖ ሳይሆን አሸናፊ ሆኖ የሚወጣበትን ስትራቴጅ የሚነድፉ፤ የተነደፈውን ስልት ወደ ውጤት የሚቀይሩ የኦፕሬሽን ሰዎች፤ ይህንን የሚደግፉና የሚያሰርፁ አባላት በብዛት ያስፈልጋሉ፡፡ የዚህ ፅሁፍ አቅራቢዎ አንደታዘበው ግን በተቃውሞ ጎራው ስለ ግልፅ የማሸነፊያ ስትራቴጅና ስለ ስልት እምብዛም አይወራም፡፡ ሕዝቡ ካለበት የኑሮ ጫና፣ የነፃነት እጦትና የስርዓቱ ሹማምንት ከሚያደርሱበት ምሬት አንፃር የተቃውሞ ጎራውን በስፋት ይደግፋልና ይመርጣል የሚለውን ግምት በተግባር መፈተሽና በአግባቡ የዚህን የተገፋ ህዝብ ይሁንታ የሚያገኙበትን ተክለ ቁመና መፍጠር ያስፈልጋል፡፡

ዞሮ ዞሮ ከላይ ለመግለፅ በሞከርኩት መንገድ የተቃውሞ ጎራው ከውህደት ባሻገር ከአመራር አንፃርና አጠቃላይ ትግሉ ያለበትን ነባራዊ ሁናቴ ፈትሾ፤ የሚፈለገውን ቁርጠኝነት አሳይቶ ለውጥ ከማምጣት አንፃር መሰራት እንዳበት አንስተን የኢ-ወጋዊ ውይይታችን ማጠቃለያ የሆነው በሚቀጥለው ዓመት ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቀው ሃገራቀፍ ምርጫ ነበር፡፡ (በነገራችን ላይ ምርጫ፣ ምርጫ ስል ምርጫ አለ እንዴ! በ2002 ምርጫ ተደርጎ ነበር እንዴ! በማለት ታማኝነትን ያተረፈ ምርጫ ካልተደረገ እንደተደረገ አይቆጠርም በማለት ጠንከር ያለ መከራከሪያ የሚያቀርቡ እንዳሉ ሳይዘነጋ ማለት ነው) በአንፃራዊነት ጠንካራ የሚባሉ ፓርቲዎች 2007ን እንዴትና ለምን ግብ ሊጠቀሙበት እያሰቡ ነው? ምርጫውን ለመሞከር ወይስ ዘለቄታዊ ጠቀሜታ ላለው ዴሞክራሲያዊ ለውጥ ለማምጣት? የሚለው ዋና ጥያቄ ነው፡፡

የምርጫ ጊዜ ወፎች

ከጋንግስተሪዝም ለጥቆ የሚመጣው የምርጫ ግርግር ፈጣሪው ነው፡፡ ስለ ሰላማዊ ትግል ስናስብ ስለ ውጤትም ማሰብ ይገባል፡፡ ኢህአዴግን ብቻ ሳይሆን እንደ መስቀል ወፍ ምርጫና የምርጫ ወሬ ሲሰማ የሚሉትን የምርጫ ጊዜ ወፎች መታገል ይገባል፡፡ የነዚህ ወፎች ግብ ከላይ እንደገለፅኩት ዘለቄታዊ ለውጥ በማምጣት የሚፈለገውን ዴሞክራሲ መገንባት አይደለም፡፡ ዘላቂነት ያለው የለውጥ ስሜትም ሆነ ስትራቴጅ ስለሌላቸው በምርጫ ጊዜ ብቻ ብቅ ይሉና ‹‹ሲያቃጥል በማንኪያ ከበረደ በእጅ›› የምትል የጮሌ ስትራቴጅ በመያዝ ምርቻ ላይ ለመሳተፍ የሚፈልጉት ናቸው፡፡ እነዚህ ሃይሎች ካራባት በማሳመር ምርጫ ማሸነፍ ይቻል ይመስል ‹‹የ2007ን ምርጫማ መሞከር አለብን›› ይላሉ፡፡ መሞከር ብሎ ትግል፡፡ ሰው የሚወዳደረው ለመሞከር ሳይሆን ለማሸነፍ ነው፡፡ የምርጫ ጊዜ ወፎች ግን ‹‹ኸረ እባካችሁ ህዝብና ሃገር መሞከሪያ አይደለም፤ ኢህአዴግ በዚህ ጭቁን ህዝብ ላይ የሞከረበት ይበቃል፤ ዘላቂነት ያለው ስትራቴጅና ራዕይ ካላችሁ ወዲህ በሉ›› ሲባሉ ያኮርፋሉ፡፡ ይፈርጃሉ፡፡ ያችኑ የሚውቋትን የሴራ ጨዋታ ከች ያደርጓታል፡፡ ያ የፈረደበት ምርጫ 97 ይጠቀስና ‹‹ስንት ዋጋ ከፍለን፤ ደማችን ፈስሶ አጥንታችን ተከስክሶ…›› የምትል ‹ፉከራ› በማምጣት ጉዞ ወደ ምርጫ ሙከራ ይሆናል፡፡

ዋናው ቁምነገር የተከፈለውን ዋጋ ለማሳነስ አይደለም፡፡ በ97 ደግሞ የስርዓቱን አስከፊ ገፈት ያልቀመሰና ዋጋ ያልከፈለ የለም፡፡ ዳሩ ግን ከታሪክ መማር እንጅ በታሪክ መኖር አይቻልም፡፡ በታሪክ መኩራት እንጅ በታሪክ ማሸነፍ አይቻልም፡፡ ማሸነፍ የሚቻለው ዛሬ ላይ አቅዶ፣ እቅዱን ወደ ተግባር ለውጦ፣ ህዝቡን አሳትፎ መጓዝ ሲቻል ነው፡፡

አንድነትና መኢአድ ጀምረውታል፡፡ ቢያንስ የሁለቱን ትላልቅ ፓርቲዎች ሃይል በአንድ መስመር ማስገባት የሚቻልበት ታሪካዊ ስራ ነው፡፡ ግን በቂ አይደለም፡፡ አሁንም ዳርላይ የቆሙ ፓርቲዎች አሉ፡፡ የተናጠሉ ጉዞ አያዋጣም እየተባለ ነው፡፡ 2007ን በአግባቡ ለመጠቀም የተሰባሰበ አንድ የተቃውሞ ሃይል መፍጠር አንዱ ነው፡፡ ለዚህ ትልቅ የተቃውሞ ሃይል የሚመጥንና ወደ ፊት የሚያራምድ አመራርም ያፈልገዋል፡፡ የምርጫ ጊዜ ወፎች ምርጫ መግባትን እንደ ግብ ስለሚያዩ ከተቻለ ትግሉ ምርጫ የመሞከር ሳይሆን ትግሉ እየተካሄደ ያለው ለውጥ ለማምጣትና ለትልቋ ሀገራችን የሚመጥን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የማስፈን ስለሆነ ወደ ትክክለኛ መስመር እንዲገቡ ማድረግ ነው፡፡ አልገባም ካሉ እነሱንም መታገል ነው፡፡

የዚህ ፅሁፍ አቅራቢዎ በድጋሚ እንደታዘበው አሁን በተቃውሞ ፖለቲካው ውስጥ ሁለት አይነት የውስጥ ትግል እየተካሄደ ነው፡፡ ይሄ ትግል የሚካሄደው በለውጥ ፈላጊ ሃይሎችና (ይሄ በብዛት የወጣቱን ቀልብ የሳበ ይመስላል) በቀደመው መንገድ ማዝገም በሚፈገልጉ፣ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ከእኛ በላይ ላሳር ብለው የሚምኑ፤ ነገርግን በተግባር ውጤት ያላስመዘገቡ ሃሎች መካል ነው፡፡ በዚህ መልኩ መታገል መብት ነው፡፡ ፖለቲካ ውስጥ የውስጥ ትግልና የውጭ ትግል መኖሩ የተለመደ ነው፡፡ የሚዳኘው ግን አባላትና ህዝቡ ይሆናል፡፡

የግል ይዞታነት

በመጨረሻ ማንሳት የምፈልገው ትግሉን ፍሬያማ ለማድረግ እንቅፋት እንደሆነ የሚታመነው የግል ዞታ አመለካከት ነው፡፡ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ከምርጫ ባለፈ የምንመለከት ከሆነ በተቃዋሚ ጎራው የሚታየውን ፓርቲን እንደግል ንብረት የመመልከት ዝንባሌ ማጥራት ያስፈልጋል፡፡ በትግል ውስጥ ዋጋ መክፈል ማለት ፓርቲውን የግል ንብረት ማድረግ ማለት አይደለም፡፡ ከላይ እንደጠቀስኩት ፓርቲ የሚቋቋመው ለህዝብና ለሀገር የሚጠቅም ርዕዮተ ዓለምና የማስፈፀሚያ ስልት ይዞ እሱን ተግባራዊ ለማድረግ እንጅ የግል ዝናና ሞገስ ለማግኘት አይደለም፡፡

እኔ አይነኬ ነኝ የሚሉ እንዳንድ ግለሰቦች ‹‹እኔ አንደዚህ፣ እንደዚህ አድርጌ በመሰረትኩት ፓርቲ…›› የምትል መከራከሪያ ሲያቀርቡ ይሰማል፡፡ ፓርቲ ውስጥና ፖለቲካ ውስጥ ‹‹እኔ›› የምትል የግለኝነት ሃሳብ መነሳት ከጀመረች ህዝብና ሀገር ተዘንግቷል ማት ነው፡፡ ፓርቲን እንደ ግል ዞታ መመልከት የሚመጣው እኔ ከሚል ያልተባረከ ሃሳብ ነው፡፡ ማንም ሰው ማወቅ የሚገባው ወደ ኢትዮጵያ የተቃውሞ ፖለቲካ የሚመጣው ሊሰጥ እንጅ ሊቀበል አይደለም፡፡ ፖለቲካ ውስጥ ገብቶ መስጠት ሳይሆን መቀበል የሚፈልግ ካለ ወደ ኢህአዴግ ዘንድ ቢሄድ ውጤታማ ይሆናል፡፡ ተቃዋሚው ጎራ ያለው ግን መስጠት ብቻ ነው – ያውም ክቡር የሆነውንና የመጨረሻ ውዱን ህይወት፡፡ ስለዚህ በተቃውሞ ጎራ ያለውን የግል ይዞታ አመለካከት መታገል ወደሚፈለገው የለውጥ ግብ ያደርሳል፡፡

ለማጠቃለልም አሁንም ከፊት ለፊታችን የሚጠብቀን ሀገራቀፍ ምርጫ አለ፡፡ በኢህአዴግ በኩል ግልፅ የሆነ  የመጠቅለል አካሄድ እየታየ ነው፡፡ ይህንን የአፈና አካሄድ መስበር የሚቻለው የምርጫ ግርግር ውስጥ በመግባት ወይም ለመሳተፍ በመጓጓት ብቻ አይደለም፡፡ በቅድሚያ ምርጫ እንዲኖር መታገል ያስፈልጋል፡፡ 2007ን ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ መጠቀም የሚቻለው እስከ ምርጫ ብቻ በማሰብ አይደለም፡፡ ከምርጫ ባሻገርም ተቃውሞ ጎራው ላይ አስተማማኝ መሰረት ጥሎ ዴሞክራሲያዊ መንግስት መመስረቱም ሊታሰብበት ይገባል፡፡ ሁለንተናዊ ችግሮችን ፈትሾ፣ አካዶችን በግልፅ ተችቶ መድረሻ ጎል ማስቀመጥ፡፡ አዎ ጊዜው እየሮጠ ነው፡፡ ህዝቡም የተጫነበት ቀንበር ከብዶታል፡፡ ስለዚህ በዚህ ልክ መሮጥ ያስፈልጋል፡፡ ጎበዝ እንሩጥ፡፡

“ያልተሄደበት መንገድ” –ሊነበብ የሚገባው ድንቅ መጽሐፍ! (ነፃነት ዘለቀ)

$
0
0

ነፃነት ዘለቀ
freeandualemaragie.org

ይህን የአንዱአለም አራጌን በራሱ አገላለጽ ከጠባቧ የቃሊቲ እስር ቤት የተጻፈ ግሩም መጽሐፍ ሳነብ የተሰማኝን ስሜት ባጭሩ ለመግለጽ እንጂ ሥነ ጽሑፋዊ ደንብ የተከተለ ሂስ ወይም የመጽሐፍ ግምገማ ለመስጠት አለመነሳቴን መግለጽ እፈልጋለሁ – መሆኑን እንዴት ከረማችሁ?

ከሁሉ በፊት ግን ከሰሞነኛ ጉዳዮች መካከል ቂላቂሉ ወያኔ በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የሠራውን አስቂኝ ድራማ ስመለከት እያዘንኩ የታዘብኩትን በዓለም ወደር የማይገኝለት ምርጥ የምርመራ ውጤት በሚመለከት ትንሽ ልበል፡፡

Yeltehedebet Menged

የኢትዮጵያን ቴሌቪዥን በውነቱ አልመለከትም፤ አለመመልከቴ ስህተት መሆኑ ቢገባኝም ጤንነቴን አጥብቄ ስለምፈልገው ይሁነኝ ብዬና ቁም ነገር አገኝበታለሁ ብዬ ኢቲቪን አላየውም – ብዙዎች እኔን መሰሎች ስላሉ “የዐዋጁን በጆሮ” እንዳትሉኝ እንጂ፡፡ የሆኖ ሆኖ በቀደምለታ ከሰዎች ጋር የሆነ ቦታ ቁጭ ብዬ ቁርስ ቢጤ ስንቀምስ በፖሊስ ፕሮግራም የተከታተልኩት በዓይነቱም ሆነ በይዘቱ ድንቅ የሆነ የወያኔ የወንጀል ምርመራ ቴክኒክና ውጤት ያጫረብኝን ልዩ ስሜት በዚህ አጋጣሚ ሳላነሳው መቅረት አልፈለግሁም፡፡ ከእውነት ሰው መሆኔን ጠላሁ፡፡

“መርማሪው” ወያኔ አይታይም፤ ይህን የለመድነው ነው፡፡ ወያኔዎች ራሳቸውን እንደወንጀለኛ አድርገው ስለሚቆጥሩና ከአልቃኢዳ ጋር የሚያመሳስሏቸውን ድርጊቶች የሚፈጽሙ መሆናቸውን ሕዝቡ የተረዳው መሆኑን ስለለተገነዘቡ ይመስለኛል የመንግሥትን ሥልጣንና ኃይልም የጨበጡ “ምሁራኑ መርማሪዎች” በግልጽ በሚዲያ መታየትን የሚወዱ አይመስሉም ፤ እነዚህ ጭራቅ ገራፊዎችና ሀዘን አምላኪዎች (ሳዲስቶች) በራሳቸውም በመንግሥታቸውም የሚተማመኑ እንዳልሆኑና በሆዳቸውና በዘረኝነት ቁርኝታቸው ብቻ ተለክፈው በስሜት ፈረስ የዕውር ድምብር ግልቢያ ዜጎችን የሚያሰቃዩ ናቸው – ቀናቸው ሲደርስ ምን እንደሚውጣቸው ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቀው፤ አሣር አለባቸው – የቁናው ሥፍር እየተንደረበበ ይጠብቃቸዋል – እዚህ ወይም እዚያ፡፡ ከሞራል ዕሤቶቻችንና ከምርመራ ህግ በወጣ ሁኔታ አቡበከር የሚባለውን የሙስሊም ተቃውሞ አመራር አባል እጆቹን በእጀሙቅ አስረው የሚያካሂዱትን “ምርመራ” በአደባባይ በቲቪ ለዓለም ሕዝብ ሲያሳዩም “መርማሪው ሊቅ” መታየትን አልወደደም – አስጠሊታ ሣቁ ግን ከአንጀቱ ጥርስ ሳይሆን ከማተብ የለሽ አንገቱ ይሰማ ነበር፡፡ ስለዚህ የአንዲ ልዩነት እጆቹ አለመታሰራቸው እንጂ ሂደቱ ልክ እንደአቡቦከር ነው፡፡ ይህ የምርመራ ሂደትና ውጤቱ የሀገራችን የለየለት ውርደትና የወያኔን ማንአለብኝነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ ወያኔዎች ከግዑዝ ድንጋይ የማይሻሉ የመጨረሻ ደደቦች መሆናቸውን ምናልባትም ለሚሊዮንኛ ጊዜ የገለጡበት ማፈሪያ ድርጊት ነው፡፡ የሚታዘነው በተመርማሪዎቹ ሳይሆን በመርማሪ ተብዬዎቹ ነው፡፡ ከመነሻው የዘረኝነት ልክፍት ያሽመደመደውና ከዘር ማዕቀፍ ውጭ የማያስብ ደንቆሮ ማይምና ሳዲስት እንዴት አንድን የተማረን ሰው ይመረምራል? እንዲያው ትንሽም ቢሆን የተማረ ዘረኛ ወያኔ ጠፍቶ ነው ወይ? ይህ ዓይነቱ የአደባባይ ግፍ ሄዶ ሄዶ የሚያስከትለውን መዘዝ እንዴት አጡት? ድንቁርና ይህን ያህል በጀብደኝት ያሳውራል?

ወደአስቂኙ ድራማ ልለፍ፡፡ አንዳርጋቸው በ“ነፃ ኅሊናው” የሰጠውና ለኢትዮጵያ ሕዝብ በደናቁር የወያኔ ወንበዴዎች እሳቤ ሊተላለፍ የተፈለገው መልእክት ይህን ይመስላል፤ “የግንቦት ሰባት ኅልውና ከእንግዲህ ግፋ ቢል ለሁለት ወራት ቢዘልቅ ነው፤ ወዲያም አለ ወዲህ ዕድሜው ከሁለት ወር አይበልጥም፡፡ የአውሮፓና አሜሪካ ምቾቱን ትቶ እንደኔ በረሃ ወርዶ የሚያታግል ቆራጥ ሰው አይኖረውም፡፡…”  የግንቦት ሰባት ቀሪ ዕድሜ ሁለት ቀንም ይሁን ሁለት ወር እሱ ሌላ ጉዳይና ወደፊትም የሚታይ ሆኖ ይህን የተናገረው ግን አንዳርጋቸው ጽጌ መሆኑን ልብ ይሏል – አንዲን በሚዲያም ቢሆን ባላውቀው ኖሮ ከአሁን በፊት “የተናገረውን”ና ገና ወደፊት “እንደሚናገረው በጉጉት” የሚጠበቀውን ሁሉ በበኩሌ ሳላንገራግር በሙሉ ልቤ አምኜ በተቀበልኩና ከወያኔ የሸፈተውን ልቤን ወደወያኔ በመለስኩ ነበር – ይህ ሁሉ ድካማቸው ታያ የማንን ቀልብ ለመሳብ ? በመሠረቱ እስካሁን ወያኔ የነበረ በአንዳርጋቸው ንግግር ምክንያት የወያኔነት ደረጃው አይጨምርም – በተቃራኒውም እስካሁን ወያኔ ያልነበረ በዚሁ የአንዲ ንግግር ምክንያት ንዴቱና ቁጭቱ ይጨምርና ወደድርጊት ይገባ እንደሆነ እንጂ ከተቃዋሚነቱ የሚያፈገፍግ አይመስለኝም፤ እናም የወያኔዎች የጅልነት ምጥቀት ያሳዝነኛል ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያውያንንና ዓለምን በጠቅላላው እስከዚህን ያህል መናቃቸው ምን ያህል ወራዳዎች – እደግመዋለሁ ምዕመናን – ምን ያህል ወራዳዎች መሆናቸውን ከማሳየት በስተቀር የአንዲ ስቃይና የሙሌት ኑዛዜ የሚጨምርላቸው አንዳችም አወንታዊ ነገር የለም – ይህን ነባራዊ እውነት ለመናገር ደግሞ የክር ወይም የሃቂቃ ጉዳይ እንጂ የግንቦት ሰባት አባልም ሆነ ደጋፊ መሆንን አይጠይቅም፡፡ የወያኔዎችን ውስጠ ምሥጢርና የግፍ ታሪክ በየመድረኮች ሲዘከዘክ ሚሊዮኖችን በዕንባ ሲያራጭና በትካዜ ባህር ሲያሰምጥ የምናውቀው አንዳርጋቸው ጽጌ በምትሃታዊ ፍጥነት ወደማፊያው መንግሥት ተገልብጦ ተናገረው የተባለውን እንዲያ ሲናገር ይታያችሁ፡፡ የምናውቀው አንዳርጋቸው የምናውቅለትን ጽኑ ፀረ-ወያኔ አቋሙን በሻጥርና በብዙ ገንዘብ ክፍያ በየመኖች ተይዞ በወያኔዎች እጅ በገባ በሁለት ሣምንታት ጊዜ ውስጥ ሲለውጥ በዐይነ ኅሊናችሁ ይታያችሁ፡፡

ግሩም የምርመራ ውጤት! ዓለምን የሚያስደምም ሣይንሳዊ የወንጀል ምርመራ ግኝት! በዚህ በአንዳርጋቸው ቃልና የመከራ ኑዛዜ ማፈር ያለበት ቀደም ሲል ለመጠቆም እንደሞከርኩት ወያኔ ብቻ ነው፡፡ ከወያኔ ውጭ ማንንም ሊያሳፍር አይችልም፡፡ እንዲያውም እኔ ብሆን ኖሮ “ግንቦት ሰባት የሚባል ድርጅት ከነአካቴው በሕይወት አለ እንዴ? አሁን እናንተ ስትሉ ሰማሁ፡፡ ማን ተናገር እንዳለኝ አላውቅም ዝም ብዬ ነበር እኮ በኢሳት ያንን ሁሉ ንግግር የምዘባርቀው፡፡ ደግሞ ብርሃኑን ብሎ ግንቦት ሰባት! ከመነሻው ግንቦት ሰባት ብሎ ነገር ሲኖር አይደለም ወርቆቼ! …” ብዬ አስደስታቸው ነበር እንጂ የሌለን ምሥጢር ለመደበቅ በመሞከር ሰውነቴን ለስቃይ አልዳርግም – ሊያውም በዚያ ኑዛዜየም ስቃዩን ቢቀንሱልኝ አይደል? ግን አይቀንሱልኝም – ስለዚህ ብናገርም ባልናገርም ለውጥ የለውም፤ ጠባችን በደም የሚጠራ እንጂ በውሃ ታጥቦ የሚጸዳ አይደለምና፡፡

እንደውነቱ ታዲያ አንዳርጋቸው ሊሰጠው የሚችለው የማይታወቅ የተከደነ አዲስ ምሥጢር ሊኖር ይችላል? ሁሉም ነገር እኮ ግልጽ ነው፤ ወያኔ የሚባል ሀገር አጥፊና ፀረ-ሕዝብ የሆነ የማፊያዎች ቡድን አራት ኪሎ ቤተ መንግሥት ውስጥ መሽጎ አለ – እሱን ለማስወገድ ደግሞ ዜጎች በተበታተነ ሁኔታም ቢሆን በየፊናቸው ጥረታቸውን እያደረጉ ነው፤ ምሥጢር ከተባለ ይህ ነው ምሥጢሩ፡፡  አንዳርጋቸው የትግል መስመሩ ስላበሳጫቸውና እየሠራ ያለው ነገር ለኅልውናቸው አስጊ ሆኖ ክፉኛ የሚያሳስባቸው በመሆኑ እርግጥ ነው እሱን ከመድረክ ገለል እንዲል ማድረግ ቢፈልጉ ያንን መቀበል ይቻላል – ሰይጣናዊ ፍላጎታቸውን ለማርካት የሄዱበት ርቀት ብዙ የሕግና የሞራል ችግር ማስነሳቱ እንዳለ ሆኖ፡፡ ከዚያ ውጪ ምሥጢር አውጣ ብሎ የዓለማችን ቤት ባፈራው የማሰቃያ ዘዴ ሁሉ ሰውን ማሰቃየት፣ በዚያም ሂደት ራስን ለትዝብትና ለስላቅ የሚያጋልጥ ነውረኛ የምርመራ ሂደት ማካሄድና ተመርማሪዎች የማያምኑበትን ነገር እንዲናገሩ ማድረግ በእግረ መንገድም “በሰላም አንገዛም፣ አንገብርምም ያሉንንና ሕዝብን የሚያሳምጹብንን ቀንደኛ ጠላቶቻችንን ‹እንዲህ አሸናናቸው!›፣ የወንዶች ወንዶች መሆናችንን ብልታቸውን እየቆረጥን አሳየናቸው…” በማለት ስብዕናን ለማዋረድ መሞከር ወደራስ የሚዞር አሉታዊ ውጤትን መጋበዝ መሆኑን መረዳት ይገባቸው ነበር፡፡ ለነገሩ ወያኔ ልብሱም ጉርሱም ቅሌትና ውርደት በመሆኑ በዚህ ረገድ የሚሰማው አንድም የሀፍረትም ሆነ የይሉኝታ ስሜት የለም፡፡ ጃዝ ብለው የለቀቁት 13 እና 33 ቁጥሮችም እየሳቁበትና እየተዝናኑበትም ቢሆን ወያኔ ለሚሠራው ግፍና በደል ሁሉ ቡራኬያቸውን አይነፍጉትም፡፡ እነሱስ ቢሆን በጭፍሮቻቸው አማካይነት በጓንታናሞና ኢራቅ ውስጥ አስከሬኖች ላይ እስከመሽናት በሚዘልቅ ኢሰብአዊነት ስንትና ስንት ግፍ ይፈጸሙ የለም? ልጅ ከአባት ቢማርና የጭካኔ ደረጃውን አዘምኖ ምሥኪን ኢትዮጵያውያንን ምድራዊ ገሃነም ውስጥ ቢዘፍቃቸው ዋኖቹ ሀዘን አምላኪዎች ይደሰታሉ እንጂ ከከንፈር ሽንገላ ባለፈ ሕዝቡን ሊታደጉት አይፈልጉም – ይህንንም አሳምረን እናውቃለን፡፡ ጭምብሉን ፖለቲካዊ የተለሳለሰ የሚመስል አካሄድም አንዘነጋም – አገም ጠቀሙን፡፡

በነገራችን ላይ 13 እና 11 ወይም 33 ደግሞ ተመሳሳይነት አላቸው፡፡ ለሚያምንበት ሁሉም የትልቁ ቁጥር የአውሬው መገለጫ የ666 ቅንስናሾች ናቸው፡፡ አሥራ አንዶች በ110 የለበጣ ቀመር ቢያላግጡም እውነቱ ቀፎ የመለዋወጥ – የትሮይን ፈረስ ቅርጽ የማሻሻል ጉዳይ እንጂ ሲሙ ያው ነው – አሥራ አንድ፡፡ ለነገሩ ዝናር ባንገቴም ይሁን 11 ወይም ዜሮም ይሁን አንድ ሽንትር ዋናው ነገር ተግባር ነው፡፡ ሌላው ትርፍና ጨዋታን ለማሳመር ያህል በአጃቢነት የገባ ነው፡፡ እናም በሀገራችን ሁኔታ የሰውዬው ማንነት ምንም ይሁን ምን በስቃይና በግድያ የሚያምን ሁሉ እናት ክፍሉና ጥንተ አመጣጡ ከአውሬው መሆኑን ልብ ይሏል፡፡ ክፉና ደግ መንፈሶች ኅብረት የላቸውም፡፡ ሩህሩህ መሐሪና አረመኔ/ጨካኝ ገዳይ አንድነት የላቸውም፡፡ መጽሐፉም ጣፋጭ ፍሬ በዛፍ ላይ ሳለ ይታወቃል እንደሚል ማን የማን ወገን መሆኑ በተለይ በዘመናችን በግልጽ ይታወቃል፡፡ ማን ነው የበሽታ ሕዋሳትን በቤተ ሙከራ እየፈለሰፈና እያራባ ለዓለም በተለይም ለኋላቀር ሀገሮች እንደ ዕርዳታ ስንዴ የሚያከፋፍል? ማን ነው የዓለማችንን የአየር ንብረት እያዛባና ዕድሜዋን በብርሃን ፍጥነት እያሳጠረ የሚገኘው? የዓለምን ጠቅላይ ገዢነት በትረ መንግሥት በጉልበት የተቆጣጠረውና “ለኔ ካልሰገዳችሁ ሀብትና ሥልጣን አይኖራችሁም” ብሎ ሁሉን እያስደገደገ የሚገኘውና በትዕምርተ ኅቡኣታዊ ባለአንድ ዐይን ፒራሚዳዊ ቅርጽ ወይም በፔንታጋራማቲን የኮከብ ቅርጽ የሚታወቀው ምሥጢራዊ ኃይል ማን ነው? ማን ነው አሁንም ሆነ ከአሁን በፊት መካከለኛውን ምሥራቅ እያተራመሰ ያለው? መፍለቂያው የሆነችን የአንዲት ትንሽዬ ሀገር ኅልውናና የበላይነት ለማስጠበቅ ሲል ድምጽን በድምጽ የመሻር መብቱ የዓለምን የመንግሥታት ኅብረት እንደአሽከር ሰጥ ለምበጥ አድርጎ የሚገዛ ማን ነው? አይኤም ኤፍ፣ ዩኤን፣ ወርልድባንክ፣ ኔቶ፣ ሲአርኤፍ፣ … የማን አድቃቂ ክንዶች ናቸው? ለመሆኑ የዚህ ሞገደኛ የወቅቱ የዓለማችን ገዢ ዋና መሥሪያ ቤትና ቅርንጫፍ ቢሮዎቹ የት የት ናቸው? ጽዮንና ሀማስ የማን ልዑካን ናቸው? የግጭቶች መንስኤና የምክንያታዊነት ሚዛኑ ለማንም ያጋድል ዋናው የሁለቱም ተልእኮ ግና ለአውሬው ግብር የሚሆን ብዙ የደም ባህር ማቆር መሆኑን መዘንጋት የዓለም ነገር አያገባኝም ብሎ እንደመመነን ይቆጠራል፡፡ በየትኛውም የዓለም ክፍል – ማን ነው የጦር ኃይሎችን በሁለት ጎራ እየከፈለ በተፃራሪነት በማሰለፍ የሚሊዮኖችን ደም በከንቱ እያፋሰሰ ያለው? ኢራንና አሜሪካ በርግጥም ባላንጣዎች ይሆኑ እንዴ? በፍጹም፡፡ ጠላቶች መስለው ትያትር በመከወን ለአንድ ዓላማ ስኬት የሚተጉ የአንድ ገዢ አንድ አምሳል አንድ አካል ናቸው፡፡  ማን ነው በአራት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከአፍ እስከገደፋቸው በንጹሃን ተሣፋሪዎች ጢም ብለው የሞሉ የሲቪል አውሮፕላኖችን(የማሌዥያን) ባልታወቀ ዕፀ መሠውርና በሚሳኤይል ድራሻቸውን ያጠፋው? ምን ዓይነት ወያኔያዊ ጨካኝ አንጀት ያለው ፍጡር ይሆን ይህን ያደረገ? ለምን ዓላማ? ቫቲካንንና መለስተኛ አውሮፕላን የምታህል የነጭ እርግብ ምስል ለማስመሰል ያህል በሰላም ምልክትነት በዋና የፓትርያርክ ጸ/ቤቱ በር ላይ ያቆመውን የኛኑ ኦርቶዶክስ ሳይቀር ከሞላ ጎደል ሁሉንም የሃይማኖት ተቋማት ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ተቆጣጥሮ ሁሉንም ሃይማኖት አለኝ ባይ በአውሬው ትዕዛዝ ሥር ያደረገው ማን ነው? ለመሆኑ በአሁኑ ሰዓት ቅዱስ ሊባል የሚችል ቦታና ሰው አለ ወይ? ፖፕ ጆን ፖል አንደኛ፣ ፖፕ ቤኔዲክት 16ኛ፣ ‹አቡነ› ጳውሎስ የኛ… ሌሎችም የማን ወኪል ነበሩ? ፍየሎች በበጎች ጋጣ ውስጥ መሽገዋል፡፡ በጎች እያለቁ ነው፡፡ አውሬው ሆሊውድና ቦሊውድን ብቻ ሳይን ገዳማትንና ካቴድራሎችንም ከተቆጣጠረ ምዕተ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ጭካኔን በሚያስተምሩ ፊልሞች፣ በልቅና ባልተገሩ ኢ-ሞራላዊም በሆኑ ፖርኖግራፊዎች በተለይ የዓለምን ወጣት ትውልድ ጡጦ ከመጣሉ በእንጭጩ ለማምከን  ይህችን ዓለም ማንና ከየትስ ሆኖ እየገዛት እንዳለ መች አጣነው? የዚያ ‹ታላቅ› የጨለማ ንጉሥ የእጅ ሥራዎች የሆኑ ወያኔዎችም ባቅማቸው ቅድስቲቱን ሀገር ድራሽዋን ቢያጠፏት ከድጋፍ በስተቀር ማን ከልካይ አላቸው? በጎችስ ቢጮኹ አለጊዜው ማን ይደርስላቸዋል? ግን ግን አይዞን፤ የፍየሎችና የበጎች የመጨረሻ ዕድል ተለይቶ የሚታወቅበት የፍርድ ቀን በፍጥነት እየመጣ ነው፡፡ ብሎም ቢሆን ሥጋዊም ሆነ መንፈሳዊ ድል በምኞት ሊገኝ እንደማይችል ልብ ማለት ይገባናል፡፡ ብቻ ይህን መሰሉን ነገር በሆድ ይፍጀው ለሌላ ቀን በይደር ማቆየቱ ሳይሻል አይቀርም፡፡ ለነገሩ እኛን ምን አገባን? ሁሉም ከልኩ አይዘል፡፡

 

ከሰው ተውሼ እያነበብኩት ነበር – “ያልተሄደበት መንገድ”ን፡፡ በቅርብ ካነበብኳቸው በሀገር ችግር ዙሪያ ከሚያጠነጥኑ የቅርብ ጊዜ መጻሕፍት ውስጥ በኔ ዕይታና ለኔ ፍጆታ ይሄኛውን ወደር አላገኘሁለትም፡፡ አንዱአለም አራጌ ዋለ የተዋጣለት መጽሐፍ በመጻፉ – ሊያውም በዚህ አፍላ የጎልማሳነት ዕድሜውና በመከራ ውስጥ ሆኖ – ባለበት አድናቆቴ ይድረሰው፡፡ ወላድ በድባብ ትሂድ የሚባለው በዚህ ዓይነት አጋጣሚ ነው፡፡ ሚሊዮኖች ፈርተንና ለሥጋችን አድረን በየሽርንቁላው ተወትፈን በፍርሀት ቆፈን ስንርድ ሊያውም በእስር ቤት ውስጥ ሆኖ ይህን የመሰለ አብሪ መጽሐፍ ካለበቂ ማጣቀሻና ዋቢ መጻሕፍት በአዩኝ አላዩኝ ሰቀቀን ሌሊት ሌሊት እየተደበቁ መጻፍ ልዩ ጀግንነትና ተሰጥዖም ነው፡፡ አንዱአለምና መሰል የብዕርና የፖለቲካ ታጋዮች ለነፃይቱ ኢትዮጵያ በሕይወት እንዲደርሱ እግዚአብሔር ይታደገን፤ ይታደጋቸው፡፡ ቤተሰባቸውንም ይባርክ፡፡ ለእኛም ለባከንነውና ለራሳችን ጥቅምና ፍላጎት ስንል በ‹እስኪያልፍ ያለፋል› ተረት ራሳችንን እያታለልን የወያኔ ባርያ ሆነን ለጠፋነው ዜጎችም ፈጣሪ ረድኤቱንና ወኔውን ይስጠን፡፡ እንደዚህ ያሉ ዜጎች ባይኖሩን ኖሮ ሕይወት በጠቅላላው ለይቶላት ጨለማ በሆነች ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር እግዜር የተመሰገነ ይሁን፡፡ እርሱን መሰል ሌሎች ጸሐፊዎችንና ታሳሪዎችንም ጭምር እግዜር ይባርክልን፡፡ ለቤታቸውም ያብቃልን፡፡ የሚሳነው ነገር የሌለው የኢትዮጵያ አምላክ የመከራ ደብዳቤያችንን የሚቀድድና ሃራ የሚያወጣን አንዳች ኃይል ይዘዝልን፡፡ አሜን፡፡

ይህ መጽሐፍ የዋቢ መጻሕፍትን ገጽ ጨምሮ በጠቅላላው 320 ገጾች አሉት፡፡ በአራት ዋና ዋና ክፍሎች ሥር የተካተቱ 18 ርዕሶችንም ይዟል፡፡ ጠቅጠቅ ብሎ የተጻፈ በመሆኑ እንደሌሎች በርካታ መሰል መጻሕፍት በቀላሉ አይገፋም፡፡ የሆኖ ሆኖ በተለይ እስከማገባደጃው ድረስ ስሜትን ቆንጥጦ በመያዝ መነበብ የሚያስችለው ሥነ ጽሑፋዊ ውበትና ይዘታዊ ግርማ ሞገስ አለው፡፡ እናም አንብቡት፡፡ በነገራችን ላይ ይህን መጽሐፍ እያነበብኩ ወደ ገጽ 100 አካባቢ ስደርስ የተዋስኩትን እንደምመልስ ገባኝና ወዲያውኑ ከተማ ወጥቼ ገዛሁት፡፡ ተውሼ ያነበብኩትን ወይም እያነበብኩት ያለሁትን መጽሐፍ ስገዛ ይህ የመጀመሪያ ጊዜየ ነው፡፡ አንጡራ ሀብቴና የመጻሕፍት መደርደሪያየ አንዱ ፈርጥ እንዲሆን ተመኘሁ፡፡ ተመኝቼም አልቀረሁ፡፡ ለልጆቼ ውርስ ይሆናል፡፡ እናንተም አሁኑኑ ግዙና ንብረታችሁ አድርጉት፡፡ መጽሐፉ “ኩሎ አመክሩ ወዘሰናየ አጸንዑ” እንዲል፡፡

አመስጋኝ አማሳኝ እንዳልባል በዚህ መጽሐፍ የታዘብኳቸውን አንዳንድ ግድፈቶችም በዚሁ አጋጣሚ ብጠቁም ደስ ይለኛል፡፡ ጥቂት የማይባሉ የአርትዖት ችግሮች አሉበት፡፡ አሉታዊ መሆን ያለበት በአወንታዊ ወይም የዚህ ተቃራኒ ሆኖ የሚጻፍበት አጋጣሚ አልፎ አልፎ ይስተዋላል፡፡ አማርኛ ላይ ብዙውን ጊዜ የምታስቸግር ነገር አለች – ለምሳሌ “እኔን እንደሚያገባኝ እንዴት ረሳኸው?” በሚለው ዐረፍተ ነገር ውስጥ “ሚ”ን “ማ” ብናደርጋት ትርጉሙ ሙሉ በሙሉ ይለወጣል፡፡ “ጽንፍ” ለማለት “ቅንፍ” ብንል አንዳንዶችን ግር ሊያሰኝ ይችላል፡፡ የአርትዖት ሥራ ሽንፍላ እንደማጠብ ነው፡፡ በተቻለ መጠን ብዙ ሰዎች በብዙ አዳዲስ ዐይኖች ሊተባበሩበት የሚገባው አስቸጋሪ ሥራ ነው፡፡ እንዲያም ሆኖ የማይጠራበት ጊዜ አለ፡፡ ከዚህ አኳያ ይህን ቆንጆና ለታሪክ የሚቀመጥ መጽሐፍ ዐዋቂ ሰው እንደገና “ኤዲት” ቢያደርገው የበለጠ ማለፊያ ይሆናል፡፡ የግሌ አስተያየት ነው፡፡ (አንድ ወዳጄ የነገረኝ አንድ አርትዖታዊ ስህተት በጭንቅላቴ ብልጭ እያለ ‹እዚህ ላይ ካልጻፍከኝ ሞቼ እገኛለሁ!› ብሎ አስቸገረኝ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡ የመሥሪያ ቤቱ የብድር ኮሚቴ ስብሰባ ይጠራል፡፡ ለተሰብሳቢዎችም “ከብድር ኮሚቴ…. ለጠቅላላ አባላት” የሚል ጽሑፍ ተበትኗል፡፡ ሁሉን ያስፈገገው ግን ጸሐፊዋ “ከብድር ኮሚቴ” ከሚለው ሐረግ ውስጥ የአንዱን ቃል የመጨረሻ ፊደል ሳትጽፈው መቅረቷና እስከዚያን የስብሰባ ጊዜ ድረስ ማንም ጉዳዩ የሚመለከተው አካል ስህተቱን ልብ አለማለቱ  ነበር፡፡ ያቺ “ነገረኛ” ጸሐፊ የትኛዋን ሆሄ እንደዘነጋቻት እኔም አሁን ዘነጋኋት፡፡ )

ከሆሄያት ግድፈትና ሞክሼ ፊደላትን  በነባሩ ሰዋስዋዊ ልማድ ከመጠቀም አኳያ ከሚታዩ አንዳንድ ጥቃቅን “ስህተቶች” በተጓዳኝ ጥቂት የመረጃ መዛባትና የዘይቤና ፈሊጥ አጠቃቀም እጅግ አነስተኛ ችግር ሳይኖር እንደማይቀር እገምታለሁ፡፡ ለምሳሌ “ኢሕአፓ” የሚለው ምሕጻረ ቃል ሲፈታ እኔ የማውቀው “የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ” በሚል ነው፡፡ በዚህ መጽሐፍ ግን “የኢትዮጵያ ሕዝብ አደራጅ ፓርቲ” በሚል ከአንዴም ሁለቴ ገደማ ቀርቧል፡፡ ፈሊጥን በተመለከተ “ለያዥ ለገራዥ” ለማለት “ለያዥ ለገናዥ” ተብሏል፡፡ በተጨማሪም የሃሳብ ድግግሞሽ በስፋት ይታይበታል፡፡ በዚያም ምክንያት አንድ አንባቢ በጀመረበት የስሜት ሞቅታ መጨረስ ባይችል ችግሩ ከዚህ የሃሳቦች መደጋገም የሚመነጭ ይመስለኛል፡፡ የሆኖ ሆኖ የመጽሐፉ አጻጻፍና ለኅትመት መብቃት በብዙ ችግር የታጠረ በመሆኑ የአሁኑ ይዘቱ ራሱ ከሚጠበቀው በላይና በአንጻራዊ ሁኔታ ከሌሎች በርካታ መሰል ጸሑፎች(እኔ ካነበብኳቸው) በጣም የተሻለ መሆኑን በበኩሌ ልገነዘብ ችያለሁ፡፡ በመሆኑም ይህ ጥረቱ ደራሲውን በእጅጉ ያስመሰግነዋል፡፡ እዬዬም ሲደላ ነው ጓዶች፡፡ እነኚህንና መሰል ሌሎች እንከኖችን አስተካክሎ በቀጣይ ኅትመት ለንባብ የሚያበቃው ወገን ከተገኘ መልካም ነው፡፡ ደግሞም የማይቻል አይመስለኝም፡፡

 

አንዱአለምን በዚህ መጽሐፉ ደርቤ እንዳነበብኩት የፕሮፌሰር መስፍን ደቀ መዝሙር ይመስለኛል፡፡ ይህን የምለው ፕሮፌሰሩ አንድ ወቅት እነብርሃኑ ነጋ “ሁለገብ ዘዴን በመጠቀም ወያኔን እንታገላለን” ባሉ ወቅት ክፉኛ ይተቿቸውና “እኛ ወደዚህ ‹የማይረባና ውዳቂ› የአስተሳሰብ ደረጃ አንወርድም”  ማለታቸውን በማስታወስና አንዱአለምም በዚያው ቅኝት አሁንም ድረስ በዚህ በኢትዮጵያ ውስጥ ወንዝ ቀርቶ የደረቀ ምንጭ በማያሻግር የሰላማዊ ትግል ሥልት ወያኔን እንጥላለን ብሎ የሚያምን በመሆኑ ነው፡፡ እርግጥ ነው አንዱአለም አሁን ባለበት ሁኔታ በኃይል ወይም በጦር መሣሪያ ወያኔን እንታገል ብሎ ቢጽፍ የሚደርስበትን ተጨማሪ መከራና ፍዳ ስለምንገነዘብ ይህን አቋም ያርምድ ብለን በሰው ቁስል እንጨት አንሰድም፡፡ ይሁንና ቢያንስ ዝም ማለት ሲገባ ወያኔ የፈጠረው የኢትዮጵያ ውጥንቅጥ ችግር የሚፈታው ወያኔን በሰላማዊ መንገድ በመታገል ብቻ ነው የሚል እምነት በጭፍን ማራመዱን አልወደድኩለትም፡፡ (በነገራችን ላይ ኤርምያስ ለገሰ ቅድም በኢሳት አንድ ውይይት ላይ ሲናገር እንደሰማሁት የአንዳርጋቸውን በወያኔዎች መያዝ ኔልሰን ማንዴላ በኢዲያሚን ዳዳ እንደተያዘ ያህል እቆጥረዋለሁ ማለቱን እኔም በጣም እደግፋለሁ፡፡) ሰው ከሰው ጋር ቢታገል አሸናፊውና ተሸናፊው ይለያል፡፡ ከአውሬ ጋር ግን እንዴት መታገል ይቻላል? ውሾች በ“አስተሳሰብ” ከሚበልጡት ወያኔ ጋር እንዴት ስለሰላም መወያየት እንደሚቻል አንዱአለም ቢያስረዳኝ ደስ ባለኝ፤ ውሾ ሲሸናነፉ በሚያሳዩት ተፈጥሯዊ ምልክት ይግባቡና ጦርነቱን ያቆማሉ፤ ከዚያም በመካከላቸው ሰላም ይሰፍናል፡፡ ሁኔታዎችም ወደጥንቱ (statusquo ante) ይመለሱና ማኅበረከልባዊ ሕይወት ትቀጥላለች (“ከልብ” ውሻ ማለት ነው – “ል” ጠብቃ አትነበብም)፡፡ ወያኔ ግን ያሸነፈውን ሁሉ በሕይወት ያለውን ብቻም አይደለም የሞተውን ሳይቀር እስከመቃብር ድረስ የፕሮፓጋንዳ ሠራዊት እያዘመተ የቅርብ አጥንቶችንና የሩቅ አፅሞችን የሚፋለም ዶንኪሾት ነው፡፡ ይህን ባሕርዩን ለማወቅ በግድ እንደነአሥራት ወ/የስ መሞትና እንደነእስክንድር ነጋ መታሰር አያስፈልግም፡፡ ዛሬ ላይ ቁጭ ብሎ ወያኔን በሰላማዊ መንገድ ከሥልጣን አስነሳለሁ ብሎ መቃዠት በርግጥም ቅዠትና ሲያንስም የዋህነት እንጂ አንዱአለምን ከመሰለ በሳል የፖለቲካ ሰውነት የሚጠበቅ አይመስለኝም፡፡ ከዚህ ውሱን ነጥብ አኳያ ምን እንደነካው ሊገባኝ አልቻለም፡፡

አክራሪ ኦርዶቶክሳውያን እንዳይቀየሙኝ እንጂ የአንዱአለም የዋህነት (naivety?) ከ‹ቅድስት› ክርስቶስ ሠምራ ጋር ይመሳሰልብኛል፡፡ ‹ቅ.› ክርስቶስ ሠምራ – በገድሏ ላይ ተጽፎ እንደሚነበበው – ሰይጣንን ከእግዚአብሔር ለማስታረቅ ዕቅድ ትነድፋለች አሉ፡፡ … እርሱ ወዳለበት ሲዖል በቀጥታ ትሄዳለች፡፡ “ስፈልግሽ ኖሮ እዚሁ መጣሽልኝ?” ይላትና የክርስቶስ ሠምራን ነፍስ ይዞ ወደግዛቱ ሊያስገባት ሲል መላእክት ደርሰው ወደመጣችበት ወደገነት ይወስዷታል፡፡ በአጋጣሚው ግን 78 ሺህ የተኮነኑ የሲዖል ነፍሳት በቅድስቲቷ መንፈሳዊ አካል ላይ በመጣበቅ ወደገነት ይገባሉ፡፡ እምነት ነው፡፡ በየዘመናቱ በገዢዎችና በሃይማኖት መሪዎች ፈቃድ እንዲካተቱ የተደረጉና እነዚህን አሳሳች ይዘት ያላቸውንና እርስ በርስ የሚቃረኑ፣ “በእግዚአብሔር መንፈስ የተነዱ” ሰዎች ስለመጻፋቸው የሚጠቁም አንዳችም ማስረጃም የሌላቸውን በመጽሐፍ ቅዱስ የተካተቱ አንዳንድ ጽሑፎችንና ሰይጣናዊ ሳጋዎችን ሳይቀር ላለመቀበል አንድ ሰው መብት ያለው መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህን ኢትዮጵያዊ ሃይማኖታዊ ድርሰት ማመን አለማመን የማንም ውዴታ እንጂ ግዴታ ሊሆን አይገባም – እዚያው ውስጥ በሚገኙት ዘንድም ቢሆን፡፡ ታርጋ ሳይለጠፍብኝ ስለሃይማኖቴ ልናገር እንዴ? አይ፣ ለማንም አይጠቅምም፡፡ ግን ማንኛውንም ሃይማኖታዊ አክራሪነትና ጽንፈኝነት የምጠላ አማኝ(theist) መሆኔን ብገልጽ ደስ ይለኛል፡፡ አነሳሴ ወዳልሆነ ነገር በመንሸራተቴ ይቅርታ – ምን ላድርግ ሁሉም ነገር አንሸራታች ሆኖ ዐረፈው እኮ፡፡ ብቻ አንዱአለም የዚህችን ቀና ሴት ባሕርይ የተላበሰ ግን በአፀደ ሕይወት የሚገኝ የማይቻልን ነገር ለመሞከር የሚተጋ የወንድ ክርስቶስ ሠምራ ይመስለኛል፡፡  

ሰላማዊ ትግል የራሱ መደላድል አለው፡፡ በቅድሚያ የሀገርህ ሰው ከሆነ ሰው ጋር፣ ዜጋህ ከሆነ ሰው ጋር፣ እንደዜጋው ከሚቆጥርህ ወይም ከሚመለከትህ የአገዛዝ ኃይል ጋር፣ በትንሹ ደግሞ ሰው መሆንህን አምኖ ከሚቀበል ሰው ጋር እንጂ ከአውሬና ከለዬለት የዲያብሎስ መንጋ ጋር በሰላማዊ መንገድ እታገላለሁ ብለህ ወርቃማ የመቶዎች ዓመታት ጊዜህን አታባክንም – አንዱአለም የሚለው ግን ዝንታለሙን እየታሰርንና እየተገደልን ነፃነታችንን ከወያኔ በችሮታ እንቀበል ነው – ምናልባትም በወዲያኛው የምፅዓት ዘመን፡፡ ሰዎች ወያኔን መረዳት እንዴት እንዳልቻሉ ወይም እንደማይችሉ ሳስበው ይገርመኛል፤ እንዲያውም ወያኔዎች፣ ሰዎች እንዲህ እንዲሆኑ – ማለትም በሰላማዊ መንገድ ከነሱ ጋር መታገል እንደሚቻል እንዲያምኑና እንዲያሳምኑ – የሚያደርግ ድግምት ቢጤ ሳይኖራቸው የሚቀር አይመስለኝም፡፡ አለበለዚያስ የሰላማዊ ትግልን ገፈት ቀማሽ ከሆነ አንዱአለምን ከመሰለ ብርቅዬ ዜጋ እንዲህ ያለ ተሳስቶ የሚያሳስት አነጋገርና እምነት ሊደመጥ ባልተገባ ነበር፡፡ ይቅርታ ይደረግልኝና ዝምታ ማንን ገደለ? በከንቱ መነቃቀፍ ከትዝብት በስተቀር ምን አወንታዊ ውጤት ያስገኛል? እንዳለመታደልና እንደርግማንም ሆኖ በኅብረት መታገል ቢያቅት ሁሉም ባመነበት ቢንቀሳቀስ ምን ክፋት አለው? ከአድማስ ማዶ ሊኖር ይችላል ተብሎ በሚታሰብ ሥጋት ከወዲሁ መቆራቆስ አግባብ ነው ወይ? ለዚህማ ወያኔ አለ አይደል? ይህን ስል አንዱአለማውያንና መስፍናውያን – በተወሰነ ደረጃ እኔንም ጨምሮ – ስሜታችን እንደሚጎፈንን ይሰማኛል፡፡ ግን ምርጫ የለኝም፡፡ የሚሰማኝን መናገሬ እንደወንጀል ሊቆጠርብኝ አይገባም፡፡ አውቃለሁ – አንዱአለም እሳት ውስጥ ነው፡፡ አልክድም – እኔም ከርሱ ባልተናነሰ ሁኔታ እሳት ውስጥ አለሁ፡፡ ልዩነታችን እርሱ ባመነበት ገብቷል፡፡ “ደስ”ም ያለው ይመስላል፡፡ የኔ ግን ከሁሉ ያጣ ሆኜ በዕብደትና በስክነት መካከል አንዴ ሰው አንዴ ዐፈር በመሆን እየተቀያየርኩ መረጋጋትና ሰላም የሌለው ሕይወት እገፋለሁ፡፡ ኅሊናህን አፍነህ መኖር ከመታሰር በበለጠ እንደሚጎዳ አውቄያለሁ፡፡ ሰው እንኳን ሳያውቅልህ በአእምሮ ስቃይ ምክንያት ከቤተሰብህም ከጓደኞችህም ‹እየተናጀስክ› ሰላምህን አጥተህ በትልቁ እስር ቤት መኖር በትንሹ እስር ቤት ከመኖር የበለጠ እንደሚያሰቃይ ተረድቻለሁ፡፡ መብላት፣ መጠጣት፣ መዳራትና በሰፊ ጎዳና መመላለስ ትርጉም የሚያጡበትና አንጎልህ ተቀፍድዶ ተይዞ ሰዎችን ሰላም በምትነሳበት ሁኔታ ለመኖር ያህል ብቻ መኖር ከለዬለት ከርቸሌ ያልተሻለ መሆኑን ከተረዳሁ ቆይቻለሁ፡፡ ስለሆነም ከአንዱአለም ባልተናነሰ የኔም እስረኝነት የዋዛ አይደለምና ሁላችንም አንድ ነን፡፡ እንዲህ የምለው ስለኔ ብቻ አይደለም – ስለሌሎች እኔን መሰሎችም እንጂ፡፡ እንዲህ የምለው ግን ለምንድነው? የማንን አንጀት ለማላወስ? ማንስ ነው ሆዴ ላይ ቆሞ ያናዘዘኝ? ሆ!   

በውሸት መከሰሱን፣ በውሸት ምሥክር (አዳፍኔ በሚላቸው) ዘብጥያ መውረዱን፣ በውሸት የግንቦት ሰባት አባልና የሽብር ጥቃት ሊፈጽም ከምንደኞች ጋር እያቀነባበረ ነው መባሉን፣ …. ሁሉንም ዘንግቶ ከእባብ ዕንቁላል እርግብ እንደሚፈለፈል ሊያስረዳን መሞከሩ አንዱአለም ወያኔን ለማወቅ ገና ብዙ ጊዜ የሚፈጅበት መሆኑን አመልክቶኛል – ጠሊቅ ሀገራዊና ታሪካዊ ዕውቀት ያለው መሆኑ ተይዞልኝ፡፡ እናም እላለሁ – ሰማይ ዝቅ መሬት ከፍ ቢሉ ወያኔ በሰላማዊ ትግል ሥልጣን አይለቅም፡፡ ይህን ፀሐይ የሞቀውንና ሀገር ያወቀውን ሃቅ በመካድ ከዚህ የተለዬ ህልም ማለም – እንደአካሄድ ባይከለከልም – ትዝብት ላይ ይጥላል፡፡ በነገራችን ላይ ክርስቶስም ለትግስቱና ለፍቅሩ ገደብ ነበረው፤ ለዚህም ነው በመሳም አሳልፎ የሰጠውን ይሁዳን የረገመው – በአንገቱ የወፍጮ መጅ ታስሮ ወደጥልቅ ባህር ቢወረወር እንደሚሻለው በምሬት በመናገር፡፡

ይቅርታችሁንና በዚህስ አንዱአለምን ተናድጀበታለሁ፡፡ ምን ነካው ግን? እንግዲያውስ ያበጠው ይፈንዳ በኢትዮጵያ እንደእስካሁኑ የስግብግብነትና ራስ ወዳድነት በሽታችንና የሥልጣን አራራችን ከሆነ በሰላማዊ መንገድ እንኳንስ ወያኔ ኢንጂኔር ግዛቸው ሽፈራውም ሥልጣን አይለቅም፤ እንኳንስ ወያኔ ኢንጂኔር ኃይሉ ሻውልም አይለቅም (በጤና ምክንያት …ካልሆነ)፤ እንኳንስ ወያኔ ፕሮ. በየነ ጴጥሮስም አይለቅም፤ እንኳንስ ወያኔ ዶር. መረራ ጉዲናም አይለቅም፤ እንኳንስ ወያኔ ዶር. ፍስሐ እሸቱም አይለቅም፤ እንኳንስ ወያኔ በቁሙ የሞተው ከሃዲው ልደቱ አያሌውም አይለቅም … (ዝርዝሩ ብዙና ብዙ ነው – ስንተዋወቅ? ግን እባብ ልቡን ዐይቶ እግሩን ነሣው ሆነና …)፡፡ የኢትዮጵያ መሬት አዲስ በሚፈልቅ ፍቱን ጠበል ካልተረጨ ይሄ የሥልጣንና የገንዘብ እንዲሁም የሴሰኝነት ጠንቆች በቀላሉ አይለቁንም – በኛ ባሱብን እንጂ እርግጥ ነው እነዚህ መሰናከያዎች የአጠቃላዩ የሰው ዘር መደናቀፊያዎች መሆናቸው የታወቀ ነው (ለምሳሌ የሰሞኑንና የቅርብ ሩቅ ጊዜውን የኢራቁን አልማሊኪንና የግብጹን አልሲሲን የሥልጣን ሱስ ብናይ በሰው ልጅ ራስ ወዳድነት መገረማችን አይቀርም – ይህ ነገር ወደኛ መጥቶ ከማይምነታችን፣ ከሥልጣን ወዳድነታችንና ከቦክሰኛው አስተዳደጋችን ጋር ሲደመርማ ምን ያሳይ፡፡) በኛ ሀገር ለሁሉም ነገር በተለይም ለጥላቻችንና ለራስ ወዳድነታችን ልጓም አጣን፤ ለከት ጠፋ፤ በቃኝን ተጸየፍን፤ ጠገብኩን ጠላን፤ ከይሉኝታና ሀፍረት ተፋታን – ስንገርም፡፡ እናም ለነዚህ ነገሮች ያለን ጥብቅ ቀረቤታ ከሌሎች የጥፋት ሰበዞች ጋር ተደማምሮ እንደሀገርም እንደሕዝብም ከናካቴው ከምድረ ገጽ ልንጠፋ – መለኮታዊ ጣልቃገብነት በቅርብ ጊዜ ውስጥ ካልተከሰተ –  ዘመኑ ቀረበ፡፡ ውሸት ነው? ውሸት ነው ካልክ እውነት ነው ማለት ነው፡፡ “አልሞትኩም ብዬ አልዋሽም” የሚል መጽሐፍ ዱሮ አነበብኩ ልበል? አዎ፣ ‹ፀጉራም ውሻ አለ ሲሉት ይሞታል› እንዲሉ ካልሆነ ለይቶልን ጠፍናል፡፡ አንወሻሽ፡፡

አንዱአለም ወያኔ በሰላማዊ መንገድ ሥልጣን እንደማይለቅ አሳምሮ ያውቃል፡፡ መጽሐፉ ላይ በገደምዳሜ ገልጾታል፡፡ እንደመፍትሔ በየገጾቹ የሚያቀርበው ግን ያንኑ የሰላማዊ መንገድ የትግል ሥልት ነው፡፡ “የሰላማዊ መንገዱ ካልሠራ” ይላል አንዱአለም ፈገግ ባደረገኝ ሁኔታ “የሰላማዊ መንገዱ ካልሠራ ሌላ የሰላማዊ መንገድ መሞከር ነው፡፡” ከመሰነባበታችን በፊት በመጽሐፉ መጨረሻ አካባቢ ገጽ 312 ላይ የሚገኘውንና ወያኔን በሰላማዊ መንገድ ማስወገድ ባይቻል በማስከተል ምን ማድረግ እንደሚገባ አንዱአለም የመጨረሻ መፍትሔ ብሎ የሚሰነዝረውን እንመልከት – ወጣቱ ፖለቲከኛ አይፈረድበትም፡፡ የት ነው ያለውና? አያድርስ ነው – እነዚህ ሰዎች አስጨንቀው ያዙንና እምንለውንም እያሳካሩ ግራ አጋቡን እኮ፡፡ አንዱ ለጓደኛው “ያዋስኩህን ዕቃ ባትመልስ ዋልህ! አሳይሃለሁ!” ይለዋል፡፡ “ምናባህ ልታደርገኝ አንት የውሻ ልጅ!” ብሎ ቢያፈጥበት “አይ፣ ምን አድርግሃለሁ ያው ታዝቤህ እቀራለሁ እንጂ” አለው ይባላል፡፡ እርግጥ ነው መናገር የማድረግን ያህል እንደማይከብድ አውቃለሁ፡፡ “አይ መሬት ያለ ሰው!” ብሏል አሉ የሚጋልበው ፈረስ የደነበረበት አንድ ሰው – “እንዲህ አድርገው፤ እንዲህ ያዘው” ባሉት ጊዜና፡፡ አሁንም እርግጥ ነው – ለተቀማጭ ሰማይ ቅርብ ነው፡፡ እርግጥ ነው – አታሞ በሰው እጅ ስታምር በገዛ እጅግ ግን ልታደናግር ትችላለች፡፡ ቢሆንም የሚሰማኝን ብናገር ቢያንስ ዴሞክራሲያዊ መብቴን “ባልተሸራረፈ” መልኩ እንደተጠቀምኩበት ከመረዳቴም በተጨማሪ የተወሰነ እፎይታን አገኛለሁ፡፡ ለማንኛውም ወደአንዱአለም የመጨረሻ የችግሮቻችን መፍትሔ እናምራና ለአፍታ እንመልከትለት፤

 

ትልቁ ጥያቄ ኢሕአዴግ የብሔራዊ ዕርቁን ጥያቄ አሁንም “የባልና የሚስት ፀብ አይደለም” ብሎ ቢያጣጥለው ምን ማድረግ ይቻላል? የሚለው ነው፡፡ በእኔ እምነት ኢሕአዴግ ከዚህ በኋላም (እስካሁን) ለ21 ዓመታት የዳከረበትን መንገድ የሚመርጥ ከሆነ ተቃዋሚዎች ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ሆነው የሚጓዙ(በ)ት የራሳቸው አዲስ መንገድ መፈጠሩ አይቀሬ ይመስለኛል፡፡ ኢትዮጵያን በአስተማማኝ መሠረት ላይ ለመገንባት (የ)ሚያስችለውን የብሔራዊ ዕርቅ መንገድ በመጓዝ ለፍትሃዊ ነፃና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንገድ መጥረግ የማይፈልግ ኃይል በኢትዮጵያ ሕዝብ ሰቆቃ ላይ የራሱን ግላዊ ወይም ቡድናዊ ጥቅም ብቻ የሚያስቀድም መሆኑን ያመለክታል፡፡ ኢሕአዴግም ይሄን መንገድ እስከመረጠ ድረስ የኢትዮጵያን ሕዝብ በኃይል ረግጦ የመግዛት ፍላጎቱን አሁንም ለመቀጠል እንደሚፈልግ ያሳያል፡፡ የማንወጣው መንገድ ቢሆንም ከተገደድን ግን ኢትዮጵያውያን በፀና ሰላማዊ ትግል ኢሕአዲግን ልኩን እንዲያውቅ ብሎም ለኢትዮጵያ ሕዝብ ፈቃድ እንዲገዛ ማድረግ አማራጭ የለውም፡፡ … (መስመር የተጨመረ) 

 

 

ወያኔ ልኩን የሚያውቀው በሰላማዊ ትግል ነውን? ይህ ነገር እውነት ይሆን? ይህች ነገር አጭር የክበበው ገዳን ቀልድ ትመስለኛለች፡፡

 

 

በመሠረቱ ጥሩ መመኘት በራሱ መጥፎ አይደለም፡፡ ነገር ግን የምኞትን ገደብ ማወቅ ተገቢ ነው፡፡ አንዱአለም ከዕድሜ አንጻርም ይሁን ከገጠመኝ ማጠጥ/ማጠር የተነሣ በኢትዮጵያ ምድር አይመኙትን ምኞት በመመኘት እርሱን መሳይ የዋሃንን በተስፋ ዳቦ ለመቀብተትና በከንቱ ለማስገሳት ሲጥር እንመለከታለን፡፡ እዚህም ላይ ወያኔን አለማወቁ ያሳዝነኛል፡፡ ማንበብ ጥሩ ነው፤ ማወቅና መመራመርም ጥሩ ነው፡፡ ተስፈኝነት መልካም ነው፡፡ ተስፋ አለመቁረጥና ሩቅ ማሰብም ደግ ነው፡፡ ይሁንና ጓዳችን ውስጥ እንደመዥገር ተለጥፎ በመርዘኛ ጥርስና ምላሱ እያንገበገበን የሚገኘውን ወያኔ በሰላማዊ ትግል ይወገዳል ብሎ ማሰብና መስበክ አንድም ባለማወቅም ቢሆን የወያኔን ዓላማ የማራመድ ያህል ነው አለዚያም ሞኝነት ነው፡፡ ቢሆን በወደድን፡፡ ግን ፈጽሞ አይሆንም – ተምኔታዊነት (ዩቶፒያን መሆን) ነው፡፡ ኔልሰን ማንዴላ ለኢትዮጵያ አብነት ሊሆን አይችልም፤ ማኅተመ ጋንዲ ለኢትዮጵያ አብነት ሊሆን አይችልም፡፡ እነዚህ ምርጥ የዓለማችን ዜጎች የታገሉት ከሰዎች ጋር ነው፡፡ የኛን የሚለየው ትግላችን ከድፍን ቅል ዘረኞችና መቼም በማይበርድ እንዲያዉም እየሰላ በሚሄድ የጥላቻና የቂም በቀል አባዜ ከተሞሉ የባንዳ ልጆች ጋር ነው፡፡ ምናልባት አንዱአለም ያልተገነዘበው ይህንን ሃቅ ሊሆን ይችላል ብዬ እገምታለሁ፡፡ በዚያ ላይ በሰላማዊ ትግል ቀርቶ በመሣሪያም የሚነቀንቃቸው እንዳይኖር ሕዝቡን በማይምነት ጋርደው፣ ፍጹም ከደረጃ በታች በሆነና “A,B,C,D”ን በቅጡ በማያስለይ እንዲሁም ዜጎችን በሚከፋፍል የትምህርት ሥርዓት ትውልድን አደድበው፣ ጥቂት የማይባሉ ኢትዮጵያውያንን በማይረባ የጥቅም ፍርፋሪ ከፋፍለው፣ በዘረኛ የፌዴራል ፖሊስ፣ በደንቆሮ ካድሬና መከላከያ አፍነው፣ በቅንድብ ጥቅሻና በስልክ ቀጭን ትዕዛዝ ወንበዴዎቹ የሚፈልጉትን ፍርድ በሚያስተላልፍ ኮንዶም ዳኞችና ፍርድ ቤቶች ሀገር ምድሩን ሞልተውት፣ ዜጎችን በጎጠኛ የፀጥታና ደኅንነት መዋቅር ቀፍድደው፣ በድህነት ኮድኩደው፣ በተለይ ወጣቱን በልዩ ልዩ ሱሶችና በወሲብ የአዶከብሬ ዛር ዳንኪራ አስረግጠው፣ በመርዘኛ የጎሰኝነትና የዘረኝነት በሽታ ሕዝበ አዳምን በክለው፣ … ከጠማማ ጎጆው ባለፈ – የሰኞን ነፍሱን ወደማክሰኞ በማሳደሩ ከመደሰት በዘለለ ለሀገርና ለወገን የሚቆረቆር ዜጋ እንዳይኖር አድርገው የሀገሪቱን ኅልውና ገደል ጫፍ ላይ ጥለውታል፡፡ ይህን ኃይል በሰላማዊ መንገድ እጥላለሁ ብሎ ማሰብ ዕብደት ነው የምለውም ለዚህ ነው፡፡ የደቡብ አፍሪካው አፓርታይድ ሥርዓት የመጨረሻ ፕሬዝደንት ኤፍ ደብልይው ደክለርክ ጭንቅላቱ ውስጥ ተሸክሞት ይዞር የነበረው ሊማር የሚችል ጤናማ ነጭ አንጎል እንጂ እንደወያኔ በድንቁርና የታጀለ ከመግደልና በሰው ስቃይ ከመደሰት ውጪ ምንም የማያውቅ የገማና የበሸቀጠ ጥቁር ጭቃ አልነበረም፡፡ ወያኔን በሰላማዊ መንገድ እታገላለሁ ማለት ለወያኔ አዲስና ለራሳቸው ለአባላቱም ቢሆን ግርታን የሚፈጥር ልዩ ተፈጥሮን እንደማላበስ ይቆጠራል፡፡…     

አፄ ኃ/ሥላሴ ለጉብኝት ይሁን ለሥራ ወዳንድ ቦታ ሲሄዱ አንዲት ችግረኛ ሴት ከነልጆቿ መንገድ ዳር ቆማ “ወድቃ በተነሳችው ባንዲራችን፣ በልዑል እግዚአብሔር ይሁንብዎ…” በማለት ባንዴራ ዘርግታ ታስቆማቸዋለች፡፡ ያኔ እንደዛሬው ዘመን መሪ ሲወጣና ሲገባ ግድግዳ እያስደገፉ (የሚገርም እኮ ነው!) ለገዢዎች የኅለውና መሠረት ከመሆናቸው አንጻር ውድና ብርቅ ሊሆኑ የሚገባቸውን ዜጎች በኢሰብአዊነት ማሰቃየት አልነበረምና ጃንሆይ መኪናቸውን አስቁመው በመውረድ “ችግርሽ ምንድነው?” ብለው ይጠይቋታል፡፡ ሴትዮዋም፣ “ጃንሆይ፣ ለምግብ ያላነሱ ለሥራ ያልደረሱ ስድስት ልጆችን ጥሎብኝ ባለቤቴ ሞተ…” ብላ ችግሯን መናገር ስትጀምር በቀልደኛነት የሚታወቁት የቀድሞው ንጉሣችን አጠገባቸው አጅበዋቸው ወደቆሙ መኳንንት ዘወር ብለው “አግባኝ ነው የምትለው?” ብለው እንደዋዛ ጣል ያደረጓት ቀልድ በሴትዮዋ ጆሮ ገብታ ኖሮ ድሃ መቼም ሞኝ ነውና “ጃንሆይ! ሆኖልኝ ነው! አ’ርጎት ነው!” አለች ይባላል፡፡ ቀልድ በአግባቡ ጥሩ ነው፡፡ ኃ/ሥላሴ ሴትዮዋን እንደማያገቧት ግልጽ ነው – ሴትዮዋ ግን ድሃና በዕውቀትም ዝቅተኛ ናትና በጣለችው ተስፋ አንፈርድባትም፡፡ ከወያኔ ጉያ ሕዝባዊ ሥልጣን በሰላማዊ መንገድ ይገኛል ተብሎ ተስፋ ማድረግ ግን ከሴትዮዋ የበለጠ ጅል መሆንን የሚያመለክት እንጂ የወያኔን ተፈጥሮ ከመገንዘብ የሚመነጭ ገምቢ ዕውቀትና ጥበብ አይመስለኝም፡፡ ይህን የሚመር ቀልድ የሚቀልዱ ሰዎች ራሳቸውን ቢመረምሩ የተሻለ ነው፡፡ ሰላማዊ ትግል ደግሞም በኢትዮጵያ – ሆ!

በጦርነት የሚገኝ ነገር መልካም ነው እያልኩ እንዳልሆነ ግን ይመዝገብልኝ፡፡ ምርጫ ከጠፋ ግና ምን ይደረጋል? ከሁለት መጥፎዎች የተሻለውን መምረጥ የምንገደድበት ጊዜ ይኖራል፡፡ እናም ሰው ካልሆነ አውሬ ጋር እየታገሉ ከማለቅ ቢያንስ የራሴ ነው ከሚሉት ጨካኝና አምባገነን መሪ ጋር መፋለም ይመረጣል – ለዚያም መብቃት እኮ መታደል ነው፡፡ እንደሚመስለኝ አሁን ሰዎችን እያሳሰባቸው ያለው የማያሳስብ ነገር ነው፡፡ ቀድሞ የመቀመጫየን ያለችው ፍጡር ወድዳ እንዳልሆነ መረዳት ተገቢ ነው፡፡ “ሌላውን እሾህ በመቀመጫየ ተቀምጬ ራሴው እነቅለዋለሁ” ማለቷ ነው፡፡ እና ያልበላንን የሚያኩልን ወገኖች አደብ ቢገዙልን ብዙ እንደረዱን ይቆጠራል፡፡ ለነገሩ ወያኔን ማንም ደገፈው ማን – በማወቅም ይሁን ባለማወቅ -  ወቅቱን ጠብቆ ወረደ መቃብሩን ሳይወድ በግዱ መቀበሉ አይቀርም፡፡ አንድዬ በመንበሩ ካለ – አለም- ይህን ሁሉ ግፍና በደል የፈጸሙ ሰው መሳይ “ሰዎች” የቁናቸውን ሳይከፈሉ ይቀራሉ ብሎ ማሰብ የታሪክንና የፈጣሪን ፍርድ አለመረዳት ነው፡፡ የሞተ ይነሳል፤ የተኛ ይነቃል፤ የቆመ ይቀመጣል፤ የተጋደመ ይቆማል፡፡ ለሁሉም ጊዜ እንዳለው ዛሬ አይደለም የምናውቀው፡፡ ታሪክና እግዜሩ ወያኔ ላይ ሲደርሱ ሥራቸውን ያቆሙ ይሆን? ለጅላጅሎቹ ወያኔዎች እንዲያ ሳይመስላቸው የሚቀር አይመስለኝም፡፡ ለኔ ግን በፍጹም! ጊዜው ቀርቧል፡፡

አገባቤና አወጣጤ የተምታታ ነገር ያለበት መሆኑ ይሰማኛል፡፡ ለዚህ የተምታታ ነገሬ ማንን ይቅርታ መጠየቅ እንዳለብኝ ግን አላውቅም፡፡ የሆኖ ሆኖ የዚህ ዘመን እውነት ባብዛኛው የተዘበራረቀ በመሆኑ አላግባብ ሊፈርድብኝ የሚቃጣ እንደማይኖር እገምታለሁ፡፡ ሁሉን ቢናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራልና ወደማይቀረው ድል እየተጠጋን ስንመጣ እንጫወታለን፡፡ ማርቲን ሉተር ባይቀድመኝ እኔም “ህልም አለኝ!” ብል በወደድኩ፡፡

 

“ቀኒቷን ማንም አያውቅም፡፡ ከጥቂቶች በስተቀር ብዙኃኑ ጎጋም እንኳን የምፅዓትን የመጨረሻ ቀን አያውቃትም፡፡ እናንተ የሚገባችሁ ታጥባችሁ ታጥናችሁ መጠበቅ ነው – ከሙስናና ከዕድፍ ርቃችሁ፤ ከዘረኝነት አረንቋና ከሆዳምነት ተቆጥባችሁ፤ አስተዋይነትን ተላብሳችሁ፣ በወረተኛ ወጀባዊ ንፋስ እንዳትወሰዱ ተጠንቅቃችሁ … ፡፡ ይሁንና ምልክቶቹን ስታዩ የቀኒቷን መቅረብ ትረዳላችሁ፡፡ ምልክቶቹን ያዬ ትውልድ ከምፅዓት በፊት የምትገለጠዋን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ቀን ያያታል፡፡ …” (‹መጽሐፈ ትንሣኤ ኢትዮጵያ› ፣ ምዕራፍና ቁጥር የማይነበብ!)  

በየነ

 More on —-http://www.freeandualemaragie.org/?p=359

ባዕት ዕንባ በልታ። (ከሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 13.08.2014 ( ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

xxe

በትቢያ – ድሪቶ

በቋሰኛው – ጉቶ

ተመተረ ዘመን – በቅንቅን ተበልቶ፤

በበደል ተቁላልቶ

በግለት ተወግቶ

በቁርሾ ተሰልቶ።

ሲናሳ መራራ – የአስተሳሰብ ንቅዘት

ሲሰነብት እሬት – የባንዳነት ስባት

- ብነት።

ትናትን – ገደለ

ዛሬን – ረሸነ

ነገን – አተነነ

ዬበነነ።

ዞጋማ ቁሌቱ

ቅብረት ነው ስሌቱ

የወያኔ ማቱ

ጥፋቱ።

ዬት ሳውቅህ – በምንህ!?

ቃር=== ማ —- ነው ቃርሚያህ

የደም ሲቃ ግብርህ።

ዘረፋ – ሰርዴታህ

ዕበለትም – አትራፊህ፤

ሲካዳህ – ዕለትህ

የቆዬ ሰው፤ – ይይህ

ትነቱ ዘመድህ – የዘለአለም ስንቅህ

ፍልሰትህ —።

ኤሉሄ! ትላለች እናት ልጇን አጥታ፣

ኤሉሄ! ትላለች ባዕት ዕንባን በልታ፣

ኤሉሄ! ይለዋል ምጣድ የድርቅ ዋልታ

ኤሉሄ ትላለች – እንሥራ ተጠምታ፤

የሲሳዩ ማሳ በዕንባ እዬተፈታ

በጫካ -  ገበጣ።

ሸንተረር አነባ – በጉልበት ሲመታ

ወንዙም ሆዱ ባባ – በእርግጫ ሲለጋ

አፈር አለቀሰች – ተግርፋ በአለንጋ ….

… በበቀል ተወራ – ለድርቡሽ ተሰጥታ

ከውስጧ – ተራቁታ።

ጥንት – ከጥዋቱ፤ ልጇ ተቆላምጦ

የሚፈልገውን እንዳዬው መራርጦ …

ታዬ በወያኔ – ቀኑ ተገልብጦ —-

…. ተቀማ ዕህሉን፤  ወገን በወረንጦ

አምጦ።

ወያኔ የሚሉት —- የመከራ ጥሪት

ወያኔ የሚሉት —  የአሳሩ ስሌት

ወያኔ የሚሉት —- የመጋኛ ሌሊት

ወያኔ የሚሉት — የአሲድ እፉኝት

ህማማት።

የዋህነት – ቀብሮ

ቅንነትን – ቀብሮ

አብሮነት – ተቀብሮ

ትህትናንም – ቀብሮ

መተዛዘን – ቀብሮ

ነፃነት ተባሮ

መርዛማው ወያኔ – ውሳጣችን – ቆፍሮ

አዬነው እራሱን በጥፋት ተቀብሮ፤

በመንደር ተዋቅሮ

እሮ!

አመዳማ — ጉዞ

ጎርብጥባጣ — አዞ

ሳጥናኤል — ተመዞ

ለጥፋትም — ታዞ፤

ታሪክን – አንቅዞ

ትውፊትን – አፍዝዞ

ባህልን – ጠምዝዞ

መንፈስ –  ተገንዞ

ናውዞ።

ሞት ቢሞት ሞቱ ነው

ቢኖርም ሞቱ ነው

ሰኔልና ቹቻ

ስለት ለቋቁቻ።

 

 

28.06.2014 ሲዊዘርላንድ ቪንቱርቱር ተጣፈ።

 

መከራን ሳዳምጠው ደሜን አገኘዋለሁ!

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

 

 

 

 

Viewing all 1664 articles
Browse latest View live